• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዘላቂ ወዳጅ የሌላት አሜሪካ ፊቷን በትህነግ ላይ እያዞረች ነው

January 12, 2022 01:00 pm by Editor Leave a Comment

ትህነግ ብዙ ወጪ ያደረገበት የሎቢ ሥራ ኪሣራ እየገጠመው ነው
አሜሪካ ኢትዮጵያን ወደ አጎዋ ለመመለስ ፍንጭ አሳየች

የኢትዮጵያ መንግሥት ከአሜሪካ የንግድ ልዑክ የተነሱበትን ቅሬታዎች በተመለከተ ተጨማሪ “አዎንታዊና ገንቢ” ዕርምጃዎችን የሚወስድ ከሆነ፣ ኢትዮጵያ ከተጠቃሚነት የተሰረዘችበትን የአሜሪካ መንግሥት ከቀረጥ ነፃ የንግድ ዕድል (አጎአ) በተመለከተ የንግግር ሒደት ውስጥ ለመግባት ፈቃደኛ መሆኑ ተገለጸ፡፡

ጥር 2 ቀን 2014 ዓ.ም. ከጋዜጠኞች ጋር በስልክ ጋዜጣዊ መግለጫ የሰጡት ስማቸው ያልተጠቀሰ አንድ የአሜሪካ ከፍተኛ ባለሥልጣን፣ ኢትዮጵያ ከአውሮፓውያኑ ጥር ወር 2022 ጀምሮ ከአጎአ ተጠቃሚነት የታገደችው የዕድሉ ተጠቃሚ ለመሆን ከሰብዓዊ መብትና ሌሎች ጉዳዮች ጋር በተያያዘ የተቀመጡ መስፈርቶችን ባለማሟላቷ መሆኑን መናገራቸውን ኋይት ሀውስ በድረ ገጹ አስታውቋል፡፡

ይሁንና የኢትዮጵያ መንግሥት የተነሱበትን ቅሬታዎች አስመልክቶ ተጨማሪ ዕርምጃዎችን የሚወስድ ከሆነ አሜሪካ በየጊዜው ከሚደረገው የአገሮች ሁኔታ ምዘና ውጪ የንግግር ሒደት ውስጥ እንደምትገባ ባለሥልጣኑ ለጋዜጠኞቹ አብራርተዋል፡፡

“ነገር ግን በዚያ መንገድ ለመሄድ በመጀመሪያ ደረጃ ለአጎአ መቋረጥ ምክንያት በሆኑት ጉዳዮች ላይ ጉልህ የሆነ ማሻሻያ ማየት አለብን” ብለዋል፡፡

ባሳለፍነው ሳምንት ታኅሳስ 28 ቀን 2014 ዓ.ም. ከጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ጋር ንግግር ማድረጋቸው የተገለጸው የቀድሞውን የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ጄፍሪ ፌልትማንን የኢትዮጵያ ጉዞ አስመልክቶ በመግለጫው ላይ የተነሳ ሲሆን፣ ከፍተኛ ባለሥልጣኑ ፌልትማን (አምባሳደር) ወደ ኢትዮጵያ ጉዞ ያደረጉት “በኢትዮጵያ መንግሥት ጥያቄ” መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

የቀድሞውን የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ጄፍሪ ፌልትማንን በመተካት የተሾሙት አምባሳደር ዴቪድ ሳተርፊልድ መቼ ወደ ቀጣናው ለመጓዝ እንዳሰቡ ለባለሥልጣኑ ጥያቄ የቀረበላቸው ሲሆን፣ የልዩ መልዕክተኛው የጉብኝት ቀንን በተመለከተ የተወሰነ ቀን አለመኖሩን ገልጸው “ነገር ግን ረዥም [ጊዜ] እንደማይሆን እንጠብቃለን፤” ብለዋል፡፡

ጥር 2 ቀን 2014 ዓ.ም. ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) እና የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በስልክ ንግግር ማድረጋቸው የሚታወስ ሲሆን፣ ሁለቱ መሪዎች ንግግር ያደረጉት በፕሬዚዳንት ባይደን ጥያቄ መሠረት መሆኑን እኚሁ ስማቸው ያልተጠቀሰው ከፍተኛ ባለሥልጣን በመግለጫው ላይ ተናግረዋል፡፡

ሁለቱ መሪዎች ባደረጉት የስልክ ንግግር የኢትዮጵያ መንግሥት በእስር ላይ የነበሩ ፖለቲከኞችን የክስ ሒደት ማቋረጡን አስመልክተው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ (ዶ/ር) ምሥጋና ማቅረባቸው ተገልጿል፡፡ የስልክ ንግግሩን አስመልክቶ ጥር 2 ቀን 2014 ዓ.ም. በፌስቡክ ገጻቸው መልዕክት ያሰፈሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ (ዶ/ር) “በጋራ በመከባበር ላይ የተመሠረተ ገንቢ ተሳትፎ ማድረግ ትብብራችንን ለማጠናከር ትልቅ ጥቅም እንዳለው ሁለታችንም ተስማምተናል” ማለታቸው አይዘነጋም፡፡ (አማኑኤል ይልቃል – ሪፖርተር)

ትህነግ “Tigray Center for Information & Communication” በሚል ስም አሜሪካ አገር በፈጠረው ድርጅት አማካኝነት በፖለቲካው ዘርፍ ድል ለመቀዳጀት በርካታ የውስወሳ (ሎቢ) ሥራዎች ሲያከናውን ቆይቷል። በተለይ “Von Batten Montague York PC” ለሚባለው ወትዋች ድርጅት በርካታ ገንዘብ በመክፈል ከዓላማው አንጻር ውጤቶችን አምጥቷል። በተለይ ኢትዮጵያን ከአጎዋ በማስወጣት ረገድ ወትዋቹ ድርጅት በተከፈለው ልክ ሥራውን ፈጽሟል። ሆኖም አሁን አሜሪካ ኢትዮጵያን ወደ አጎዋ ለመመለስ እንደምትነጋገር መግለጽዋ በርካታ ገንዘብ የፈሰሰበት የትህነግ ውትወታ ቁሻሻ መውረጃ ውስጥ ተጥሎ ተጠርጎ እንደጠፋ መዋዕለ ንዋይ አድርጎታል። ይፈጥራል የተባለው የፖለቲካ ተጽዕኖም ትህነግን መልሶ የሚያፈርስ እየሆነ መጥቷል።

በቀጣይ ዘላቂ ወዳጅ የሌላት አሜሪካ የፈለገችውን ሊያሳካላት ያልቻለውን ትህነግ በማስወገድ ሒደት እንደተጠመደች ፍንጮች እየታዩ መሆናቸውን የደረሱን መረጃዎች ይጠቁማሉ።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, rapist tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule