• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዘላቂ ወዳጅ የሌላት አሜሪካ ፊቷን በትህነግ ላይ እያዞረች ነው

January 12, 2022 01:00 pm by Editor Leave a Comment

ትህነግ ብዙ ወጪ ያደረገበት የሎቢ ሥራ ኪሣራ እየገጠመው ነው
አሜሪካ ኢትዮጵያን ወደ አጎዋ ለመመለስ ፍንጭ አሳየች

የኢትዮጵያ መንግሥት ከአሜሪካ የንግድ ልዑክ የተነሱበትን ቅሬታዎች በተመለከተ ተጨማሪ “አዎንታዊና ገንቢ” ዕርምጃዎችን የሚወስድ ከሆነ፣ ኢትዮጵያ ከተጠቃሚነት የተሰረዘችበትን የአሜሪካ መንግሥት ከቀረጥ ነፃ የንግድ ዕድል (አጎአ) በተመለከተ የንግግር ሒደት ውስጥ ለመግባት ፈቃደኛ መሆኑ ተገለጸ፡፡

ጥር 2 ቀን 2014 ዓ.ም. ከጋዜጠኞች ጋር በስልክ ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት ስማቸው ያልተጠቀሰ አንድ የአሜሪካ ከፍተኛ ባለሥልጣን፣ ኢትዮጵያ ከአውሮፓውያኑ ጥር ወር 2022 ጀምሮ ከአጎአ ተጠቃሚነት የታገደችው የዕድሉ ተጠቃሚ ለመሆን ከሰብዓዊ መብትና ሌሎች ጉዳዮች ጋር በተያያዘ የተቀመጡ መስፈርቶችን ባለማሟላቷ መሆኑን መናገራቸውን ኋይት ሀውስ በድረ ገጹ አስታውቋል፡፡

ይሁንና የኢትዮጵያ መንግሥት የተነሱበትን ቅሬታዎች አስመልክቶ ተጨማሪ ዕርምጃዎችን የሚወስድ ከሆነ አሜሪካ በየጊዜው ከሚደረገው የአገሮች ሁኔታ ምዘና ውጪ የንግግር ሒደት ውስጥ እንደምትገባ ባለሥልጣኑ ለጋዜጠኞቹ አብራርተዋል፡፡

“ነገር ግን በዚያ መንገድ ለመሄድ በመጀመሪያ ደረጃ ለአጎአ መቋረጥ ምክንያት በሆኑት ጉዳዮች ላይ ጉልህ የሆነ ማሻሻያ ማየት አለብን” ብለዋል፡፡

ባሳለፍነው ሳምንት ታኅሳስ 28 ቀን 2014 ዓ.ም. ከጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ጋር ንግግር ማድረጋቸው የተገለጸው የቀድሞውን የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ጄፍሪ ፌልትማንን የኢትዮጵያ ጉዞ አስመልክቶ በመግለጫው ላይ የተነሳ ሲሆን፣ ከፍተኛ ባለሥልጣኑ ፌልትማን (አምባሳደር) ወደ ኢትዮጵያ ጉዞ ያደረጉት “በኢትዮጵያ መንግሥት ጥያቄ” መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

የቀድሞውን የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ጄፍሪ ፌልትማንን በመተካት የተሾሙት አምባሳደር ዴቪድ ሳተርፊልድ መቼ ወደ ቀጣናው ለመጓዝ እንዳሰቡ ለባለሥልጣኑ ጥያቄ የቀረበላቸው ሲሆን፣ የልዩ መልዕክተኛው የጉብኝት ቀንን በተመለከተ የተወሰነ ቀን አለመኖሩን ገልጸው “ነገር ግን ረዥም [ጊዜ] እንደማይሆን እንጠብቃለን፤” ብለዋል፡፡

ጥር 2 ቀን 2014 ዓ.ም. ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) እና የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በስልክ ንግግር ማድረጋቸው የሚታወስ ሲሆን፣ ሁለቱ መሪዎች ንግግር ያደረጉት በፕሬዚዳንት ባይደን ጥያቄ መሠረት መሆኑን እኚሁ ስማቸው ያልተጠቀሰው ከፍተኛ ባለሥልጣን በመግለጫው ላይ ተናግረዋል፡፡

ሁለቱ መሪዎች ባደረጉት የስልክ ንግግር የኢትዮጵያ መንግሥት በእስር ላይ የነበሩ ፖለቲከኞችን የክስ ሒደት ማቋረጡን አስመልክተው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ (ዶ/ር) ምሥጋና ማቅረባቸው ተገልጿል፡፡ የስልክ ንግግሩን አስመልክቶ ጥር 2 ቀን 2014 ዓ.ም. በፌስቡክ ገጻቸው መልዕክት ያሰፈሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ (ዶ/ር) “በጋራ በመከባበር ላይ የተመሠረተ ገንቢ ተሳትፎ ማድረግ ትብብራችንን ለማጠናከር ትልቅ ጥቅም እንዳለው ሁለታችንም ተስማምተናል” ማለታቸው አይዘነጋም፡፡ (አማኑኤል ይልቃል – ሪፖርተር)

ትህነግ “Tigray Center for Information & Communication” በሚል ስም አሜሪካ አገር በፈጠረው ድርጅት አማካኝነት በፖለቲካው ዘርፍ ድል ለመቀዳጀት በርካታ የውስወሳ (ሎቢ) ሥራዎች ሲያከናውን ቆይቷል። በተለይ “Von Batten Montague York PC” ለሚባለው ወትዋች ድርጅት በርካታ ገንዘብ በመክፈል ከዓላማው አንጻር ውጤቶችን አምጥቷል። በተለይ ኢትዮጵያን ከአጎዋ በማስወጣት ረገድ ወትዋቹ ድርጅት በተከፈለው ልክ ሥራውን ፈጽሟል። ሆኖም አሁን አሜሪካ ኢትዮጵያን ወደ አጎዋ ለመመለስ እንደምትነጋገር መግለጽዋ በርካታ ገንዘብ የፈሰሰበት የትህነግ ውትወታ ቁሻሻ መውረጃ ውስጥ ተጥሎ ተጠርጎ እንደጠፋ መዋዕለ ንዋይ አድርጎታል። ይፈጥራል የተባለው የፖለቲካ ተጽዕኖም ትህነግን መልሶ የሚያፈርስ እየሆነ መጥቷል።

በቀጣይ ዘላቂ ወዳጅ የሌላት አሜሪካ የፈለገችውን ሊያሳካላት ያልቻለውን ትህነግ በማስወገድ ሒደት እንደተጠመደች ፍንጮች እየታዩ መሆናቸውን የደረሱን መረጃዎች ይጠቁማሉ።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, rapist tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule