• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል

May 16, 2022 08:30 am by Editor Leave a Comment

50 ሚሊዮን ሕዝብ የሚኖርበት የአማራ ክልል ዓመታዊ በጀት ሰማኒያ ቢሊዮን ነው

በትግራይ ክልል ለአምስት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ሕዝብ ሰብዓዊ ድጋፍ እየተሰጠ መሆኑን የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ። እስካሁን ወደ ትግራይ የሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦት ይዘው ከሄዱ አንድ ሺህ 626 ከባድ ተሽከርካሪዎች የተመለሱት ተሽከርካሪዎች 596 ብቻ እንደሆኑ አመልክተዋል። ክልሉን የሚያስተዳድረው ትህነግ በበኩሉ የሚገባው እርዳታ ከሚፈለገው አንጻር በቂ እንዳልሆነ ገልጿል። ዕርዳታ ጭነው የሚገቡትን ከባድ ተሽከረካሪዎች ለምን እንደሚያግታቸው ምክንያት አላቀረበም።

የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ደበበ ዘውዴን ጠቅሶ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንዳስታወቀው፤ ምግብ፣ ምግብ ነክ ያልሆኑና መድኃኒት እንዲሁም የትራንስፖርትና የጥሬ ገንዘብ ዝውውርን ጨምሮ ለአምስት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን የትግራይ ሕዝብ ሰብዓዊ ድጋፍ እየተሰጠ መሆኑንን ገልጸዋል።

በትግራይ ክልል ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች በተለያዩ ድርጅቶች አማካኝነት እንዲደርሳቸው በማድረግ በኩል ሥራው የተሠራና ተፈቅዶ እንዲሄድ እየተደረገ ያለው በኢትዮጵያ መንግሥት እንደሆነ አቶ ደበበ ገልጸዋል። በዚህም በአሁን ወቅት በክልሉ ድጋፍ ለሚሹ አምስት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ሕዝብ ሰብዓዊ ድጋፍ እየተሰጠ ይገኛል ብለዋል።

ሰብዓዊ ድጋፉ በርካታ ምግብና ምግብ ነክ ያልሆኑ ድጋፎችን ያካተተ እንደሆነ፤ በዚህም በርካታ የዓለም አቀፍ ሰብዓዊ ድጋፍ ላይ የተሰለፉ አጋር አካላት ምግብን ጨምሮ መድኃኒትና ሌሎች ድጋፎችን ለክልሉ ዜጎች በመስጠት ላይ እንደሚገኙ ጠቅሰዋል።

አቶ ደበበ እንዳሉት፤ እስከ ግንቦት 1 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ በጥሬ ገንዘብ ለአስተዳደርና ለፕሮግራም ማስፈጸሚያ የሚሆን አንድ ነጥብ 76 ቢሊዮን ብር ወደ ክልሉ እንዲላክ ተደርጓል። ይሄንንም የሚያስፈጽሙት በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ አጋር ድርጅቶች ናቸው።

202 ሺህ 79 ኪሎ ግራም የተለያዩ መድኃኒቶች በተለያዩ አጋር ድርጅቶች ሰብዓዊ ድጋፍ በአየር ትራንስፖርት ወደ ክልሉ መጓጓዙንም አቶ ደበበ ገልጸዋል።

ከዚህም ባሻገር በተለያዩ ድርጅቶች የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦት 406ሺህ 403 ኪሎ ግራም የተመጣጠነ ምግብ እና 91ሺህ 558 ኪሎ ግራም ምግብ ነክ ያልሆኑ የተለያዩ ቁሳቁሶች በአየር ትራንስፖርት እንደተጓጓዘ ተናግረዋል።

እንደ አቶ ደበበ ገለጻ፤ በሚያዚያ ወር 2014 ዓ.ም 401 ሺህ 29 ሊትር ነዳጅም ተጓጉዟል። እስካሁን ይህንን በመጓጓዝ ደረጃ በየብስ ላይ መቀሌ የደረሱ ከባድ ተሽከርካሪዎች አንድ ሺህ 626 ናቸው። ከዚህ ውስጥ የተመለሱት ተሽከርካሪዎች 596 ብቻ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

አቶ ደበበ፤ እስካሁን ለሰብዓዊ አገልግሎት 221 የአየር በረራ መከናወኑን ጠቅሰው፤ ሌሎች ክልሎች እየተላከ ካለው በበለጠ 83 ድርጅቶች በትግራይ ሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦት እየተረባረቡ እንደሚገኙ ነው የገለጹት።

ከሐምሌ 2013 ጀምሮ 50 ሺህ 921 ሜትሪክ ቶን ምግብ፤ እንደ ውሃ፣ መጠለያ፣ ቁሳቁስ፣ ንጽህና መጠበቂያ የመሳሰሉ ዘጠኝ ሺህ 563 ሜትሪክ ቶን ተጨማሪ ቁሳቁሶች በተለያዩ አጋር ድርጅቶች ሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦት አማካኝነት በየብስ ትራንስፖርት ለክልሉ ዜጎች መጓጓዙን አስታውቀዋል።

ስለ ኢትዮጵያ ሕዝብ የመናገርና አጠቃላይ መረጃ መስጠት የሚቻለው በኢትዮጵያ መንግሥት ብቻ ነው። በተለይ በሚዲያዎች በኩል ከግለሰብ ጀምሮ የሚሰሙ ነገሮችን ተመርኩዞ መናገር አስቸጋሪ ነገር ነው ሲሉም አቶ ደበበ ተናግረዋል።

ወደ ትግራይ ክልል እየገባ ያለው የዕርዳታ አቅርቦት ከሚያስፈልገው አንጻር እጅግ አነስተኛ መሆኑን እና በዚህም ምክንያት ሞትና ረሃብ እየተስፋፋ እንደሚገኝ የትግራይ ክልል የግብርና እና ገጠር ልማት ቢሮ ኃላፊ መሆናቸውን የገለጹት ዶ/ር አትንኩት መዝገቡ፣ በቅርቡ ለቪኦኤ ተናግረዋል፡፡

ወደ ክልሉ ለሚደረገው የዕርዳታ አቅርቦት ማነስ የትግራይ ክልል አመራሮች እና አንዳንድ የረድኤት ድርጅቶች መንግሥትን ተጠያቂ አድርገዋል። ሃላፊው መንግስት በቁጥር፣ በቀን፣ በመለክያና በስም ለይቶ አንድ በአንድ ወደ ትግራይ የገባውን እርዳታ፣ እንዲሁም 76 ቢልዮን ብር አስመልክቶ ቪኦኤ ቃል በቃል ጥያቄ አላቀረበም። የቪኦኤ የትግራይ ዘጋቢ በደፈናው ሃላፊው መንግስትን እንደወነጀሉ ነው ያስታወቀው። መንግስት ውንጀላውን እንደይቀበለውም አመልክቷል።

76 ቢሊዮን ብርና እርዳታ የሚላክለት የትግራይ ክልል አስተዳዳሪ ትህነግ በስሌት ደረጃ በአገሪቱ ካሉ ክልሎች በላይ ሃብት እየተላከለት መሆኑንን መረጃው ያሳያል። እስከ ግንቦት አንድ ቀን 2014 ድረስ ለማስፈጸሚያ ወደ ትግራይ የተላከው 76 ቢልዮን ብር ከአማራ ክልል ዓመታዊ በጀት ጋር ሲነጻጸር በአራት ቢሊዮን ብቻ ነው የሚያንሰው። 50 ሚሊዮን የሚጠጋ ህዝብ ያለው አማራ ክልል በጀቱ ሰማኒያ ቢሊዮን መሆኑ ይታወቃል። በጀቱ ተጨማሪውን ሳያካትት ሲሆን ለማሳያነት ለመጠቀም እንጂ ሌላ ዓላማ የለውም። (ኢትዮ 12)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule