• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ውሃ ጥምን በኢትዮጵያዊ እስረኞች ስቃይ ‘የማርካት’ ፖለቲካዊ ቅዠት

January 28, 2022 11:46 am by Editor Leave a Comment

ሪያድ ኢትዮጵያን በተለያዩ መስኮች በዘላቂነት እንደምትደግፍ የሳዑዲ ልማት ፈንድ መግለፁን ከወደ ሳዑዲ አረቢያ በዛሬው ዕለት ተሰምቷል።

የኢትዮጵያ ገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ እና የሳዑዲ ልማት ፈንድ ስራ አስፈፃሚ “ለሳዑዲ አረቢያና ኢትዮጵያ የጋራ ጥቅም የሚውሉ ጉዳዮች ላይ ምክክር አድርገዋል።

እንደ ዘገባዎቹ የሳውዲ የልማት ፈንድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሱልጣን ቢን አብዱራህማን አል-ሙርሺድ የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴን ተቀብለው ያነጋገሩ ሲሆን፤ ሳዑዲ አረቢያ በሳዑዲ ፈንድ በኩል በኢትዮጵያ ባከናወናቸው የልማት ተግባራትና እየተከናወኑ በሚገኙ ፕሮጀክቶች ላይ ከመወያየት ባለፈም ስለ ቀጣይ የትብብር ዘርፎች መክረዋል ነው የተባለው።

የትብብር መስኮቹ በዝርዝር ያልተገለፁ ቢሆንም የትብብር መስኮቹ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የብልጽግና ዘርፎች ላይ እንደሚሆኑ ነው የተገለፀው። 

የሪያድ ውሃ-ጥም እና ስሁት ጎዳናዎቿ 

በቀጣዮቹ ሃያ ዓመታት ውስጥ ለመካከለኛው ምስራቅ የፖለቲካና ማህበራዊ ቀውስ መንስኤ የሚሆነው ጦርነት ወይም ሽብርተኝነት እንዳይመስላችሁ” ይላል Jon B. Alterman ከ10 አመት በፊት ይፋ ያደረጉት ጥናታቸው። “Clear Gold” በሚል ርዕሳቸው የውሃን ቀጣይ ውድነት በሚጠቁም ጥናታቸው አልተርማን “የመካከለኛው ምስራቅ ስትራቴጂያዊ ከባድ ካርድ በመሆን ለፖለቲካዊና ማህበራዊ ቀውስ ዋነኛ መነሾ የሚሆነው ውሃ እና የውሃ እጥረት ነው” ነበር ያሉት። 

የሳዑዲ ውሃ ጥም

በአንድ ወቅት 500 ቢሊዮን ሜኪዩብ የከርሰ ምድር ውሃ ክምችት የነበራት ሳዑዲ አረቢያ 98 በመቶ የውሃ አቅርቦቷን ከዚሁ የውሃ ሐብቷ ነበር የምታገኘው። የዜጎቿ ዕለታዊ የውሃ ፍጆታ ከአውሮፓ ስታንዳርድ በእጥፍ ከፍ ያለ መሆን፤ በዛ ላይ ደግሞ በ 1980ዎቹ ጀምሮ አገሪቱን የሩዝና የእርሻ ደሴት ለማድረግ የተጀመሩ ሰፋፊ ፕሮጀክቶች የከርሰ ምድር ውሃዋን አሟጠጠውና ከባድ አደጋ ተደቀነባት። 

ይህን ተከትሎም 2015 ላይ 80 በመቶው የሳዑዲ የከርሰ ምድር ውሃ ማለቁን ጥናቶች አረጋገጡ። ናሽናል ጂኦግራፊክ ጭምር ይህንኑ ጥናታዊ ሪፖርት መዘገቡ ይታወሳል።

ይባስ ብሎም የሳዑዲው ኪንግ ፈይሰል ዩኒቨርሲቲ በ2016 ያወጣው ሪፖርት የሳዑዲ የከርሰ ምድር ውሃ በ 13 አመታት ውስጥ ሙሉ ለሙሉ እንደሚያልቅ ደምድሟል። ይኸውም በ2020ዎቹ መሆኑ ነው። 

የገጠማትን የውሃ ቀውስ ለመቅረፍ በተለያዩ አገራት ከገዛችው ውሃ ገብ የእርሻ መሬት በተጨማሪ የባህር ውሃን ለማጣራትም ሰፊ ርብርብ ማድረግ ከጀመረች ሰነባብታለች። ጨዋማ የባህር ውሃን አጣርታ ለመጠቀምም በየዓመቱ 3 ቢሊዮን ዶላር እያወጣች ነው የምትገኘው። በዓለማችን ከሚደረገው የባህር ውሃ የማጣራት ስራ ግማሹን መጠን የሚሸፍነው የሳዑዲ ዲሳሊኔሽን ነው። 

ተከዜን በፖርት ሱዳን ወደ ሪያድ የማሻገር ህልም 

የናይል ዋነኛ ገባሮች የሆነውን የተከዜ-አትባራ ወንዝ በመጥለፍ ወደ ሪያድ-ሳዑዲ አረቢያ በቀይ ባህር በኩል ለማሻገር ሳዑዲዎች ዓቅደው ነበር። ዕቅዱ የታሰበው በሳዑዲ ምኞትና በግብፅ ማን አለብኝነት ነበር። ጊዜው ደግሞ የ1980ዎቹ መጨረሻ። ዳንኤል ክንዴ የተባሉ ምሁር በ1999 እኤአ ባወጡት ፅሁፋቸውም እንደሚከተለው አስቀምጠውታል። 

▮…“በሰዓት 4.5 ሚሊዮን ሊትር የሚሆን ውሃ ከአትባራ (ተከዜ) በመጥለፍ ወደ ቀይ ባህሯ የወደብ ከተማ ፖርት ሱዳን ከዚያም ወደ ሪያድ ሳዑዲ አረቢያ በቀይ ባህር በኩል ለማሻገር በግብጽ ሙሉ ድጋፍ የ2 ቢሊዮን ዶላር ስራ በአርቃቂዎች ተጀምሮ ነበር፡፡ እንደ ዕቅዱ ከሆነ ሱዳን በሁለት መልኩ የምትጠቀም ሲሆን አንድም ከአትባራ (ተከዜ) በስተምስራቅ የሚገኘውን ጠፍ መሬት ለማልማት የሚያስችላት ሲሆን እንዲሁም በቀይ ባህር ዳርቻ ያሉ ፏፏቴዎችን በመጠቀም በሰዓት ከ7,000 ኪሎዋት በላይ ኤሌክትሪክ ለማምረት ያስችላታል፡፡ ሳዑዲዎቹም ግብፅን እና ሱዳንን (በዚህ ፕሮጀክት ምክንያት) ለሚያጡት የመስኖ ውሃ በግብርና ካፒታል ኢንቨስትመንት እና  በኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶች ያካክሱታል…”

ይህ ህልም ታዲያ ኢትዮጵያ ተከዜ ወንዝ ላይ በገነባችው ግድብ ህልም ሆኗል። ደግመው እንሞክር ቢሉም ማብሪያ ማጥፊያው ከተከዜው ግድብ ነውና። 

ታዲያ እነ ሳዑዲ ይህን ወይም ይህን መሰል ፕሮጀክት አሁንም አያስቡም አይባልም፡፡ ዕድል እየተጠባበቁ ቢሆን እንጂ። ሳዑዲ ትልቁ ስጋቷ ውሃ ጥም ነው። ከነዳጅም ከወርቅም በላይ ውሃ ትሻለች። 

በግዛቷ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊ ዜጎችን በማሰቃየት የጀመረችው ሩጫም የውሃ ጥሟን ለማርካት መሆኑ በግልባጩም ቢሆን ሐቅ ነው። ሪያድ የጀመረችውን ሤራ ትታ ወደ ትብብር ብትመለስ ከኢትዮጵያ ጥቅሟን እንደምታሳካ ማን በመከራት?! ሳዑዲ የማታ ማታ ስትለማመጠን መገኘቷ ለማይቀረው ካሁኑ የብርሃኑን መንገድ ብትመርጥ ያዋጣታል። 

Esleman Abay  የዓባይ ልጅ

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

(ፎቶ ከፋይል ክምችት)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Politics Tagged With: operation dismantle tplf, saudi arabia, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule