• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የወንጀል ክስ ማንሳት እና ማስቀጠል የሚቻለዉ መቼ ነዉ?

January 12, 2022 09:27 am by Editor Leave a Comment

የክስ ማንሳት የፍሬ ነገር ይዘትና ስነ ሥርዓት በወ/መ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 122 ስር በአምስት ንዑስ አንቀጾች ተጠቃሎ ይገኛል፡፡ በይዘቱም፡-

• ከከባድ የሰው ግድያ እና ከከባድ ውንብድና ወንጀሎች ውጭ ዐ/ሕግ ከፍርድ በፊት ክስ ማንሳት ይችላል፡፡

• ክስ የሚነሳው በዐ/ህጉ ጥያቄ ወይም በሌላ የመንግስት አካል ትዕዛዝ ሊሆን ይችላል፡፡

• ክሱ የሚነሳው በፍ/ቤት ፈቃድ ሲሆን ፍ/ቤቱ ለመከልከልም ሆነ በመፍቀድ ምክንያቱን ማስቀመጥ አለበት፡፡

• በወ/መ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 113 መሰረት አዲስ ክስ ካልቀረበ ተከሳሹ ለግዜው ይለቀቃል፡፡

• የክሱ መነሳት ዐ/ሕግ ክስን ከማንቀሳቀስ አያግደውም፡፡

የሚል ሀሳብ ያለው ነው፡፡

የፍትሕና የሕግ ሥርዓት ምርምር ኢንስቲቲዩት ባዘጋጀው ረቂቅ የወንጀል ስነ-ሥርዓት ሕግ አንቀጽ 119 ስር ዐ/ሕግ ከፍርድ ቤት በማንኛውም ጊዜ ክስ ማንሳት የሚችል መሆኑን በወ/መ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 122 ስር የተመለከተው የፍርድ ቤት ፈቃድና በተወሰኑ የወንጀል ክሶች ላይ የተደረገው ክልከላ ተነስቷል፡፡ አብሮ በተዘጋጀው የህጉ ሀተታ ዘምክንያትም ጉዳዩን ዐ/ሕግ ካልተከታተለው በውጤት ደረጃ ልዩነት የሌለው በመሆኑ በተወሰኑ ወንጀሎች የተደረገው ክልከላ እና የፍ/ቤት ፈቃድ መጠየቅ አስፈላጊ ሆኖ አልተገኘም በሚል አስፍሯል፡፡

የኢ.ፌ.ድሪ. አስፈጻሚ አካላትን ስልጣን እና ተግባር ለመወሰን የወጣው አዋጅ ቁ. 691/2003 የፍትሕ ሚኒስቴርን ስልጣንና ተግባር በዘረዝረው አንቀጽ 16 ስር በንዑስ አንቀጽ 6 “… በቂ ምክንያት ሲኖር በህጉ መሰረት ክሱን ያነሳል…” በሚል ያስቀምጣል፡፡ የፌደራል ጠቅላይ ዐ/ሕግ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁ. 947/2008 ክስ ማንሳትን አስመልክቶ “… የፌደራል ጠ/ዐ/ሕግ ለህዝብ ጥቅም አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው ጠ/ሚንስትሩን በማማከር ክስ ያነሳል፡፡ የተነሳም ክስ እንዲቀጥል ያደርጋል፡፡” የሚል ድንጋጌ አካቷል፡፡ የፍትሕ ሚኒስቴር በ2003 ባዘጋጀው የኢትየጲያ የወንጀል ፖሊሲ ላይ በገጽ 37 ክስ ማንሳትን አስመልክቶ “… ዐ/ሕግ የመሰረተውን የወንጀል ክስ ክርክር መቀጠል የህዝብና የመንግስት ጥቅምን አያስጠብቅም ብሎ ካመነ ለፍ/ቤቱ በማስታወቅ ክስን ማቋረጥ ይችላል፡፡ … በዐ/ሕግ ጥያቄ የተነሳ ክስ ለህዝብ ጥቅም አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ የተቋረጠውን የክስ ሂደት የሚቀጥል መሆኑ…” በሚል አስቀምጧል፡፡

ከላይ የተመለከቱት ህጎች በጥቅሉ ክስ ማንሳት በመቀጠል ላይ ያለ የክርክር ሂደት ለሰፊና ለተሻለ ጥቅም ሊቋረጥ የሚችልበት ሥርዓት መሆኑን ያመለክታሉ፡፡ በአንዳንድ የሕግ ስርኣቶች የወንጀል ክስ ለማስጀመር የግድ የጽሁፍ አቤቱታ መቅረብ ያለበት እንደመሆኑ መጠን (Accusatory principle) በፍ/ቤት ተቀባይነት አግኝቶ የተጀመረን ክርክር ዐ/ሕግ ማንሳት አይችልም፡፡ (Principle of immutability) በሌሎች የሕግ ስርዓቶች ክስን ለማንሳት አሳማኝ የሆነ ምክንያት በማቅረብ በፍ/ቤት ፈቃድ (Up on the consent of the court) ሊፈጸም ይችላል፡፡ የወ/መ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 122 በሁለቱ የሕግ ስርዓቶች መካከል የተቀመጠ ይመስላል፡፡ በመርህ ደረጃ በፍ/ቤት ፈቃድ በበቂ ምክንያት ክስ ማንሳት የሚቻል ሲሆን በከባድ ወንጀሎች ላይ ግን ክልከላ ተደርጎበታል፡፡

በአጠቃላይ በክስ ማንሳት ወቅት የዐ/ሕግ፤ የመንግስትና የፍ/ቤት ሚና እና ሀላፊነት ምንድን ነው? (ለማስቀጠልም-) ክስ ለማንሳትና ለማስቀጠል ተገቢ ሊሆን የሚችልና ተቀባይነት ሊኖረው የሚገባ ምክንያት የቱ ነው? የሚሉት ነጥቦች በትኩረት መመርመር የሚኖርባቸው ጉዳዮች ናቸው፡፡

ከላይ በተጠቀሱት ህጎች ውስጥ በአንድ በኩል ክስን ለማንሳትና ለማስቀጠል በፍ/ቤት ፍቅድ ስልጣን ላይ ወጥ አቋም ባያንጸባርቁም ክስ ማንሳትና ማስቀጠል በቂ ምክንያት ሊኖረው ወይም የህዝብ ጥቅምን መሰረት ያደረገ ሊሆን እንደሚገባ ያሰምሩበታል፡፡ የቀረበው ምክንያት ተገቢ መሆን አለመሆኑን ደግሞ መመርመር የፍ/ቤት ስልጣን ነው፡፡ በሌላ በኩል ፍ/ቤቱ በጉዳዩ ላይ ብይን ሲሰጥ ምክንያቱን ማስቀመጥ አለበት፡፡ ዐ/ሕግ አቤቱታውን ሲያቀርብም ምክንያት ማቅረብ ያለበት መሆኑ ግልጽ ነው፡፡

በዘፈቀደ ክስን ማንሳትና ማስቀጠል ከፍ/ቤት ነጻነት ጋር የሚያያዝ ነው፡፡ የፍርድ ቤቶች ነጻነት አንድ ጉዳይ በፍ/ቤት ከቀረበ በኋላ ፍ/ቤቱ በጉዳዩ ላይ ባለሙሉ ስልጣን በመሆኑ በእያንዳንዱ ጉዳይ የመወሰን ስልጣንን ይጎናፀፋል፡፡ እንኳንስ በወንጀል ፍትሕ አስተዳደር በፍትሐብሔር ጉዳዮች እንኳ ክስ በፍ/ቤቱ ፈቃድ እና ያለፈቃድ ካነሳ በኋላ ማስቀጠሉ ላይ ትልቅ ልዩነት ይፈጥራል፡፡ የፍ/ቤቱን ፈቃድ ለማግኘት ምክንያት ማቅረብ የሚያስፈልግ ሲሆን ከፈቃድ ውጭ ክስን ማንሳት ደግሞ ወደ ፊት በተመሳሳይ ጉዳይ ሌላ አዲስ ክስ ማቅረብ እንዳይችል ያደርገዋል፡፡ (የፍ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 278 – 279) በወንጀል የፍትሕ አስተዳደር ውስጥ በሁሉም መልኩ ሊባል በሚችል መጠን ትኩረትና ጥብቅ ቁጥጥር ያሻል፡፡

የጉዳዩን ጥቅል ይዘት በመመልከት ክስ ለማንሳትም ሆነ የተነሳ ክስ ለማስቀጠል ለህዝብ ጥቅም የተደረጉ መሆናቸውን ፍ/ቤቶች መገምገም አለባቸው፡፡ የክስ ማንሳትና ማስቀጠል ሥርዓት ተገቢ ላልሆነ አላማ እንዳይውል መከልከል አለበት፡፡ በወንጀል የፍትሕ አስተዳደር ላይ የአንድን ሰው የፍትሕ ሥርዓት ግንዛቤ እና እምነት በሚቃረን መልኩ መፈጸም የለበትም፡፡ የህዝብ ጥቅም፤ ፍትሐዊነት ቅንልቦና የሕግ ሥርዓት (ሂደት) (Public interest, Fairness, Good Faith (Bonafide) & Fairness) ታሳቢ ተደርገው የሚፈጸም ሥርዓት ነው፡፡ የማስረጃ ማነስን (Paucity of evidence) የግዜ፤ ገንዘብ እና የውጤታማነት ጉዳዮችን (Time, money & chance of success) ታሳቢ ተደርጎ ክስ የማይነሳ ሲሆን በነዚሁ ታሳቢነትም አይንቀሳቀስም፡፡

በእኛ ሀገር የሕግ ሥርዓት የህዝብ ጥቅም / በቂ ምክንያት የሚሉት የትኞቹን ምክንያቶች ነው የሚለው በግልጽ በሕግ ወይም በፍርድ ተቀምጠው ባይገኙም በዳበሩ የሕግ ስርዓቶች ውስጥ እነዚህ ምክንያቶች በተለመደ ሁኔታ የትኞቹ እንደሆኑ ይታወቃል፡፡ በዚህም፡-

• ክሶቹ ፖለቲካዊ ወይም ግለሰባዊ በቀልን መሰረት አድርገው ቀርበው ሲገኙ፤ (Political & personal vendetta)

• መንግስታዊ እና ህዝባዊ በሆነ ምክንያት ክስን ለመቀጠል የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎች አለመኖር፤

• በሁኔታዎች መቀያየር ምክንያት በክሱ መቀጠል ህዝብና መንግስትን የሚጎዳ ሆኖ ሲገኙ ናቸው፡፡

በክርክር ቀረቦ በተሰማ አንድ ጉዳይ ዐ/ሕግ የክስ ማንሳት አቤቱታ የቀረበ ሲሆን ምክንያቱም “ተጨማሪ ማጣራት የሚገባን ጉዳይ ስላገኘን” የሚል ነበር፡፡ ፍ/ቤቱም የቀረበውን ምክንያት ሳይመረመር በጥቅሉ ተቀብሎት ክሱ ተቋርጧል፡፡ በሌላ ግዜ በተመሳሳይ ጉዳይ ዐ/ሕግ ክስ እንዲንቀሳቀስ አቤቱታ ያቀረበ ሲሆን የሰጠው ምክንያትም 1ኛው ምስክር ቃሌን አቃናለሁ ያለ በመሆኑ መዝገቡ ይንቀሳቀስ ምስክሮች እንደ አዲስ ይሰሙልኝ በሚል ነው፡፡

በመሰረቱ የቀረበው ምክንያት አሳማኝ እና ለህዝብ ጥቅም የተደረገ ስለመሆኑ ከመመርመሩ በፊት ክስ ለማንሳት የቀረበው ምክንያትና ክስ ለማስቀጠል የቀረበው ምክንያት የተለያዩ ናቸው፡፡ በሌላ በኩል በክርክሩ ሂደት ተሰምተው የተመለሱ ምስክሮችን ክስን በማቋረጥ እንደገና ቀርበው እንዲሰሙ ማድረግ የክርክር አመራር ስርኣትን ያልተከተለ እና ህገ ወጥ ነው፡፡

በአጠቃላይ የክስ ማንሳትና ማንቀሳቀስ የዐ/ሕግ ያልተሸራረፈ መብት ሳይሆን በሕግ መሰረት በተቋቋሙ ፍ/ቤቶች የሚመራ የወንጀል ፍትሕ ሥርዓት መሆኑን መገንዘብ ያሻል፡፡

አንዋር መሐመድ ~ አቢሲኒያ ሎው

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Law, Left Column Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule