• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ከምርጫ 97 በኋላ የወያኔን ሴራ የሚያስፈፅሙ የክልሉ ተወላጆች 100ሺ ጠመንጃ እንዳከፋፈለ እናውቃለን”

November 8, 2021 11:42 am by Editor 1 Comment

የኢትዮጵያ ህዝብ በጉያው ተሸሽገው የአሸባሪውን ሀገር የማፈረስ ሴራ እያስፈፀሙ ያሉ የወያኔ ተላላኪዎችን መንጥሮ ማውጣት እንደሚገባው የዲሞክራሲ ተሟጋቹ አቶ ነዓምን ዘለቀ አስታወቁ።

የአርበኞች ግንቦት ሰባት መስራችና የዲሞክራሲ ተመጓቹ አቶ ነዓምን ዘለቀ ለአዲስ ዘመን እንዳስታወቁት፤ አሸባሪው የህወሓት ቡድን መለዮ አልብሶ ካሰማራቸው አራዊት መንጋዎች በተጨማሪ በህዝቡ ጉያ ተሸሽገው የሽብር ሥራውን የሚያስፈፅሙ ተላላኪዎችን በስፋት በማንቀሳቀስ ላይ ይገኛል።በተለይም በከተሞች አካባቢ በህቡዕ ያደራጃቸው እነዚሁ ፀረ ሰላም ኃይሎች የሃሰት ወሬ በማሰራጨት የህዝቡን ስነልቦና የሚሰርቁ አሉባልታዎችን በማራገብ ላይ ይገኛሉ። በመሆኑም ህዝቡ የአሸባሪውን ተላላኪዎች እንቅስቃሴ በንቃት መከታተልና መንጥሮ በማውጣት በህግ ተጠያቂ ሊያደርጋቸው ይገባል።

እንደአቶ ነዓምን ገለፃ፤ ኢትዮጵያን ለማጥፋት ቆርጦ የተነሳው ይህ ወራሪ ኃይል ከ500 ሺ ያላነሱ ፀረ ህዝብ የሆኑ አራዊት መንጋዎችን በጥላቻና በዘረኝነት መርዞ ንፁሃንን እያስጨፈጨፈ ይገኛል። ከዚህም ባለፈ በየክልሉ የመንግሥት ኃላፊነት ላይ የነበሩ የክልሉ ተወላጆችን በማደራጀት የህዝቡንና የደህንነት አካላትን አጠቃላይ እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር የሚያስችላቸውን የጥፋት አጀንዳ መዘርጋቱን ነው የተናገሩት።

አሸባሪው ቡድን ደሴ፣ ኮምቦልቻና ጎንደር ላይ ተመሳሳይ ድርጊት ሲፈፅም እንደነበር አስታውሰው በተለይም ከህዝቡ ጋር አብረው የኖሩ ተላላኪዎችን በመጠቀም ቀላል የማይባል ጥፋት ማድረሱን ጠቁመዋል። “በየከተማው ከውስጥ ሆነው መረጃ የሚሰጡ፤ የሚያስተኩሱ፤ ህዝብን የሚያሸብሩ ከዚያም አልፎ ጎረቤታቸው ላይ ሽጉጥ ያወጡ የእነሱ አባሎች አሉ” ያሉት አቶ ነዓምን በተለይም አዲስ አበባ ከተማ ከፍተኛ ውድመት ለማስከተል አድብተው እየተጠባበቁ ያሉ ተላላኪዎች መኖራቸውን ጠቁመዋል።

አሸባሪው ቡድን መላውን የኢትዮጵያ ህዝብ በባርነት ለመግዛት ሲል ለዓመታት የራሱን ሰዎች ሲያዘጋጅና ሲያደራጅ መቆየቱን አመልክተው “በተለይም ከምርጫ 97 በኋላ ድብቅ ሴራውን ለሚያስፈፅሙለት የክልሉ ተወላጆች 100 ሺ ጠመንጃ እንዳከፋፈለ እናውቃለን” ብለዋል።በተጨማሪም ከመከላከያ የተባረሩ በጀነራል ማዕረግ ያሉ የወያኔ ቅጥረኞች ሰላማዊ መስለው በየእለቱ መረጃ ከማቀበል ጀምሮ ለአውሬው ቡድን ጥርጊያ መንገድን በማበጀት ላይ እንደሚገኙ አመልክተዋል።

በተለይም በሰሜን እዝ ላይ ከተደረገው አራዊታዊ ጥቃት ተከትሎ በህቡዕ ያደራጀው የወያኔ ወኪሎች ለሀገር ከፍተኛ የደህንነት ስጋት በመሆናቸው ህዝቡ ያለአንዳች ይሉኝታ መንጥሮ ማውጣት አለበት ብለዋል። “እነሱን በጉያችን አኑረን የደህንነት ስጋት ውስጥ መግባት የለብንም” በማለት ተናግረውም፤ ወያኔ በለስ ቀንቶት ደብረ ብርሃን ከደረሰ አዲስ ከተማ ውስጥ አድብቶ በመጠባበቅ ላይ ያለው ተላላኪ ሀገር የማፍረስ ሴራውን እውን ሊያደርጉት የሚችሉበት እድል እንዳለ ስጋታቸውን ተናግረዋል።

“ቡድኑ ንፁሃንን ሊያርድ፤ ደካሞችን ሊገድል፤ ሴቶችን ሊደፍር የሚመጣ ሰው መሳይ አራዊት መሆኑን መዘንጋት የለብንም፤ በመሆኑም ድምፃቸውን አጥፍተው በየቦታው የተሰገሰጉ የእነሱን ደጋፊዎች በንቃት መጠበቅ ይገባል” ብለዋል። በተለይም በየአካባቢው ያለው ኢትዮጵያዊ ወጣት ተደራጅቶ በጥንቃቄ ህዝቡን መጠበቅ እንዳለበት አሳስበዋል።

መንግሥትም ህዝቡን በማደራጀትና በማስታጠቅ ራሱንና አገሩን እንዲጠብቅ የማድረግ ኃላፊነት ያለበት መሆኑን አመልክተዋል። “በዚህ መካከል ንፁሃና ሰላማዊ ሰዎች እንዳይጎዱ መጠንቀቅ ያስፈልጋል” ያሉት አቶ ነዓምን “በግልፅ አሁንም ጭምር እነሱን የሚደግፉ፤ ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ቡድኑን የሚጠባበቁ ፤ በየቦታው በውስኪ የሚጨፍሩ እንዳሉ ይታወቃሉ። የመመንጠር ሥራችን ከእነሱ ሊጀምር ይገባል” በማለት አስገንዝበዋል። (አዲስ ዘመን)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Interviews, Middle Column, Politics Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. dereje says

    November 23, 2021 07:05 am at 7:05 am

    Ethiopia tashenfalch

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule