• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ከምርጫ 97 በኋላ የወያኔን ሴራ የሚያስፈፅሙ የክልሉ ተወላጆች 100ሺ ጠመንጃ እንዳከፋፈለ እናውቃለን”

November 8, 2021 11:42 am by Editor 1 Comment

የኢትዮጵያ ህዝብ በጉያው ተሸሽገው የአሸባሪውን ሀገር የማፈረስ ሴራ እያስፈፀሙ ያሉ የወያኔ ተላላኪዎችን መንጥሮ ማውጣት እንደሚገባው የዲሞክራሲ ተሟጋቹ አቶ ነዓምን ዘለቀ አስታወቁ።

የአርበኞች ግንቦት ሰባት መስራችና የዲሞክራሲ ተመጓቹ አቶ ነዓምን ዘለቀ ለአዲስ ዘመን እንዳስታወቁት፤ አሸባሪው የህወሓት ቡድን መለዮ አልብሶ ካሰማራቸው አራዊት መንጋዎች በተጨማሪ በህዝቡ ጉያ ተሸሽገው የሽብር ሥራውን የሚያስፈፅሙ ተላላኪዎችን በስፋት በማንቀሳቀስ ላይ ይገኛል።በተለይም በከተሞች አካባቢ በህቡዕ ያደራጃቸው እነዚሁ ፀረ ሰላም ኃይሎች የሃሰት ወሬ በማሰራጨት የህዝቡን ስነልቦና የሚሰርቁ አሉባልታዎችን በማራገብ ላይ ይገኛሉ። በመሆኑም ህዝቡ የአሸባሪውን ተላላኪዎች እንቅስቃሴ በንቃት መከታተልና መንጥሮ በማውጣት በህግ ተጠያቂ ሊያደርጋቸው ይገባል።

እንደአቶ ነዓምን ገለፃ፤ ኢትዮጵያን ለማጥፋት ቆርጦ የተነሳው ይህ ወራሪ ኃይል ከ500 ሺ ያላነሱ ፀረ ህዝብ የሆኑ አራዊት መንጋዎችን በጥላቻና በዘረኝነት መርዞ ንፁሃንን እያስጨፈጨፈ ይገኛል። ከዚህም ባለፈ በየክልሉ የመንግሥት ኃላፊነት ላይ የነበሩ የክልሉ ተወላጆችን በማደራጀት የህዝቡንና የደህንነት አካላትን አጠቃላይ እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር የሚያስችላቸውን የጥፋት አጀንዳ መዘርጋቱን ነው የተናገሩት።

አሸባሪው ቡድን ደሴ፣ ኮምቦልቻና ጎንደር ላይ ተመሳሳይ ድርጊት ሲፈፅም እንደነበር አስታውሰው በተለይም ከህዝቡ ጋር አብረው የኖሩ ተላላኪዎችን በመጠቀም ቀላል የማይባል ጥፋት ማድረሱን ጠቁመዋል። “በየከተማው ከውስጥ ሆነው መረጃ የሚሰጡ፤ የሚያስተኩሱ፤ ህዝብን የሚያሸብሩ ከዚያም አልፎ ጎረቤታቸው ላይ ሽጉጥ ያወጡ የእነሱ አባሎች አሉ” ያሉት አቶ ነዓምን በተለይም አዲስ አበባ ከተማ ከፍተኛ ውድመት ለማስከተል አድብተው እየተጠባበቁ ያሉ ተላላኪዎች መኖራቸውን ጠቁመዋል።

አሸባሪው ቡድን መላውን የኢትዮጵያ ህዝብ በባርነት ለመግዛት ሲል ለዓመታት የራሱን ሰዎች ሲያዘጋጅና ሲያደራጅ መቆየቱን አመልክተው “በተለይም ከምርጫ 97 በኋላ ድብቅ ሴራውን ለሚያስፈፅሙለት የክልሉ ተወላጆች 100 ሺ ጠመንጃ እንዳከፋፈለ እናውቃለን” ብለዋል።በተጨማሪም ከመከላከያ የተባረሩ በጀነራል ማዕረግ ያሉ የወያኔ ቅጥረኞች ሰላማዊ መስለው በየእለቱ መረጃ ከማቀበል ጀምሮ ለአውሬው ቡድን ጥርጊያ መንገድን በማበጀት ላይ እንደሚገኙ አመልክተዋል።

በተለይም በሰሜን እዝ ላይ ከተደረገው አራዊታዊ ጥቃት ተከትሎ በህቡዕ ያደራጀው የወያኔ ወኪሎች ለሀገር ከፍተኛ የደህንነት ስጋት በመሆናቸው ህዝቡ ያለአንዳች ይሉኝታ መንጥሮ ማውጣት አለበት ብለዋል። “እነሱን በጉያችን አኑረን የደህንነት ስጋት ውስጥ መግባት የለብንም” በማለት ተናግረውም፤ ወያኔ በለስ ቀንቶት ደብረ ብርሃን ከደረሰ አዲስ ከተማ ውስጥ አድብቶ በመጠባበቅ ላይ ያለው ተላላኪ ሀገር የማፍረስ ሴራውን እውን ሊያደርጉት የሚችሉበት እድል እንዳለ ስጋታቸውን ተናግረዋል።

“ቡድኑ ንፁሃንን ሊያርድ፤ ደካሞችን ሊገድል፤ ሴቶችን ሊደፍር የሚመጣ ሰው መሳይ አራዊት መሆኑን መዘንጋት የለብንም፤ በመሆኑም ድምፃቸውን አጥፍተው በየቦታው የተሰገሰጉ የእነሱን ደጋፊዎች በንቃት መጠበቅ ይገባል” ብለዋል። በተለይም በየአካባቢው ያለው ኢትዮጵያዊ ወጣት ተደራጅቶ በጥንቃቄ ህዝቡን መጠበቅ እንዳለበት አሳስበዋል።

መንግሥትም ህዝቡን በማደራጀትና በማስታጠቅ ራሱንና አገሩን እንዲጠብቅ የማድረግ ኃላፊነት ያለበት መሆኑን አመልክተዋል። “በዚህ መካከል ንፁሃና ሰላማዊ ሰዎች እንዳይጎዱ መጠንቀቅ ያስፈልጋል” ያሉት አቶ ነዓምን “በግልፅ አሁንም ጭምር እነሱን የሚደግፉ፤ ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ቡድኑን የሚጠባበቁ ፤ በየቦታው በውስኪ የሚጨፍሩ እንዳሉ ይታወቃሉ። የመመንጠር ሥራችን ከእነሱ ሊጀምር ይገባል” በማለት አስገንዝበዋል። (አዲስ ዘመን)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Interviews, Middle Column, Politics Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. dereje says

    November 23, 2021 07:05 am at 7:05 am

    Ethiopia tashenfalch

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule