• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ቀጣይዋ ትግራይ = “ትግ-ሶቶ”

December 5, 2021 11:14 am by Editor 7 Comments

መውጫው እንደመግቢያው ቀላል አልሆነም። በትግሬ ልሂቃን እብደት፣ ማኅበራዊ መሠረታቸው ላይ የእሳት ቀለበት ሰርተዋል። በእያንዳንዱ የትግሬ ጎጆ የመከራ ዜና፣ የመርዶ መልዕክት ገብቷል። በጦርነቱ እና ከጦርነቱ ጋር ተያያዥ በሆኑ ምክንያቶች አራት መቶ ስድሳ ሺህ ትግሬዎች ረግፈዋል። ይህን እኔ ሳልሆን ያልኩት የሳልሳዊ ወያኔ (ሳወት) መሪ ተስፋ ኪሮስ ሳህለ ነው። ያለምንም ጥርጥር ጦርነቱ በሕዝባቸው ላይ የትውልድ ክፍተት ፈጥሯል። ምናልባትም አንድ ወንድ አምስት ሴቶችን እንዲያገባ በልዩ ሁኔታ የቤተሰብ ሕጉ ካልተሻሻለላቸው በስተቀር የትውልድ ክፍተቱን በቀላሉ አይሞሉትም። 

ወያኔ ራሱ በለኮሰው እሳት “እወክለዋለሁ” የሚለውን ሕዝብ የእሳት ቀለበት ውስጥ አስገብቶታል። ከዚህ ጦርነት የሚተርፍ ቢኖር እንኳ በርካታ የትግራይ ከተሞችና መንደሮች የአዛውንት እና የሕጻናት ስብስብ ከመሆን ውጭ አማካኝ ዕድሜ ላይ የሚገኝና አልሚ ጉልበት ያለው ወጣት ቁጥሩ አነስተኛ መሆኑ አይቀርም። ወጣቱ በጦርነት እየረገፈ ነው፤ ከጦርነት ቢያመልጥ እንኳ በስደት ከቀየው መራቁ ተገማች ነው።

ወያኔ በቀደመ የአገዛዝ፣ የዘረፋ እና የጨፍጫፊነት ባሕሪውና የዚህ ማኅበራዊ መሠረት በመሆኑ የተነሳ ትግሬ በመላ የኢትዮጵያ ሕዝብ ተይዞበት ከነበረው ቂም በከፋ ሁኔታ የጥቅምት 24ቱ ክህደቱና አሁናዊ የሽብር፣ የጦር ወረራ፣ ጭፍጨፋ፣ ውድመትና የዘረፋ ተግባራቱ የተነሳ የኢትዮጵያን ሕዝብ አስቆጥቷል። አንቅሮ ያልተፋው ብሔር የለም። ሀገር ነው የተባበረ ክንዱን ያስወነጨፈው፤ በሰማይና በምድር በሚዘንበው እሳት ጠላት እየረገፈ ነው። የአማራ እና የአፋር ተራሮችም በጥንብ አንሳ ተሞልተዋል (በጎልጉል የተጨመረ፤ ሰሞኑን ጠቅላዩ በአንድ ግምባር ሲናገሩ ይሰማ የነበረውን የቁራ ድምፅ ማስታወሱ በቂ ነው)።

በዚህ ጦርነት ኢትዮጵያ ማሸነፏ እርግጥ ነበር፤ እየሆነ ያለውም ይኼው ነው። የነገው የትግራይ ሁኔታ ግን የተለየ ገጽታ መላበሱ አይቀርም። ዙሪያውን በእሳት ካብ የታጠረ ማኅበረሰብ በምንም አይነት ተዓምር ጤናማ የገበያ ትሥሥር፣ የመሠረተ-ልማት ዕድል እና የማኅበራዊ አገልግሎት አያገኝም። ተከዜን መሻገር ቀርቶ አሳ ማጥመድ መቻልም ዕድለኝነት ነው።

ጦርነቱን ተከትሎ በደረሰበት መከራ እና ማኅበረሰባዊ ውድቀት (societal collapse) የተነሳ በቀጣይ የቱንም ያሕል ቢደክም የተረጋጋ ማኀበረሰብ መፍጠር አይችልም። ወንዱ የሚበረግግ ህሊና (paranoid) ሴቷ ደግሞ በምግብ መቀንጨር ማህጸኗ የተጎዳ መሆኗ አይቀርም። በዚህ መሀል የሚወለዱ ልጆች ከሌላው ኢትዮጵያዊ ህፃናት ጋር የማይወዳደሩ ጤናቸው የታወከ ይሆናል።

ከዚህ መዓት የሚያመልጥ ቢኖር እንኳ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ጋር የቀደመው ማኅበራዊ ወረቱ ሊቀጥል አይችልም። በተለይም ከጎረቤቶቹ አማራ እና አፋር ጋር ደም የተቃባ በመሆኑ፣ አልፎም ከኤርትራ ጋር ከትውልድ ትውልድ የሚሸጋገር ቅራኔ ውስጥ የገባ መሆኑ በደሴት ውስጥ የሚኖር ተነጣይ የዱር እንስሳት ዕጣ ያጋጥመዋል። የደቀቀ ኢኮኖሚ ታቅፎ በድንጋያማ መሬት ትርፍ ማምረት የተሳነው ተመጽዋች ይሆናል። በዚያ ክልል (በትግ-ሴቶ) ከ49 ኪሎ በላይ የሆነ ሰው ማየት ብርቅ ይሆናል።

በሁሉም መመዘኛዎች ከታየ ትግራይ በቀጣይ ጊዜ የጨነገፈ ትውልድ ይዛ መንገታገቷ ከሀቅ የራቀ አይደለም። በትግራይ ልሂቃን እብደት የተነሳ፣ በቀጣይ እያንዳንዱን ዋይታና የመከራ ዘመን በነፍስ-ወከፍ የሚኖረው የትግሬ ሕዝብ “የጎረቤት ያለህ” በሚል ሲንከራተት መኖሩ አይቀሬ ነው። ወያኔ በክህደት ባህሪው የተነሳ ትላንት የድርጅት አጋርነት ውድቀት ታሪኩ “የአጋር ያለህ” አሰኘው፤ ዛሬ የሁኔታዎች ድምር ውጤት የገዛ ሕዝቡን “የጎረቤት ያለህ” እያሰኘው ነው።

ከትላንት የቀጠለው የዛሬ ሰይጣናዊ ድርጊታቸው በውል ሕዝቡን የተጠላ ነገድ እንዲሆን አድርጎታል። ይህ ጦርነት ደግሞ ራቁታቸውን አስቀርቷቸዋል። ትግሬ እንደሕዝብ በኢትዮጵያ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ቦታዎችን ማጣቱ ርግጥ ሁኗል። ከእንግዲህ እንኳንስ ሀገር፣ ዕድር እና እቁብ የመምራት ዕድል አያገኙም። የዳር ሀገር መናኛ ሕዝብ የመሆን ጉዞውንም ከወዲሁ ጀምሯል። ለዚህ ተጠያቂው የትግሬ ልሂቅ እንጅ ኢትዮጵያዊያን አይደሉም።

የስንብት ሃረካት…

አሁን እየሆነ ያለው አንድ የነሱ ሰው ከወራት በፊት “ሁሉም ትግሬ ጦርነት ውስጥ ነው” እንዳለው ነው። ወይ ሞኞ! ለዚህ አፀፋው “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሀገሩን ለመታደግ ጦርነት ውስጥ ነው”። በየትም ቦታ በምንም ሁኔታ ያሉ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች የእናት ሀገራቸው ዘብ ሆነው ተሰልፈዋል። ከትግሬ ወራሪ ጋር የሚጠፋፋ እንጅ የሚስተሃቀር ፍላጎት የላቸውም። በነገዋ ኢትዮጵያ አንድ የትግሬ ለማኝ ከመቀሌ ተነስቶ ለልመና በመላ ኢትዮጵያዊያን በር ቢዞር አኮፋዳውን ስለመሙላቱ እጅጉን እጠራጠራለሁ!!

የሆነው ሆኖ ጠላት በጦርነቱ እንደማያሸንፍ ያውቀዋል። ፍላጎቱ (የኮሪደሩን ቅዥት እርሳውና) በቻለው መጠን አማራንና አፋርን ማጥፋት፣ ከሆነለት በኢትዮጵያ የውጭ ጠላቶች ተንጠልጥሎ ሀገር ማፍረስ ነው። “አቻ መውጣት” ነው። ጠላት ትግራይ ተስፋ ቢስ ነች የሚል ግምገማ ከያዘ ቆይቷል፣ አሁን የሞት ሽረቱን “አቻ ለመሆን” ነው ገቢረ-ጉንዳን የሆነው። ግና የዛለ ክንድ ያለው በመሆኑ ዕድሜው የጉንዳን እግር ያህል እንኳ አይረዝምም። በአጠረ ጊዜ ቃታ የመሳብ አቅም ጨርሶ አይኖረውም። ያኔ ከዛሬ በከፋ ለነገ ማኅበራዊ ውርደት ቋሚ የሕይወት ምዕራፉ ይሆናል። ሂሳቡም እጥፍ እንደሚወራረድ አትርሳው!!

የትግሬ ልሂቅ ሆይ! የመረጥከውን መኖር ተፈጥሯዊ መብትህ ነው። ተፈጥሮ ግን ሕግ አላት፤ የእጅህን ታገኛለህ! በመከራም ሆነ በዋይታ ውስጥ ስትኖር ያንተ ብቻ ሳይሆን የነገ የትውልድ ዕጣ ፈንታህን በጨፈገገ የህይወት ምዕራፍ ውስጥ መመልከትህ አይቀሬ ነው። ይህን ለማረም ደግሞ ጊዜው ረፍዷል!! ምናልባትም ማረም የሚችሉት ሲበደሉ የኖሩት ቋንቋና ኃይማኖት የማይለያያቸው መላ ኢትዮጵያዊያን ናቸው። ኢትዮጵያዊያን ደግሞ የህልውና ዘመቻ ላይ ናቸው። ከሆነልህ ባለህበት እጅ ስጥ! እምቢ ካልክ የሲዖል ትኬት ይቆረጥልሃል።

ዘላለማዊ ክብርና ሞገስ ኢትዮጵያን ብለው የማይተካ ሕይወታቸውን ለገበሩ የቁርጥ ቀን ልጆች!

ሙሉአለም ገ/መድህን (ርዕስ፤ ሲያንስህ ነው!!)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Opinions Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tigsotho, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Kidane Alemayehu says

    December 5, 2021 06:21 pm at 6:21 pm

    ይህንን መልእክት የማቀርበው፤ በጥያቄ ሥልት ነው፡፡ በአሁኑ ሰዓት፡፡
    እንደ አጋጣሚ፤ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አማካኝነት፤ በለሶቶ፤ የፖስታ፤ ቴሌኮሙኒኬሽንና የሲቪል አቭዬሽን ዋና ዲሬክተር፤ ከዚያ በኋላ ደግሞ፤ የለሶቶ የሥራ ሚኒስቴር ዋና ተጠሪ (Permanent Secretary) በመሆን አገልግዬ ነበር፡፡ ዝርዝሩን ለማወቅ፤ “My Journey with the United Nations and Quest for the Horn of Africa’s Unity and Justice for Ethiopia” የተሰኘውን መጽሐፌን መመልከት ይቻላል፡፡

    ለሶቶ በስፋት ትንሽ ብትሆንም፤ ራሷን ከእንግሊዞች ቅኝ ግዛት ማዳን የቻለች፤ ለሰላምና ለልማት በመታገል ብርቱ የሆነች ሐገር ናት፡፡ ሌላው፤ ለሶቶን፤ በተለይ የሚያስመሰግናት፤ ከደቡብ አፍሪካ በየዓመቱ $50 ሚሊዮን እያስከፈለች፤ ባላት ከፍተኛ የውሀ ህብት መብቷ እየተጠቀመች ለመሆን መቻሏ ነው፡፡

    ታዲያ፤ “ትግ_ሶቶ” ማለት ምን ለመጠቆም ይሆን? በተለይ “ሞኝ ቤት ፊት ሞፈር ይቆረጣል” ከሚያሰኝ ሰፈር!

    ኪዳኔ ዓለማየሁ፡፡

    Reply
    • Editor says

      December 7, 2021 11:13 am at 11:13 am

      Kidane Alemayehu

      በጽሁፉ ላይ በግልጽ ተቀምጧል፤ ይህቺን አንቀጽ ካላነበቧት ድጋሚ ተመልከቷት

      “ከዚህ መዓት የሚያመልጥ ቢኖር እንኳ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ጋር የቀደመው ማኅበራዊ ወረቱ ሊቀጥል አይችልም። በተለይም ከጎረቤቶቹ አማራ እና አፋር ጋር ደም የተቃባ በመሆኑ፣ አልፎም ከኤርትራ ጋር ከትውልድ ትውልድ የሚሸጋገር ቅራኔ ውስጥ የገባ መሆኑ በደሴት ውስጥ የሚኖር ተነጣይ የዱር እንስሳት ዕጣ ያጋጥመዋል። የደቀቀ ኢኮኖሚ ታቅፎ በድንጋያማ መሬት ትርፍ ማምረት የተሳነው ተመጽዋች ይሆናል። በዚያ ክልል (በትግ-ሴቶ) ከ49 ኪሎ በላይ የሆነ ሰው ማየት ብርቅ ይሆናል።”

      አርታኢ

      Reply
  2. Yoseph Awoke Awoke says

    December 7, 2021 08:04 am at 8:04 am

    መቼም በሕይወቴ ሙሉ እንደ ዘንድሮ አዝኜ አላውቅም በተለይ የተማረኩትን ትናንሽ ልጆች አይ ያስለቅሳል ግን ሕወአት በእውነት ድርጅት ነው? ይሄን ሁሉ አፀያፊ የሆነ ነገር ለምን በምስኪን ወንድሞቹና እህቶቹ ላይ ማድረግ ፈለገውን? እንደው የነጮቹ ትዕዛዝስ በገንዘብ አደረገው ቢባልም የሕወአት ሰዎችን ዓለምን የሚያናጋ ገንዘብ አላቸው አይደለም እንዴ? ወይስ እንደሚባለው የሠይጣን ናቸው በዚህም አለ በዚያ የትግራይ ሕዝብ መከራ አላበቃም አለ ከዘመን ዘመን የአሁኑ ግን በክፍለ ዘመኑ መጨረሻ ላይም የሚያበቃም አይመስልም።

    Reply
  3. Kidane Alemayehu says

    December 7, 2021 07:44 pm at 7:44 pm

    ውድ አርታኢ (ቦርኬና)፤

    ሰላም፡፡ የጠቀሱትን “አንቀጽ” ተመለከትኩት፡፡ ለሶቶ የውሀ ብቻ ሳይሆን የዓልማዝም የታታሪ ሕዝብ እሴት ያላት ሐገር በመሆኗ፤ በጽሑፉ በቀረበው ዓይነት አስተሳሰብ ልትዘቅጥ አይገባትም፡፡

    Reply
    • Editor says

      December 12, 2021 08:25 pm at 8:25 pm

      Kidane Alemayehu

      የጽሁፉ ዐውድ ሌሶቶን ከማዝቀጥ አኳያ ሳይሆን ትግራይን በካርታ ደረጃ በሌሶቶ ቅርጽ ከማስቀመጥ ነው። ይህ ደግሞ ጽሁፉ በግልጽ የተቀመጠ ሃቅ ነው።

      ተጨማሪ ጥያቄ ወይም ተቃውሞ ካለዎት በሞጋች ጽሁፍ (rebuttal or rejoinder) መልኩ ቢያቀርቡ ለአንባቢ እንዲደርስ እናደርጋለን። ወይም ጸሐፊውን ለማግኘት ከፈለጉ ስሙ ላይ ባለው ሊንክ ተጠቅመው በፌስቡክ ሃሳብዎን ሊገልጹለት ይችላሉ።

      በዚህ አጋጣሚ “ቦርኬና” በማለት የጻፉትን ቃል ትርጉም እንዲገልጹልን በአክብሮት እንጠይቃለን።

      አርታኢ

      Reply
  4. Kidane Alemayehu says

    December 15, 2021 10:37 am at 10:37 am

    ብሩካን፤

    “ቦርኬና” ያልኩት በስሕተት ነው፡፡ ይቅርታ፡፡

    Reply
    • Editor says

      December 15, 2021 05:00 pm at 5:00 pm

      እኛም አዲስ ቃል ስለሆነብን ለመማር ብለን ነው የጠየቅነው፤
      ክብረት ይስጥልን

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule