• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ቀጣይዋ ትግራይ = “ትግ-ሶቶ”

December 5, 2021 11:14 am by Editor 7 Comments

መውጫው እንደመግቢያው ቀላል አልሆነም። በትግሬ ልሂቃን እብደት፣ ማኅበራዊ መሠረታቸው ላይ የእሳት ቀለበት ሰርተዋል። በእያንዳንዱ የትግሬ ጎጆ የመከራ ዜና፣ የመርዶ መልዕክት ገብቷል። በጦርነቱ እና ከጦርነቱ ጋር ተያያዥ በሆኑ ምክንያቶች አራት መቶ ስድሳ ሺህ ትግሬዎች ረግፈዋል። ይህን እኔ ሳልሆን ያልኩት የሳልሳዊ ወያኔ (ሳወት) መሪ ተስፋ ኪሮስ ሳህለ ነው። ያለምንም ጥርጥር ጦርነቱ በሕዝባቸው ላይ የትውልድ ክፍተት ፈጥሯል። ምናልባትም አንድ ወንድ አምስት ሴቶችን እንዲያገባ በልዩ ሁኔታ የቤተሰብ ሕጉ ካልተሻሻለላቸው በስተቀር የትውልድ ክፍተቱን በቀላሉ አይሞሉትም። 

ወያኔ ራሱ በለኮሰው እሳት “እወክለዋለሁ” የሚለውን ሕዝብ የእሳት ቀለበት ውስጥ አስገብቶታል። ከዚህ ጦርነት የሚተርፍ ቢኖር እንኳ በርካታ የትግራይ ከተሞችና መንደሮች የአዛውንት እና የሕጻናት ስብስብ ከመሆን ውጭ አማካኝ ዕድሜ ላይ የሚገኝና አልሚ ጉልበት ያለው ወጣት ቁጥሩ አነስተኛ መሆኑ አይቀርም። ወጣቱ በጦርነት እየረገፈ ነው፤ ከጦርነት ቢያመልጥ እንኳ በስደት ከቀየው መራቁ ተገማች ነው።

ወያኔ በቀደመ የአገዛዝ፣ የዘረፋ እና የጨፍጫፊነት ባሕሪውና የዚህ ማኅበራዊ መሠረት በመሆኑ የተነሳ ትግሬ በመላ የኢትዮጵያ ሕዝብ ተይዞበት ከነበረው ቂም በከፋ ሁኔታ የጥቅምት 24ቱ ክህደቱና አሁናዊ የሽብር፣ የጦር ወረራ፣ ጭፍጨፋ፣ ውድመትና የዘረፋ ተግባራቱ የተነሳ የኢትዮጵያን ሕዝብ አስቆጥቷል። አንቅሮ ያልተፋው ብሔር የለም። ሀገር ነው የተባበረ ክንዱን ያስወነጨፈው፤ በሰማይና በምድር በሚዘንበው እሳት ጠላት እየረገፈ ነው። የአማራ እና የአፋር ተራሮችም በጥንብ አንሳ ተሞልተዋል (በጎልጉል የተጨመረ፤ ሰሞኑን ጠቅላዩ በአንድ ግምባር ሲናገሩ ይሰማ የነበረውን የቁራ ድምፅ ማስታወሱ በቂ ነው)።

በዚህ ጦርነት ኢትዮጵያ ማሸነፏ እርግጥ ነበር፤ እየሆነ ያለውም ይኼው ነው። የነገው የትግራይ ሁኔታ ግን የተለየ ገጽታ መላበሱ አይቀርም። ዙሪያውን በእሳት ካብ የታጠረ ማኅበረሰብ በምንም አይነት ተዓምር ጤናማ የገበያ ትሥሥር፣ የመሠረተ-ልማት ዕድል እና የማኅበራዊ አገልግሎት አያገኝም። ተከዜን መሻገር ቀርቶ አሳ ማጥመድ መቻልም ዕድለኝነት ነው።

ጦርነቱን ተከትሎ በደረሰበት መከራ እና ማኅበረሰባዊ ውድቀት (societal collapse) የተነሳ በቀጣይ የቱንም ያሕል ቢደክም የተረጋጋ ማኀበረሰብ መፍጠር አይችልም። ወንዱ የሚበረግግ ህሊና (paranoid) ሴቷ ደግሞ በምግብ መቀንጨር ማህጸኗ የተጎዳ መሆኗ አይቀርም። በዚህ መሀል የሚወለዱ ልጆች ከሌላው ኢትዮጵያዊ ህፃናት ጋር የማይወዳደሩ ጤናቸው የታወከ ይሆናል።

ከዚህ መዓት የሚያመልጥ ቢኖር እንኳ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ጋር የቀደመው ማኅበራዊ ወረቱ ሊቀጥል አይችልም። በተለይም ከጎረቤቶቹ አማራ እና አፋር ጋር ደም የተቃባ በመሆኑ፣ አልፎም ከኤርትራ ጋር ከትውልድ ትውልድ የሚሸጋገር ቅራኔ ውስጥ የገባ መሆኑ በደሴት ውስጥ የሚኖር ተነጣይ የዱር እንስሳት ዕጣ ያጋጥመዋል። የደቀቀ ኢኮኖሚ ታቅፎ በድንጋያማ መሬት ትርፍ ማምረት የተሳነው ተመጽዋች ይሆናል። በዚያ ክልል (በትግ-ሴቶ) ከ49 ኪሎ በላይ የሆነ ሰው ማየት ብርቅ ይሆናል።

በሁሉም መመዘኛዎች ከታየ ትግራይ በቀጣይ ጊዜ የጨነገፈ ትውልድ ይዛ መንገታገቷ ከሀቅ የራቀ አይደለም። በትግራይ ልሂቃን እብደት የተነሳ፣ በቀጣይ እያንዳንዱን ዋይታና የመከራ ዘመን በነፍስ-ወከፍ የሚኖረው የትግሬ ሕዝብ “የጎረቤት ያለህ” በሚል ሲንከራተት መኖሩ አይቀሬ ነው። ወያኔ በክህደት ባህሪው የተነሳ ትላንት የድርጅት አጋርነት ውድቀት ታሪኩ “የአጋር ያለህ” አሰኘው፤ ዛሬ የሁኔታዎች ድምር ውጤት የገዛ ሕዝቡን “የጎረቤት ያለህ” እያሰኘው ነው።

ከትላንት የቀጠለው የዛሬ ሰይጣናዊ ድርጊታቸው በውል ሕዝቡን የተጠላ ነገድ እንዲሆን አድርጎታል። ይህ ጦርነት ደግሞ ራቁታቸውን አስቀርቷቸዋል። ትግሬ እንደሕዝብ በኢትዮጵያ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ቦታዎችን ማጣቱ ርግጥ ሁኗል። ከእንግዲህ እንኳንስ ሀገር፣ ዕድር እና እቁብ የመምራት ዕድል አያገኙም። የዳር ሀገር መናኛ ሕዝብ የመሆን ጉዞውንም ከወዲሁ ጀምሯል። ለዚህ ተጠያቂው የትግሬ ልሂቅ እንጅ ኢትዮጵያዊያን አይደሉም።

የስንብት ሃረካት…

አሁን እየሆነ ያለው አንድ የነሱ ሰው ከወራት በፊት “ሁሉም ትግሬ ጦርነት ውስጥ ነው” እንዳለው ነው። ወይ ሞኞ! ለዚህ አፀፋው “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሀገሩን ለመታደግ ጦርነት ውስጥ ነው”። በየትም ቦታ በምንም ሁኔታ ያሉ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች የእናት ሀገራቸው ዘብ ሆነው ተሰልፈዋል። ከትግሬ ወራሪ ጋር የሚጠፋፋ እንጅ የሚስተሃቀር ፍላጎት የላቸውም። በነገዋ ኢትዮጵያ አንድ የትግሬ ለማኝ ከመቀሌ ተነስቶ ለልመና በመላ ኢትዮጵያዊያን በር ቢዞር አኮፋዳውን ስለመሙላቱ እጅጉን እጠራጠራለሁ!!

የሆነው ሆኖ ጠላት በጦርነቱ እንደማያሸንፍ ያውቀዋል። ፍላጎቱ (የኮሪደሩን ቅዥት እርሳውና) በቻለው መጠን አማራንና አፋርን ማጥፋት፣ ከሆነለት በኢትዮጵያ የውጭ ጠላቶች ተንጠልጥሎ ሀገር ማፍረስ ነው። “አቻ መውጣት” ነው። ጠላት ትግራይ ተስፋ ቢስ ነች የሚል ግምገማ ከያዘ ቆይቷል፣ አሁን የሞት ሽረቱን “አቻ ለመሆን” ነው ገቢረ-ጉንዳን የሆነው። ግና የዛለ ክንድ ያለው በመሆኑ ዕድሜው የጉንዳን እግር ያህል እንኳ አይረዝምም። በአጠረ ጊዜ ቃታ የመሳብ አቅም ጨርሶ አይኖረውም። ያኔ ከዛሬ በከፋ ለነገ ማኅበራዊ ውርደት ቋሚ የሕይወት ምዕራፉ ይሆናል። ሂሳቡም እጥፍ እንደሚወራረድ አትርሳው!!

የትግሬ ልሂቅ ሆይ! የመረጥከውን መኖር ተፈጥሯዊ መብትህ ነው። ተፈጥሮ ግን ሕግ አላት፤ የእጅህን ታገኛለህ! በመከራም ሆነ በዋይታ ውስጥ ስትኖር ያንተ ብቻ ሳይሆን የነገ የትውልድ ዕጣ ፈንታህን በጨፈገገ የህይወት ምዕራፍ ውስጥ መመልከትህ አይቀሬ ነው። ይህን ለማረም ደግሞ ጊዜው ረፍዷል!! ምናልባትም ማረም የሚችሉት ሲበደሉ የኖሩት ቋንቋና ኃይማኖት የማይለያያቸው መላ ኢትዮጵያዊያን ናቸው። ኢትዮጵያዊያን ደግሞ የህልውና ዘመቻ ላይ ናቸው። ከሆነልህ ባለህበት እጅ ስጥ! እምቢ ካልክ የሲዖል ትኬት ይቆረጥልሃል።

ዘላለማዊ ክብርና ሞገስ ኢትዮጵያን ብለው የማይተካ ሕይወታቸውን ለገበሩ የቁርጥ ቀን ልጆች!

ሙሉአለም ገ/መድህን (ርዕስ፤ ሲያንስህ ነው!!)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Opinions Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tigsotho, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Kidane Alemayehu says

    December 5, 2021 06:21 pm at 6:21 pm

    ይህንን መልእክት የማቀርበው፤ በጥያቄ ሥልት ነው፡፡ በአሁኑ ሰዓት፡፡
    እንደ አጋጣሚ፤ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አማካኝነት፤ በለሶቶ፤ የፖስታ፤ ቴሌኮሙኒኬሽንና የሲቪል አቭዬሽን ዋና ዲሬክተር፤ ከዚያ በኋላ ደግሞ፤ የለሶቶ የሥራ ሚኒስቴር ዋና ተጠሪ (Permanent Secretary) በመሆን አገልግዬ ነበር፡፡ ዝርዝሩን ለማወቅ፤ “My Journey with the United Nations and Quest for the Horn of Africa’s Unity and Justice for Ethiopia” የተሰኘውን መጽሐፌን መመልከት ይቻላል፡፡

    ለሶቶ በስፋት ትንሽ ብትሆንም፤ ራሷን ከእንግሊዞች ቅኝ ግዛት ማዳን የቻለች፤ ለሰላምና ለልማት በመታገል ብርቱ የሆነች ሐገር ናት፡፡ ሌላው፤ ለሶቶን፤ በተለይ የሚያስመሰግናት፤ ከደቡብ አፍሪካ በየዓመቱ $50 ሚሊዮን እያስከፈለች፤ ባላት ከፍተኛ የውሀ ህብት መብቷ እየተጠቀመች ለመሆን መቻሏ ነው፡፡

    ታዲያ፤ “ትግ_ሶቶ” ማለት ምን ለመጠቆም ይሆን? በተለይ “ሞኝ ቤት ፊት ሞፈር ይቆረጣል” ከሚያሰኝ ሰፈር!

    ኪዳኔ ዓለማየሁ፡፡

    Reply
    • Editor says

      December 7, 2021 11:13 am at 11:13 am

      Kidane Alemayehu

      በጽሁፉ ላይ በግልጽ ተቀምጧል፤ ይህቺን አንቀጽ ካላነበቧት ድጋሚ ተመልከቷት

      “ከዚህ መዓት የሚያመልጥ ቢኖር እንኳ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ጋር የቀደመው ማኅበራዊ ወረቱ ሊቀጥል አይችልም። በተለይም ከጎረቤቶቹ አማራ እና አፋር ጋር ደም የተቃባ በመሆኑ፣ አልፎም ከኤርትራ ጋር ከትውልድ ትውልድ የሚሸጋገር ቅራኔ ውስጥ የገባ መሆኑ በደሴት ውስጥ የሚኖር ተነጣይ የዱር እንስሳት ዕጣ ያጋጥመዋል። የደቀቀ ኢኮኖሚ ታቅፎ በድንጋያማ መሬት ትርፍ ማምረት የተሳነው ተመጽዋች ይሆናል። በዚያ ክልል (በትግ-ሴቶ) ከ49 ኪሎ በላይ የሆነ ሰው ማየት ብርቅ ይሆናል።”

      አርታኢ

      Reply
  2. Yoseph Awoke Awoke says

    December 7, 2021 08:04 am at 8:04 am

    መቼም በሕይወቴ ሙሉ እንደ ዘንድሮ አዝኜ አላውቅም በተለይ የተማረኩትን ትናንሽ ልጆች አይ ያስለቅሳል ግን ሕወአት በእውነት ድርጅት ነው? ይሄን ሁሉ አፀያፊ የሆነ ነገር ለምን በምስኪን ወንድሞቹና እህቶቹ ላይ ማድረግ ፈለገውን? እንደው የነጮቹ ትዕዛዝስ በገንዘብ አደረገው ቢባልም የሕወአት ሰዎችን ዓለምን የሚያናጋ ገንዘብ አላቸው አይደለም እንዴ? ወይስ እንደሚባለው የሠይጣን ናቸው በዚህም አለ በዚያ የትግራይ ሕዝብ መከራ አላበቃም አለ ከዘመን ዘመን የአሁኑ ግን በክፍለ ዘመኑ መጨረሻ ላይም የሚያበቃም አይመስልም።

    Reply
  3. Kidane Alemayehu says

    December 7, 2021 07:44 pm at 7:44 pm

    ውድ አርታኢ (ቦርኬና)፤

    ሰላም፡፡ የጠቀሱትን “አንቀጽ” ተመለከትኩት፡፡ ለሶቶ የውሀ ብቻ ሳይሆን የዓልማዝም የታታሪ ሕዝብ እሴት ያላት ሐገር በመሆኗ፤ በጽሑፉ በቀረበው ዓይነት አስተሳሰብ ልትዘቅጥ አይገባትም፡፡

    Reply
    • Editor says

      December 12, 2021 08:25 pm at 8:25 pm

      Kidane Alemayehu

      የጽሁፉ ዐውድ ሌሶቶን ከማዝቀጥ አኳያ ሳይሆን ትግራይን በካርታ ደረጃ በሌሶቶ ቅርጽ ከማስቀመጥ ነው። ይህ ደግሞ ጽሁፉ በግልጽ የተቀመጠ ሃቅ ነው።

      ተጨማሪ ጥያቄ ወይም ተቃውሞ ካለዎት በሞጋች ጽሁፍ (rebuttal or rejoinder) መልኩ ቢያቀርቡ ለአንባቢ እንዲደርስ እናደርጋለን። ወይም ጸሐፊውን ለማግኘት ከፈለጉ ስሙ ላይ ባለው ሊንክ ተጠቅመው በፌስቡክ ሃሳብዎን ሊገልጹለት ይችላሉ።

      በዚህ አጋጣሚ “ቦርኬና” በማለት የጻፉትን ቃል ትርጉም እንዲገልጹልን በአክብሮት እንጠይቃለን።

      አርታኢ

      Reply
  4. Kidane Alemayehu says

    December 15, 2021 10:37 am at 10:37 am

    ብሩካን፤

    “ቦርኬና” ያልኩት በስሕተት ነው፡፡ ይቅርታ፡፡

    Reply
    • Editor says

      December 15, 2021 05:00 pm at 5:00 pm

      እኛም አዲስ ቃል ስለሆነብን ለመማር ብለን ነው የጠየቅነው፤
      ክብረት ይስጥልን

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule