• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሸዋሮቢት ከተማ በአሸባሪው ትህነግ ታጣቂዎች በቡድን የተደፈሩት እናት ራሳቸውን አጠፉ!

December 5, 2021 02:27 pm by Editor 1 Comment

“መግደልም መድፈርም መብታችን ነው” – “ተገድደነው የዘመትነው” የሚሉት የትህነግ ታጣቂዎች

ዕድሜያቸው 50ዎቹን ያለፈው የሸዋሮቢት ከተማ ነዋሪዋ አዛውንት በአሸባሪው የህወሓት ታጣቂዎች በቡድን ከተደፈሩ በኋላ ራሳቸውን አጥፍተዋል።

ፖሊስና የአካባቢው የዓይን እማኞች በሥፍራው ለሚገኙት የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘጋቢዎች እንደገለጹት፤ ዕድሜያቸው 50ዎቹን የተሻገረውና የሸዋሮቢት ከተማ ቀበሌ 02 ነዋሪ የነበሩት ወይዘሮ ሞሚና አህመድ (ስማቸው የተቀየረ) በአሸባሪው የህወሓት ታጣቂዎች በመደፈራቸው የልጄን ዓይን ከማይ ብለው ራሳቸውን አጥፍተዋል።

ወ/ሮ ሞሚና የማገዶ እንጨት በመሸጥና እንጀራ በመጋገር የሚተዳደሩ ሲሆን፤ የ15 ዓመት ታዳጊ ልጅ እንዳላቸው የሸዋሮቢት ከተማ ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ክፍል ሀላፊ ኮማንደር አህመድ መሐመድ ለኢፕድ ገልጸዋል።

ዛሬ ትህነግን በመቃወም ሰለፍ ያደረጉ ካነገቡት መፈክሮች አንዱ

ኮማንደሩ እንዳሉት፤ ግፈኛው ቡድን ልጃቸው ላይ በር ቆልፎ እናቱን ወደ ሌላ ቤት በመውሰድ አስነዋሪውን ግፍ ፈጽሟል።

በተመሳሳይ ከወ/ሮ ሞሚና ጋር በአንድ ቤት በአሸባሪው ቡድን ታጣቂዎች አብረው የተደፈሩት ወይዘሮ አለምሸት አሸብር (ስማቸው የተቀየረ) ከሟች ጋር አንድ ቤት እንደነበሩ እና እየተፈራሩቁ በሰው ልጅ ላይ ሊፈጸም ቀርቶ ሊታሰብ የማይችል በደል እንዳደረሱባቸው ይናገራሉ።

ዛሬም በሳቸውና በጓደኛቸው ላይ የተፈጸመው በደል ያንገበግባቸዋል። እሳቸው በህይወት ተርፈው ጓደኛቸውን የነጠቃቸውን ግፍም በሲቃ ተሞልተው ይናገራሉ።

ጓደኛየ በደሉ ከደረሰባት በኋላ “ከዚህ በኋላ የልጄን አይን የማይበት ዐይን የለኝም’ ብላ ራሷን አጠፋች” ሲሉ ተናግረዋል።

እርሳቸውም በታጣቂዎቸ የተደፈሩት በቡድን መሆኑን የገለጹት ወይዘሮ አለምሸት፤ ከሞራል ስብራቱና በደሉ ባሻገር አከላዊ ህመም እየተሰማቸው እንደሆነ ለኢፕድ ገልጸዋል።

የራስ ጸጉራቸውን በመንጨት ብዙ እንግልት በማድረስ ሁለቱን አዛውንት አየተፈራረቁ ድርጊቱን እንደፈጸሙባቸው ወይዘሮዋ የነገሩን ሀዘንና ሲቃ በተሞላበት አንደበታቸው ነው።

እነዚህ አረመኔዎች ግፉን ከመፈጸማቸው በፊት “እንጀራ አምጡ” ብለው ጠይቀው በእጃቸው ከበሉ በኋላ እንደሆነና፤ “መግደልም መድፈርም መብታችን ነው” እያሉ በመሳሪያ አስፈርርተው ድርጊቱን እንደፈጸሙ ተጎጂዋ ተናግረዋል።

አሸባሪው የህወሓት ቡድን ወረራ በፈጸመባቸው የአማራና አፋር አካባቢዎች ንጹሃንን በጅምላ መግደል፣ ህጻናትና አዛውንት ሴቶችን መድፈርና ንብረት ማውደም መፈጸሙን የሰብአዊ መብት ተቋማት ጭምር እየገለጹ ይገኛሉ። (ኢፕድ፣ አዲሱ ገረመው፣ ሸዋሮቢት)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: operation dismantle tplf, rape victim, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    December 5, 2021 08:19 pm at 8:19 pm

    በምድራችን አረምና አራሙቻ እየበቀለ ህዝባችን በዚህም በዚያም ማወክ ከጀመረ ረጅም ዘመን ቆጥረናል። አብሮ መክሮ ወገኑን ያስገደለ፤ ምንም ባልሰራው (ችው) በጥይት ተደብድበው የሞቱ፤ አካለ ጎድሎ የሆኑ፤ ይህን ያዪ ህይወታቸውን ለማትረፍ ወደ ጎረቤት ሃገሮችና ወደ አውሮፓና ሌሎችም የነጭና የዓረብ ሃገሮች ሲያፈተልኩ እንደ ወጡ ቀርተዋል። አሁን ወያኔ የከተማ ሰው ከሆነ ወዲህ የተሰራውና የሚሰራው ግን ከሰውነት ደረጃ የወረደ ፍጽም አውሬነት ነው። አሁን በምንፋተግበት የእብዶች ጦርነት የውሸት ጋጋታና የማጋነን ወሬዎች ውስጥ ስንት ሃሰትና የፕሮፓጋንዳ ጡሩንባ እንደሚነፋ ልብ ላለ ይታየዋል። ታዲያ ከመቀሌ ዶ/ር ደብረጽዪንና አንድ የወያኔ ጄኔራል ጦርነቱ አልቋል ከማን ጋር ነው የምንደራደረው ሲሉን አሁን ደግሞ ዶ/ር አብይ ጦርነቱ አልቋል፤ ወያኔ ተበትኗል ተብለናል። በዚህ መካከል ግን ህዝባችን በዚህም በዚያም እንደ ቅጠል ይረግፋል። የዶ/ር ደብረጽዪንን የቅርብ ቀን መግለጫ ላዳመጠ የወያኔን እብደት ማቆሚያ እንደለሌው ማየት ይቻላል። ትላንትም ውሸት፤ ዛሬም ውሸት፤ ትላንትም የትግራይ ህዝብ ዛሬም በትግራይ ህዝብ ላይ ቁማር መጫወት። አሁን ማን ይሙት ወያኔዎች ስፍራ ለቀው የወጡት ወደው ነው? ጭራሽ? እየገደሉ፤ እያፈረሱ፤ እየዘረፉ፤ በደቦ ሴቶችን እየደፈሩ ነው በጦርነት ተሸንፈውና እየተሸነፉ እንጂ። ይህ ትውልድ ከዚህ ፍትጊያ እንኳን ተርፎ መኖር ቢችል የህሊና ችግር እንደሚኖርበት ምንም አያጠራጥርም። ታላቋ ትግራይን እንመሰርታለን የሚለው የወያኔ ጡሩንባ ያቺ ታላቅ ትግራይ ለማን እና በእነማን ነው የምትመሰረተው? ሰው ሁሉ ካለቀና አካለ ጎደሎ ከሆነ በህዋላ ለማን ነው ያቺ የህልሟ ትግራይ የምትቆመው?
    ልቤ እጅግ ያዝናል በደረሰባት በደል የተነሳ ደጋፊ አጥታ ራሷን ያጠፋቸው እህታችን ሳስብ። አይ ሃገር እንዲህ ሆንን ብለን ብለን ዘርና ቋንቋ እየቆጠርን ሰውን ብቻ ሳይሆን እንስሳትንና የተከመረ እህልን ሁሉ የምናቃጥል የሙታን ጥርቅም። ወያኔ ጉድጓድ መግባት ያለበት ድርጅት ነው። በሚሊዪን የሚቆጠሩ ሰቆቃዎችን ያደረሰና በማድረስ ላይ ያለ ድርጅት ምህረት ሊደረግለት አይገባም። እኔን የሚያናድኝ የወያኔ የጭፍን ደጋፊዎች የትግራይ ተወላጆች ናቸው። እውነቱንና ፕሮፓጋንዳውን እንዴት ሰው መለየት ይሳነዋል? በወያኔ ስንት የትግራይ ልጆች ነው የተገደሉት? አሁንስ በዚህ ግጭት የሚረግፉት? ደብረጽዪን አሁንም ጥሉ ከአማራ ህዝብ ጋር ነው። ልብ ይሰብራል። አማራ የትግራይ ህዝብ ላይ ምን በደል ፈጸመ? ወያኔ ግን ለዘመናት የአማራን ህዝብ ሲያተራምስና አምካኝ መርፌ ሁሉ ሲወጋ የኖረ ለመሆኑ አሊ የማይባል መረጃ አለ። ያው ግን የሽፍጠት ፓለቲካ ጠላትህ መጣ፤ ተወረርክ፤ ተያዝክ፤ እናትህ ሚስትህ እህትህ ልትደፈር ነው በማለት ነው ሰውን ወደ እሳት የሚማግደው። ዶ/ር አብይ የውጭ ሃይሎች ከወያኔ ጋር ሆነው እየተዋጉ ነው እንዳለው ሁሉ አሁን ደግሞ የወያኔ ጭፍን መሪ የውጭ ሰዎች ገብተው እየተዋጉን ነው በማለት አላዝኗል። በሁለቱም ጎን ግን የቀረበልን መረጃ የለም። ይህ ደግሞ እንደተባለው የጦርነትን ቀዳሚ ሰለባ እውነት ራሷ መሆኗን ያሳየናል።
    አርቲ ቡርቲውን የሃበሻ ፓለቲካ ወደ ኋላ ጥሎ ነገሮችን በረጋ መንገድ ለተመለከተ የዓለም መሳቂያ መሆናችን ያሳያል። እኛው የቆመን ሁሉ አፍርሰን፤ አቃጥለን አሁን ተመልሰን ተራብን፤ በሽታ ገባ፤ እንዲህና እንዲያ ሆንን ብንል ሰሚ የለም። የሰሙን ከመሰለንም እኛኑ የሚያናኩር ነገር ቋጥረው እንጂ በቅንነት ሃገርን አይረድም። ይህ አሁን በድህረ ገጾች ላይ የምናየውና የምንሰማው የቀድሞ የአውሮፓና የአሜሪካ ዲፕሎማቶች በዶላር ከተገዙ ሃገር ሽያጭ ሃበሾች ጋር በመሆን የሚሸርቡት ሴራ ከአንድ ምንጭ መቀዳቱን ያሳያል። ያስገርማል። It is rehearsed play. በተናጠልም ሆነ በህብረት የሚሰጧቸውን ቃለ መጠይቆች፤ ማስጠንቀቂያዎች፤ የድጋፍ ሃሳቦች ላጤነ ከአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ፓሊሲ የተቀዳ ሁሉም የፈረሙበት ለመሆኑ አያጠራጥርም። እነዚህ ናቸው ሰለ ሰላምና ዲሞክራሲ ዓለም ሊያስተምሩ የሚሹት። የራሷ ሲያርባት የሰው ታማስላለች እንዲሉ። ዛሬ በአውሮፓ፤ በአሜሪካ በራችው ድረስ የተኮለኮሉት ጥገኝነት ጥያቄዎች የመጡት ነጩ ዓለም ተባብረው ከደረመሷቸው ሃገሮች ነው። ገና ብዙ ይነጉዳል። ግን ያልታበሱ እንባዎች አይዞሽ አዞህ ብሎ የሚያጽናናቸው ወገን ሳያገኙ በተስፋ መቁረጥ ራሳቸውን ሲያጠፉ ምንኛ ያሳዝናል። ዘሩን ጎሳውን፤ ቋንቋውንና ሃይማኖቱን ወግድልኝ ብሎ በሰውኛ ልብ ላሰበ እየየው ያሰኛል። ግን ሁሉ አልቃሽና አስለቃሽ በሆነበት የሃበሻ ምድር መሰማማት የት አለና። ግን መቼ ይሆን መገዳደላችን የሚያበቃው? ጊዜ ይመጣ ይሆን? አላውቅም።
    እውቁ አሜሪካዊ የህዋ ተመራማሪ Carl Sagan ከዘመናት በፊት “Pale Blue Dot” እንዲህ ይለናል። ፈልጋችሁ ራሱ ሲናገር ብትሰሙት የበለጠ የሃሳቡ ጥልቀት ይገባቹሃል። ያም ሆነ ይህ ቅንጫቢ ሃሳቡ እንሆ።
    The Earth is a very small stage in a vast cosmic arena. Think of the rivers of blood spilled by all those generals and emperors so that, in glory and triumph, they could become the momentary masters of a fraction of a dot. Think of the endless cruelties visited by the inhabitants of one corner of this pixel on the scarcely distinguishable inhabitants of some other corner, how frequent their misunderstandings, how eager they are to kill one another, how fervent their hatreds.
    አምናለሁ በዚህም በዚያም ለሰው ልጅ ህሊናው ይመሰክርለታል። ግን ምንም ያልሰራ ሰው ዝቅዝቆ የሚሰቅል፤ ይህ መሬት ላይ ያንቺ ልጅ አይወለድም በማለት የነፍሰጡር ሴት ሆድ ቀዶ ልጅ የሚያወጣ፤ እናቱን፤ እህቱን ወንድሙን አባቱን ገድሎ የሚፎክር፤ ያለምንም ሃፍረት ሴት ልጆችን በደቦ የሚደፍር የአውሬ ስብስብና መሪዎችሁ በመዘዙት ሰይፍ ይወድቃሉ። በታሪክ ያየነው ያን ነው። እስከዚያው ግን በዚህም በዚያም መገዳደሉ ይቀጥላል። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule