• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሕዝብ ላይ የሚስማር ጥይት እስከማዝነብ የደረሰው የህወሓት የጭካኔ ጥግ!!

January 13, 2022 08:44 am by Editor 2 Comments

እብሪተኛው የህወሓት ኃይል የትኛውንም አማራጭ ተጠቅሞ ወደ ሥልጣን መመለስ ወይም ኢትዮጵያን መበታተን የሚል ቀቢፀ ተስፋ ይዞ ነበር ወደ ወረራ የገባው፡፡

ለዚህ ማሳያ የሚሆነው በዓለም አቀፍ ደረጃ የተከለከለውን በርካታ ሚስማር መሰል ፍንጣሪ (flechette) የተሰገሰገባቸውን በከባድ መሣሪያ ጭምር የሚተኮሱትን የሚስማር ጥይቶች በንፁሃን ላይ ማርከፍከፉ ነው፡፡

በምስሉ ላይ ወራሪው ኃይል በአፋር ጭፍራ ከተማ በንጹኃን ላይ የተጠቀማቸው የሚስማር ጥይቶች ይታያሉ፡፡ ወራሪው ኃይል ይህን መሣሪያ በአፋር እና በአማራ ክልሎች ተጠቅሟል፡፡

ነዋሪዎች እንደመሰከሩት ሚስማሮቹን ከበርካታ ጉዳት ከደረሰባቸው ንፁሃን ሰዎች ገላ ላይ ነቅለዋል፡፡ ሰቆቃውን ተመልክተዋል፡፡

ኢትዮጵያ እንደዚህ አይነት መሣሪያዎች ጥቅም ላይ ላለማዋል ዓለም አቀፍ ስምምነት ፈርማለች። (አዲስ ሚዲያ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. gi says

    January 15, 2022 01:29 am at 1:29 am

    ሕወኣት ኑክለር ቦምብም ቢሰጠው እንኳን አፋርና ሃማራውን ከአድዋ ውጭ ያሉትንም የትግራይ ሕዝብ ካልደገፉት ይጨርሳል። ደም ያሰከረው ድርጅት መጨረሻው በHIV መሞት ነው።

    Reply
  2. Tesfa says

    January 20, 2022 08:43 am at 8:43 am

    ወያኔ በሰው ልጆች ሰውነት ላይ የምስማር ጥይት መቀርቀሩ አስገራሚ አይደለም። ይህ ቡድን እኮ ያለምንም ትንኮሳ ሰው ላይ ሮኬት የተኮሰ ቡድን ነው። አሁን አሁን ሃበሻው የተጃጃለ ይመስለኛል። እንዴት እንዲህ አይነት ድፍረት፤ በደልና ዘረፋ፤ ግድያና ሰቆቃ ሰው የሆነ በሰው ላይ ያደርሳል ሲሉ በተደጋጋሚ ይጠይቃሉ። ያበዳችሁት ጥያቄ የምታቀርቡት እናንተ ናችሁ። ወያኔ የሚሰራውን ጠንቅቆ ያውቃል። በወረራቸው ስፍራዎች ሰዎች እቃቸውንም ሆነ ያላቸውን ነገር እንዳያሸሹ የሚያረጋጋ ሃይል፤ ከዚያ ገዳይ ቡድን ከዚያ ጠቃሚ ነገሮችን የሚፈታና የሚዘርፍ ከዚያ የሚጭንና ወደ መቀሌ የሚያጓጉዝ ሃይል አሰማርቶ ነው በወሎ በጎንደር፤ በአፋርና በሽዋ ወገኖቻችን እንደ እባብ የቀጠቀጠው። የወያኔ ታጣቂዎችና ጄሌዎቻቸው ሰው መሆኗቸው ከቀረ ቆይቷል፡ ከደሙ ንጽህ ነኝ የሚሉትም የወያኔ ሰራዊትን ተሰባጥረው በሚኖሩበት ሥፍራ በቀረበ ቁጥር ባህሪያቸው እየተለወጠ መንገድ ሲመሩ፤ ሰው ሲያስገድሉ፤ የዘረፋው ተባባሪ ሲሆኑ ታይቷል። እጅና እግሩን አጣምሮ የተቀመጠውና በተቀናበረ የፓለቲካ አሻጥር በኦሮሞ አክራሪዎችና በወያኔ ጽልመታዊ ምህታት ለዘመናት የተመታው የአማራ ህዝብ ለመንቃት ጊዜ ፈጅቶበት አሁን እንሆ ቤቱን እያንኳኳ ለወሬ የማይመች ነገር ወያኔ ሲያደርስበት ሆ ብሎ ተነስቷል። የዛሬው ሆ ማለት በነቃ በተደራጀ፤ ለህግ በሚገዛና በሚመራ በአንድ እጅ ሥራውን በሌላ እጅ ራሱንና ቤተሰቡን የሚከላከልበት መሳሪያውን የሚታጠቅ የበሰለና የተቀናጀ ሃይል ከላይ እስከ ታችኛው በሚሩርበት ክፍል እስካልተዘጋጀ ድረስ የኢትዮጵያ ሰራዊት ያድነኛል ብሎ ቁጭ ማለት ራስን ለዳግም እልቂት ማደራጀት ነው። ገደሉን ወርደው፤ ጥሻውን ጥሰው፤ በሜዳው ተንከባለው ወያኔን እያሳደድ የመቱት የሃገሬው ኗሪዎች፤ ፋኖ፤ የአማራ ሚሊሻ እንጂ መደበኛው ጦር መቀሌን ጥሎ ከወጣ በህዋላ የት እንዳለ እንኳን አይሰማም ነበር። በህዋላ በእግር በፈረሰ ተፈልገው ዳግመኛ ውጊያውን ተቀላቅለው የሆነውን ያው እየተጋነነም ቢሆን የሰማነው በመሆኑ እዚህ ላይ አይደገምም። ለዚህ ነው አሁን ግንባታ ግንባታ መልሶ ማቋቋም ሲባል መቅደም ያለበት የአካባቢው ሰላምና የወያኔን የድጋሚ ወረራ መከላከል የሚችል ሃይል መገንባት ነው የምንለው። ወያኔ ቂመኛ ነው። የልጅ ልጅ ፈልጎ ይገላል። አዎን በመቀሌ የሚያደርገው ግፍ ሰው መሆንን ያስጠላል። እናቶችን ሰውን እንደ እንጀራ አዋጡ እያሉ ይገኛሉ። እንዴ በፊት የተወሰድት ልጆቻችን የት አሉ ሲሏቸው “እነርሱ ተቆርጠው ቀርተው ስለተከበቡ እነርሱን ለማስፈታት ተጨማሪ ሃይል ያስፈልገናል” በማለት ለሶስተኛ ጊዜ የትግራይን ወጣቶች በማሰባሰብና ስልጠና በመስጠት ላይ ይገኛሉ። እንደ ጀርመኑ ሂትለር ከጥፋት ላይ ጥፋት እየቆለሉ ውድቀታቸው የማይታያቸው ጥቂት የአድዋ ተወላጆችና ተባባሪዎቻቸው ዛሬም እንደ ጥንቱ በትግራይ ህዝብ ስምና ደም መነገዳቸውን ቀጥለዋል። ወያኔ ተለቅሞ ጣና ሃይቅ ውስጥ መጣል ያለበት የአውሬ ስብስብ ነው። አንዳቸውም ስለ ትግራይ አይገዳቸውም። ያ ሆኖ ቢሆን ኑሮ ራሳቸው ለ 27 ዓመት በናጠጡባት ኢትዮጵያ በስልጣን ዘመናቸው ለትግራይ ህዝብ ብዙ ባደረጉ ነበር። ሌላው ቀርቶ የሚጠጣ ውሃ እንኳን ያላቀረበ ድርጅት ለትግራይ ህዝብ ነጻነት እየታገልኩ ነው ቢል ያመኑበትንና ራሱን ቂላ ቂል ያደርጋል እንጂ የጠራ ንቃተ ህሊና ላላቸው መቀለዳቸው እንደ ግንብ ጉልህ ሆኖ ከፊት ይታያል። ማን እየተሰዋ፤ ማን እየበላ እንደኖርን እኛ ጠንቅቀን እናውቃለን። ነጻ እናወጣሃለን የተባለው የትግራይ ህዝብ ዛሬም ኑሮው ከእጅ ወደ አፍ ነው። በስሙ የነገድት ግን ከነቤተሰቦቻቸው በውጭ ሃገር በዘረፉት ሃብት ዘንጠው ይኖራሉ። ያ ነው ለህዝብ መቆም? ድንቄም ነጻ አውጪ። ባርነት አፍላቂ እንጂ!
    ወያኔ ከተፈጠረ ጀምሮ ሥራው ሁሉ ደም ማፍሰስ ነው። ለዚህም ጉዳይ እንዲረዳው ወያኔ 4 ነገሮችን ከልቡ አምሮ ይጠላል።
    1. የአማራ ህዝብን – የችግርህ ሁሉ መሰረቱ የአማራ የበላይነት ነው። አማራን ማጥፋትና ማቆዝቆዝ የትግራይን ህዝብ ከፍታ ላይ ያደርሳል በሚል ሸውራራ ፈሊጥ እልፎችን አፈር ውስጥ ጨምሯል። አሁን ላይ ያደረገውንና የሚያደርገውንም ቆመን እያየን ነው።
    2. የኢትዮጵያ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ – ወያኔ ቤ/ክርስቲያኗን የሚጠላት በኢትዮጵያ ህዝቦችን ህብረትና አንድነት በማመኗ ነው። ለዚያም ነው ይህችን ቤ/ክ ከአማራው ህዝብ ጋር በማጣመር ሲከፋፍላት፤ ሲዘርፋት፤ የራሱ የሆኑ ካህናትና ጳጳስትን መስቀልና ሽጉጥ እያስያዘ ህዝብን ሲያሰልልና ሲገድል የኖረው። ስንቶች ባህታዊያን ናቸው የተገደሉት? ስንቶች ደብርና ገዳማት ናቸው የተዘረፉት? ቤቱ ይቁጥረው
    3. ሻቢያ – ወያኔ የንስሃ አባቱን ሻቢያን አምሮ ይጠላል። ለምን ብሎ ለጠየቀ መልሱ አንድ ነው። ፕ/ኢሳይያስ መለስንና ሌሎችን ተው የጎሳ ፓለቲካ ለኢትዮጵያ አይጠቅምም በማለት ሲመክሯቸው የራሳቸውን የቀጥር ጥላ የማያምኑት ወያኔዎች ቶሎ ኤርትራ ተገንጥላ የምትወስደውን ወስዳ ከቁራሽ በተረፈችው ኢትዮጵያ ያለምንም ተጽኖ ሊፈነጩ ስለፈለጉ ሻቢያን ወዲያውኑ በዚህም በዚያም ከጎናቸው አባረው ኢትዮጵያን መገሽለጥ ጀመሩ። ሴራው የገባው ሻቢያም ክፋትን ያቃመሳቸው ራሱ ስለሆነ ጠንቅቆ ያውቃቸዋልና በሞኞች የባድሜ ፍትጊያ እልፍ ወገኖቻችን አሽዋ ላይ ቀሩ። ወያኔና ሻቢያ መካረር የጀመሩት ገና በረሃ እያሉም ነበር። ግን በሰፋ ሜዳ ላይና በሚዘረፍ ሃብት ላይ የከተማ አለቆች ሲሆኑ ሲሰርቁ ባልተጣሉበት ጉዳይ ሲከፋፈሉ ተፋጅ። ዛሬም ወደፊትም ወያኔ በትግራይ መሬት እስካለ ድረስ መፋለማቸው አይቀሬ ነው።
    4. ኢትዮጵያንና አንድነቷን የሚያስቀድሙ የትግራይ ተወላጆች – ወያኔ እነዚህን የትግራይ ልጆች ከበረሃ ጀምሮ ሲመነጥራቸው ኖሯል፤ አሁንም እየገደላቸው ይገኛል። ሌላው ቀርቶ ከወያኔ ሃሳብና እይታ ውጭ ገበሬም ሆነ ምሁር ከተነፈሰ ከተገኘ ራሱ ካልተገኘ ዘመድ አዝማድ ዘብጥያ ይወርዳሉ ያለዚያም ታፍሰው በዚህና በዚያ ሰበብ ይገደላሉ። የሆነው እና በመሆን ላይ ያለው ይህ ነው። እነዚህን የሰፋ እይታ ያላቸውን የትግራይ ተወላጆች የፈጠራ ስም በመለጠፍ፤ የተዛባ ወሬ በመንዛት፤ የሚሰሩበት መ/ቤት ድረስ በመሄድ ግርግር በመፍጠር፤ ከእድርና ከሌሎች ህብረቶች በማስወጣት ጭንቅ ውስጥ ይከቷቸዋል። ወያኔ ማለት የጀርመኑ ጌስታፓ፤ የጣሊያኑ ፋሽሽት ነው የምለው በዚህና በሌሎች ጉዳዪች ነው።
    ስለሆነም የሚስማር ጥይት በሰዎች ሰውነት ላይ ወያኔ መሰካቱ እንደ አቅሚቲ ነው እንጂ ወያኔ የመርዝ ጋዝ ቢያገኝ ይጠቀምበታል። ወያኔ የድሮን፤ የአየር ሃይል፤ ሌላም የሩቅና የቅርብ ተተኳሽና ደርማሽ ነገር እጅ ቢገባ አስመራና የአማራ ክልል አመድ እንደሚሆኑ ምንም ጥርጥር የለኝም። ወያኔ ህሊና የጎደለው ድርጅት ነው። ለዚያ ነው በአስመራና በአማራ ክልል ላይ የተውሶ ሮኬት ያዘነበው። ለወያኔ ማን ይሙት ማ ግድ አይሰጠውም። ቆም ብለን ልናስብ ይገባል ይህ ድርጅት ካልከሰመ በቀጠናው ሰላም አይኖርም። የነገን ባላውቅም አሁን ባለኝ እይታ ሻቢያ እንዲህ ያለ ተንኳሽ ባህሪ አሁን አሁን አይታይበትም። የሃገሪቱ መሪም የውጭውን ሴራ ጠንቅቀው ስለተረድ ልክ እንደ ጉርምስና ዘመናቸው በዙሪያቸው ያሉትን በጡጫ የሚነርቱ አይሆኑም። ሁሉን በእርጋታና በማስተዋል ለማራመድ እየሞከሩ እንደሆነ የሚያመላኩት ነገሮች አሉ። ሰላም የሰው ልጆች መሰረታዊ መብት ነው። ግን የሚበጠብጥ እያለ ማን ጥሩ ይጠጣል? በእኔ እምነት አሁን ባለችው የሃበሻ ምድር ሁለት በጥባጮች አሉ። ወያኔና የወያኔ ተላላኪዎች። ዝግጅት፤ መንቃት፤ መደራጀት፤ መታጠቅና መሰልጠን፤ ዛሬም ሆነ ወደፊትም ለሚደርስ ያልታሰበ ወረራን ለመፋለም አማራጭ የሌለው ምርጫ ነው። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule