• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሸዋሮቢት ከተማ በአሸባሪው ትህነግ ታጣቂዎች በቡድን የተደፈሩት እናት ራሳቸውን አጠፉ!

December 5, 2021 02:27 pm by Editor 1 Comment

“መግደልም መድፈርም መብታችን ነው” – “ተገድደነው የዘመትነው” የሚሉት የትህነግ ታጣቂዎች

ዕድሜያቸው 50ዎቹን ያለፈው የሸዋሮቢት ከተማ ነዋሪዋ አዛውንት በአሸባሪው የህወሓት ታጣቂዎች በቡድን ከተደፈሩ በኋላ ራሳቸውን አጥፍተዋል።

ፖሊስና የአካባቢው የዓይን እማኞች በሥፍራው ለሚገኙት የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘጋቢዎች እንደገለጹት፤ ዕድሜያቸው 50ዎቹን የተሻገረውና የሸዋሮቢት ከተማ ቀበሌ 02 ነዋሪ የነበሩት ወይዘሮ ሞሚና አህመድ (ስማቸው የተቀየረ) በአሸባሪው የህወሓት ታጣቂዎች በመደፈራቸው የልጄን ዓይን ከማይ ብለው ራሳቸውን አጥፍተዋል።

ወ/ሮ ሞሚና የማገዶ እንጨት በመሸጥና እንጀራ በመጋገር የሚተዳደሩ ሲሆን፤ የ15 ዓመት ታዳጊ ልጅ እንዳላቸው የሸዋሮቢት ከተማ ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ክፍል ሀላፊ ኮማንደር አህመድ መሐመድ ለኢፕድ ገልጸዋል።

ዛሬ ትህነግን በመቃወም ሰለፍ ያደረጉ ካነገቡት መፈክሮች አንዱ

ኮማንደሩ እንዳሉት፤ ግፈኛው ቡድን ልጃቸው ላይ በር ቆልፎ እናቱን ወደ ሌላ ቤት በመውሰድ አስነዋሪውን ግፍ ፈጽሟል።

በተመሳሳይ ከወ/ሮ ሞሚና ጋር በአንድ ቤት በአሸባሪው ቡድን ታጣቂዎች አብረው የተደፈሩት ወይዘሮ አለምሸት አሸብር (ስማቸው የተቀየረ) ከሟች ጋር አንድ ቤት እንደነበሩ እና እየተፈራሩቁ በሰው ልጅ ላይ ሊፈጸም ቀርቶ ሊታሰብ የማይችል በደል እንዳደረሱባቸው ይናገራሉ።

ዛሬም በሳቸውና በጓደኛቸው ላይ የተፈጸመው በደል ያንገበግባቸዋል። እሳቸው በህይወት ተርፈው ጓደኛቸውን የነጠቃቸውን ግፍም በሲቃ ተሞልተው ይናገራሉ።

ጓደኛየ በደሉ ከደረሰባት በኋላ “ከዚህ በኋላ የልጄን አይን የማይበት ዐይን የለኝም’ ብላ ራሷን አጠፋች” ሲሉ ተናግረዋል።

እርሳቸውም በታጣቂዎቸ የተደፈሩት በቡድን መሆኑን የገለጹት ወይዘሮ አለምሸት፤ ከሞራል ስብራቱና በደሉ ባሻገር አከላዊ ህመም እየተሰማቸው እንደሆነ ለኢፕድ ገልጸዋል።

የራስ ጸጉራቸውን በመንጨት ብዙ እንግልት በማድረስ ሁለቱን አዛውንት አየተፈራረቁ ድርጊቱን እንደፈጸሙባቸው ወይዘሮዋ የነገሩን ሀዘንና ሲቃ በተሞላበት አንደበታቸው ነው።

እነዚህ አረመኔዎች ግፉን ከመፈጸማቸው በፊት “እንጀራ አምጡ” ብለው ጠይቀው በእጃቸው ከበሉ በኋላ እንደሆነና፤ “መግደልም መድፈርም መብታችን ነው” እያሉ በመሳሪያ አስፈርርተው ድርጊቱን እንደፈጸሙ ተጎጂዋ ተናግረዋል።

አሸባሪው የህወሓት ቡድን ወረራ በፈጸመባቸው የአማራና አፋር አካባቢዎች ንጹሃንን በጅምላ መግደል፣ ህጻናትና አዛውንት ሴቶችን መድፈርና ንብረት ማውደም መፈጸሙን የሰብአዊ መብት ተቋማት ጭምር እየገለጹ ይገኛሉ። (ኢፕድ፣ አዲሱ ገረመው፣ ሸዋሮቢት)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: operation dismantle tplf, rape victim, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    December 5, 2021 08:19 pm at 8:19 pm

    በምድራችን አረምና አራሙቻ እየበቀለ ህዝባችን በዚህም በዚያም ማወክ ከጀመረ ረጅም ዘመን ቆጥረናል። አብሮ መክሮ ወገኑን ያስገደለ፤ ምንም ባልሰራው (ችው) በጥይት ተደብድበው የሞቱ፤ አካለ ጎድሎ የሆኑ፤ ይህን ያዪ ህይወታቸውን ለማትረፍ ወደ ጎረቤት ሃገሮችና ወደ አውሮፓና ሌሎችም የነጭና የዓረብ ሃገሮች ሲያፈተልኩ እንደ ወጡ ቀርተዋል። አሁን ወያኔ የከተማ ሰው ከሆነ ወዲህ የተሰራውና የሚሰራው ግን ከሰውነት ደረጃ የወረደ ፍጽም አውሬነት ነው። አሁን በምንፋተግበት የእብዶች ጦርነት የውሸት ጋጋታና የማጋነን ወሬዎች ውስጥ ስንት ሃሰትና የፕሮፓጋንዳ ጡሩንባ እንደሚነፋ ልብ ላለ ይታየዋል። ታዲያ ከመቀሌ ዶ/ር ደብረጽዪንና አንድ የወያኔ ጄኔራል ጦርነቱ አልቋል ከማን ጋር ነው የምንደራደረው ሲሉን አሁን ደግሞ ዶ/ር አብይ ጦርነቱ አልቋል፤ ወያኔ ተበትኗል ተብለናል። በዚህ መካከል ግን ህዝባችን በዚህም በዚያም እንደ ቅጠል ይረግፋል። የዶ/ር ደብረጽዪንን የቅርብ ቀን መግለጫ ላዳመጠ የወያኔን እብደት ማቆሚያ እንደለሌው ማየት ይቻላል። ትላንትም ውሸት፤ ዛሬም ውሸት፤ ትላንትም የትግራይ ህዝብ ዛሬም በትግራይ ህዝብ ላይ ቁማር መጫወት። አሁን ማን ይሙት ወያኔዎች ስፍራ ለቀው የወጡት ወደው ነው? ጭራሽ? እየገደሉ፤ እያፈረሱ፤ እየዘረፉ፤ በደቦ ሴቶችን እየደፈሩ ነው በጦርነት ተሸንፈውና እየተሸነፉ እንጂ። ይህ ትውልድ ከዚህ ፍትጊያ እንኳን ተርፎ መኖር ቢችል የህሊና ችግር እንደሚኖርበት ምንም አያጠራጥርም። ታላቋ ትግራይን እንመሰርታለን የሚለው የወያኔ ጡሩንባ ያቺ ታላቅ ትግራይ ለማን እና በእነማን ነው የምትመሰረተው? ሰው ሁሉ ካለቀና አካለ ጎደሎ ከሆነ በህዋላ ለማን ነው ያቺ የህልሟ ትግራይ የምትቆመው?
    ልቤ እጅግ ያዝናል በደረሰባት በደል የተነሳ ደጋፊ አጥታ ራሷን ያጠፋቸው እህታችን ሳስብ። አይ ሃገር እንዲህ ሆንን ብለን ብለን ዘርና ቋንቋ እየቆጠርን ሰውን ብቻ ሳይሆን እንስሳትንና የተከመረ እህልን ሁሉ የምናቃጥል የሙታን ጥርቅም። ወያኔ ጉድጓድ መግባት ያለበት ድርጅት ነው። በሚሊዪን የሚቆጠሩ ሰቆቃዎችን ያደረሰና በማድረስ ላይ ያለ ድርጅት ምህረት ሊደረግለት አይገባም። እኔን የሚያናድኝ የወያኔ የጭፍን ደጋፊዎች የትግራይ ተወላጆች ናቸው። እውነቱንና ፕሮፓጋንዳውን እንዴት ሰው መለየት ይሳነዋል? በወያኔ ስንት የትግራይ ልጆች ነው የተገደሉት? አሁንስ በዚህ ግጭት የሚረግፉት? ደብረጽዪን አሁንም ጥሉ ከአማራ ህዝብ ጋር ነው። ልብ ይሰብራል። አማራ የትግራይ ህዝብ ላይ ምን በደል ፈጸመ? ወያኔ ግን ለዘመናት የአማራን ህዝብ ሲያተራምስና አምካኝ መርፌ ሁሉ ሲወጋ የኖረ ለመሆኑ አሊ የማይባል መረጃ አለ። ያው ግን የሽፍጠት ፓለቲካ ጠላትህ መጣ፤ ተወረርክ፤ ተያዝክ፤ እናትህ ሚስትህ እህትህ ልትደፈር ነው በማለት ነው ሰውን ወደ እሳት የሚማግደው። ዶ/ር አብይ የውጭ ሃይሎች ከወያኔ ጋር ሆነው እየተዋጉ ነው እንዳለው ሁሉ አሁን ደግሞ የወያኔ ጭፍን መሪ የውጭ ሰዎች ገብተው እየተዋጉን ነው በማለት አላዝኗል። በሁለቱም ጎን ግን የቀረበልን መረጃ የለም። ይህ ደግሞ እንደተባለው የጦርነትን ቀዳሚ ሰለባ እውነት ራሷ መሆኗን ያሳየናል።
    አርቲ ቡርቲውን የሃበሻ ፓለቲካ ወደ ኋላ ጥሎ ነገሮችን በረጋ መንገድ ለተመለከተ የዓለም መሳቂያ መሆናችን ያሳያል። እኛው የቆመን ሁሉ አፍርሰን፤ አቃጥለን አሁን ተመልሰን ተራብን፤ በሽታ ገባ፤ እንዲህና እንዲያ ሆንን ብንል ሰሚ የለም። የሰሙን ከመሰለንም እኛኑ የሚያናኩር ነገር ቋጥረው እንጂ በቅንነት ሃገርን አይረድም። ይህ አሁን በድህረ ገጾች ላይ የምናየውና የምንሰማው የቀድሞ የአውሮፓና የአሜሪካ ዲፕሎማቶች በዶላር ከተገዙ ሃገር ሽያጭ ሃበሾች ጋር በመሆን የሚሸርቡት ሴራ ከአንድ ምንጭ መቀዳቱን ያሳያል። ያስገርማል። It is rehearsed play. በተናጠልም ሆነ በህብረት የሚሰጧቸውን ቃለ መጠይቆች፤ ማስጠንቀቂያዎች፤ የድጋፍ ሃሳቦች ላጤነ ከአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ፓሊሲ የተቀዳ ሁሉም የፈረሙበት ለመሆኑ አያጠራጥርም። እነዚህ ናቸው ሰለ ሰላምና ዲሞክራሲ ዓለም ሊያስተምሩ የሚሹት። የራሷ ሲያርባት የሰው ታማስላለች እንዲሉ። ዛሬ በአውሮፓ፤ በአሜሪካ በራችው ድረስ የተኮለኮሉት ጥገኝነት ጥያቄዎች የመጡት ነጩ ዓለም ተባብረው ከደረመሷቸው ሃገሮች ነው። ገና ብዙ ይነጉዳል። ግን ያልታበሱ እንባዎች አይዞሽ አዞህ ብሎ የሚያጽናናቸው ወገን ሳያገኙ በተስፋ መቁረጥ ራሳቸውን ሲያጠፉ ምንኛ ያሳዝናል። ዘሩን ጎሳውን፤ ቋንቋውንና ሃይማኖቱን ወግድልኝ ብሎ በሰውኛ ልብ ላሰበ እየየው ያሰኛል። ግን ሁሉ አልቃሽና አስለቃሽ በሆነበት የሃበሻ ምድር መሰማማት የት አለና። ግን መቼ ይሆን መገዳደላችን የሚያበቃው? ጊዜ ይመጣ ይሆን? አላውቅም።
    እውቁ አሜሪካዊ የህዋ ተመራማሪ Carl Sagan ከዘመናት በፊት “Pale Blue Dot” እንዲህ ይለናል። ፈልጋችሁ ራሱ ሲናገር ብትሰሙት የበለጠ የሃሳቡ ጥልቀት ይገባቹሃል። ያም ሆነ ይህ ቅንጫቢ ሃሳቡ እንሆ።
    The Earth is a very small stage in a vast cosmic arena. Think of the rivers of blood spilled by all those generals and emperors so that, in glory and triumph, they could become the momentary masters of a fraction of a dot. Think of the endless cruelties visited by the inhabitants of one corner of this pixel on the scarcely distinguishable inhabitants of some other corner, how frequent their misunderstandings, how eager they are to kill one another, how fervent their hatreds.
    አምናለሁ በዚህም በዚያም ለሰው ልጅ ህሊናው ይመሰክርለታል። ግን ምንም ያልሰራ ሰው ዝቅዝቆ የሚሰቅል፤ ይህ መሬት ላይ ያንቺ ልጅ አይወለድም በማለት የነፍሰጡር ሴት ሆድ ቀዶ ልጅ የሚያወጣ፤ እናቱን፤ እህቱን ወንድሙን አባቱን ገድሎ የሚፎክር፤ ያለምንም ሃፍረት ሴት ልጆችን በደቦ የሚደፍር የአውሬ ስብስብና መሪዎችሁ በመዘዙት ሰይፍ ይወድቃሉ። በታሪክ ያየነው ያን ነው። እስከዚያው ግን በዚህም በዚያም መገዳደሉ ይቀጥላል። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule