• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ውሃ ጥምን በኢትዮጵያዊ እስረኞች ስቃይ ‘የማርካት’ ፖለቲካዊ ቅዠት

January 28, 2022 11:46 am by Editor Leave a Comment

ሪያድ ኢትዮጵያን በተለያዩ መስኮች በዘላቂነት እንደምትደግፍ የሳዑዲ ልማት ፈንድ መግለፁን ከወደ ሳዑዲ አረቢያ በዛሬው ዕለት ተሰምቷል።

የኢትዮጵያ ገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ እና የሳዑዲ ልማት ፈንድ ስራ አስፈፃሚ “ለሳዑዲ አረቢያና ኢትዮጵያ የጋራ ጥቅም የሚውሉ ጉዳዮች ላይ ምክክር አድርገዋል።

እንደ ዘገባዎቹ የሳውዲ የልማት ፈንድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሱልጣን ቢን አብዱራህማን አል-ሙርሺድ የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴን ተቀብለው ያነጋገሩ ሲሆን፤ ሳዑዲ አረቢያ በሳዑዲ ፈንድ በኩል በኢትዮጵያ ባከናወናቸው የልማት ተግባራትና እየተከናወኑ በሚገኙ ፕሮጀክቶች ላይ ከመወያየት ባለፈም ስለ ቀጣይ የትብብር ዘርፎች መክረዋል ነው የተባለው።

የትብብር መስኮቹ በዝርዝር ያልተገለፁ ቢሆንም የትብብር መስኮቹ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የብልጽግና ዘርፎች ላይ እንደሚሆኑ ነው የተገለፀው። 

የሪያድ ውሃ-ጥም እና ስሁት ጎዳናዎቿ 

በቀጣዮቹ ሃያ ዓመታት ውስጥ ለመካከለኛው ምስራቅ የፖለቲካና ማህበራዊ ቀውስ መንስኤ የሚሆነው ጦርነት ወይም ሽብርተኝነት እንዳይመስላችሁ” ይላል Jon B. Alterman ከ10 አመት በፊት ይፋ ያደረጉት ጥናታቸው። “Clear Gold” በሚል ርዕሳቸው የውሃን ቀጣይ ውድነት በሚጠቁም ጥናታቸው አልተርማን “የመካከለኛው ምስራቅ ስትራቴጂያዊ ከባድ ካርድ በመሆን ለፖለቲካዊና ማህበራዊ ቀውስ ዋነኛ መነሾ የሚሆነው ውሃ እና የውሃ እጥረት ነው” ነበር ያሉት። 

የሳዑዲ ውሃ ጥም

በአንድ ወቅት 500 ቢሊዮን ሜኪዩብ የከርሰ ምድር ውሃ ክምችት የነበራት ሳዑዲ አረቢያ 98 በመቶ የውሃ አቅርቦቷን ከዚሁ የውሃ ሐብቷ ነበር የምታገኘው። የዜጎቿ ዕለታዊ የውሃ ፍጆታ ከአውሮፓ ስታንዳርድ በእጥፍ ከፍ ያለ መሆን፤ በዛ ላይ ደግሞ በ 1980ዎቹ ጀምሮ አገሪቱን የሩዝና የእርሻ ደሴት ለማድረግ የተጀመሩ ሰፋፊ ፕሮጀክቶች የከርሰ ምድር ውሃዋን አሟጠጠውና ከባድ አደጋ ተደቀነባት። 

ይህን ተከትሎም 2015 ላይ 80 በመቶው የሳዑዲ የከርሰ ምድር ውሃ ማለቁን ጥናቶች አረጋገጡ። ናሽናል ጂኦግራፊክ ጭምር ይህንኑ ጥናታዊ ሪፖርት መዘገቡ ይታወሳል።

ይባስ ብሎም የሳዑዲው ኪንግ ፈይሰል ዩኒቨርሲቲ በ2016 ያወጣው ሪፖርት የሳዑዲ የከርሰ ምድር ውሃ በ 13 አመታት ውስጥ ሙሉ ለሙሉ እንደሚያልቅ ደምድሟል። ይኸውም በ2020ዎቹ መሆኑ ነው። 

የገጠማትን የውሃ ቀውስ ለመቅረፍ በተለያዩ አገራት ከገዛችው ውሃ ገብ የእርሻ መሬት በተጨማሪ የባህር ውሃን ለማጣራትም ሰፊ ርብርብ ማድረግ ከጀመረች ሰነባብታለች። ጨዋማ የባህር ውሃን አጣርታ ለመጠቀምም በየዓመቱ 3 ቢሊዮን ዶላር እያወጣች ነው የምትገኘው። በዓለማችን ከሚደረገው የባህር ውሃ የማጣራት ስራ ግማሹን መጠን የሚሸፍነው የሳዑዲ ዲሳሊኔሽን ነው። 

ተከዜን በፖርት ሱዳን ወደ ሪያድ የማሻገር ህልም 

የናይል ዋነኛ ገባሮች የሆነውን የተከዜ-አትባራ ወንዝ በመጥለፍ ወደ ሪያድ-ሳዑዲ አረቢያ በቀይ ባህር በኩል ለማሻገር ሳዑዲዎች ዓቅደው ነበር። ዕቅዱ የታሰበው በሳዑዲ ምኞትና በግብፅ ማን አለብኝነት ነበር። ጊዜው ደግሞ የ1980ዎቹ መጨረሻ። ዳንኤል ክንዴ የተባሉ ምሁር በ1999 እኤአ ባወጡት ፅሁፋቸውም እንደሚከተለው አስቀምጠውታል። 

▮…“በሰዓት 4.5 ሚሊዮን ሊትር የሚሆን ውሃ ከአትባራ (ተከዜ) በመጥለፍ ወደ ቀይ ባህሯ የወደብ ከተማ ፖርት ሱዳን ከዚያም ወደ ሪያድ ሳዑዲ አረቢያ በቀይ ባህር በኩል ለማሻገር በግብጽ ሙሉ ድጋፍ የ2 ቢሊዮን ዶላር ስራ በአርቃቂዎች ተጀምሮ ነበር፡፡ እንደ ዕቅዱ ከሆነ ሱዳን በሁለት መልኩ የምትጠቀም ሲሆን አንድም ከአትባራ (ተከዜ) በስተምስራቅ የሚገኘውን ጠፍ መሬት ለማልማት የሚያስችላት ሲሆን እንዲሁም በቀይ ባህር ዳርቻ ያሉ ፏፏቴዎችን በመጠቀም በሰዓት ከ7,000 ኪሎዋት በላይ ኤሌክትሪክ ለማምረት ያስችላታል፡፡ ሳዑዲዎቹም ግብፅን እና ሱዳንን (በዚህ ፕሮጀክት ምክንያት) ለሚያጡት የመስኖ ውሃ በግብርና ካፒታል ኢንቨስትመንት እና  በኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶች ያካክሱታል…”

ይህ ህልም ታዲያ ኢትዮጵያ ተከዜ ወንዝ ላይ በገነባችው ግድብ ህልም ሆኗል። ደግመው እንሞክር ቢሉም ማብሪያ ማጥፊያው ከተከዜው ግድብ ነውና። 

ታዲያ እነ ሳዑዲ ይህን ወይም ይህን መሰል ፕሮጀክት አሁንም አያስቡም አይባልም፡፡ ዕድል እየተጠባበቁ ቢሆን እንጂ። ሳዑዲ ትልቁ ስጋቷ ውሃ ጥም ነው። ከነዳጅም ከወርቅም በላይ ውሃ ትሻለች። 

በግዛቷ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊ ዜጎችን በማሰቃየት የጀመረችው ሩጫም የውሃ ጥሟን ለማርካት መሆኑ በግልባጩም ቢሆን ሐቅ ነው። ሪያድ የጀመረችውን ሤራ ትታ ወደ ትብብር ብትመለስ ከኢትዮጵያ ጥቅሟን እንደምታሳካ ማን በመከራት?! ሳዑዲ የማታ ማታ ስትለማመጠን መገኘቷ ለማይቀረው ካሁኑ የብርሃኑን መንገድ ብትመርጥ ያዋጣታል። 

Esleman Abay  የዓባይ ልጅ

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

(ፎቶ ከፋይል ክምችት)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Politics Tagged With: operation dismantle tplf, saudi arabia, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule