• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል

May 16, 2022 08:30 am by Editor Leave a Comment

50 ሚሊዮን ሕዝብ የሚኖርበት የአማራ ክልል ዓመታዊ በጀት ሰማኒያ ቢሊዮን ነው

በትግራይ ክልል ለአምስት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ሕዝብ ሰብዓዊ ድጋፍ እየተሰጠ መሆኑን የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ። እስካሁን ወደ ትግራይ የሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦት ይዘው ከሄዱ አንድ ሺህ 626 ከባድ ተሽከርካሪዎች የተመለሱት ተሽከርካሪዎች 596 ብቻ እንደሆኑ አመልክተዋል። ክልሉን የሚያስተዳድረው ትህነግ በበኩሉ የሚገባው እርዳታ ከሚፈለገው አንጻር በቂ እንዳልሆነ ገልጿል። ዕርዳታ ጭነው የሚገቡትን ከባድ ተሽከረካሪዎች ለምን እንደሚያግታቸው ምክንያት አላቀረበም።

የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ደበበ ዘውዴን ጠቅሶ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንዳስታወቀው፤ ምግብ፣ ምግብ ነክ ያልሆኑና መድኃኒት እንዲሁም የትራንስፖርትና የጥሬ ገንዘብ ዝውውርን ጨምሮ ለአምስት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን የትግራይ ሕዝብ ሰብዓዊ ድጋፍ እየተሰጠ መሆኑንን ገልጸዋል።

በትግራይ ክልል ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች በተለያዩ ድርጅቶች አማካኝነት እንዲደርሳቸው በማድረግ በኩል ሥራው የተሠራና ተፈቅዶ እንዲሄድ እየተደረገ ያለው በኢትዮጵያ መንግሥት እንደሆነ አቶ ደበበ ገልጸዋል። በዚህም በአሁን ወቅት በክልሉ ድጋፍ ለሚሹ አምስት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ሕዝብ ሰብዓዊ ድጋፍ እየተሰጠ ይገኛል ብለዋል።

ሰብዓዊ ድጋፉ በርካታ ምግብና ምግብ ነክ ያልሆኑ ድጋፎችን ያካተተ እንደሆነ፤ በዚህም በርካታ የዓለም አቀፍ ሰብዓዊ ድጋፍ ላይ የተሰለፉ አጋር አካላት ምግብን ጨምሮ መድኃኒትና ሌሎች ድጋፎችን ለክልሉ ዜጎች በመስጠት ላይ እንደሚገኙ ጠቅሰዋል።

አቶ ደበበ እንዳሉት፤ እስከ ግንቦት 1 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ በጥሬ ገንዘብ ለአስተዳደርና ለፕሮግራም ማስፈጸሚያ የሚሆን አንድ ነጥብ 76 ቢሊዮን ብር ወደ ክልሉ እንዲላክ ተደርጓል። ይሄንንም የሚያስፈጽሙት በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ አጋር ድርጅቶች ናቸው።

202 ሺህ 79 ኪሎ ግራም የተለያዩ መድኃኒቶች በተለያዩ አጋር ድርጅቶች ሰብዓዊ ድጋፍ በአየር ትራንስፖርት ወደ ክልሉ መጓጓዙንም አቶ ደበበ ገልጸዋል።

ከዚህም ባሻገር በተለያዩ ድርጅቶች የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦት 406ሺህ 403 ኪሎ ግራም የተመጣጠነ ምግብ እና 91ሺህ 558 ኪሎ ግራም ምግብ ነክ ያልሆኑ የተለያዩ ቁሳቁሶች በአየር ትራንስፖርት እንደተጓጓዘ ተናግረዋል።

እንደ አቶ ደበበ ገለጻ፤ በሚያዚያ ወር 2014 ዓ.ም 401 ሺህ 29 ሊትር ነዳጅም ተጓጉዟል። እስካሁን ይህንን በመጓጓዝ ደረጃ በየብስ ላይ መቀሌ የደረሱ ከባድ ተሽከርካሪዎች አንድ ሺህ 626 ናቸው። ከዚህ ውስጥ የተመለሱት ተሽከርካሪዎች 596 ብቻ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

አቶ ደበበ፤ እስካሁን ለሰብዓዊ አገልግሎት 221 የአየር በረራ መከናወኑን ጠቅሰው፤ ሌሎች ክልሎች እየተላከ ካለው በበለጠ 83 ድርጅቶች በትግራይ ሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦት እየተረባረቡ እንደሚገኙ ነው የገለጹት።

ከሐምሌ 2013 ጀምሮ 50 ሺህ 921 ሜትሪክ ቶን ምግብ፤ እንደ ውሃ፣ መጠለያ፣ ቁሳቁስ፣ ንጽህና መጠበቂያ የመሳሰሉ ዘጠኝ ሺህ 563 ሜትሪክ ቶን ተጨማሪ ቁሳቁሶች በተለያዩ አጋር ድርጅቶች ሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦት አማካኝነት በየብስ ትራንስፖርት ለክልሉ ዜጎች መጓጓዙን አስታውቀዋል።

ስለ ኢትዮጵያ ሕዝብ የመናገርና አጠቃላይ መረጃ መስጠት የሚቻለው በኢትዮጵያ መንግሥት ብቻ ነው። በተለይ በሚዲያዎች በኩል ከግለሰብ ጀምሮ የሚሰሙ ነገሮችን ተመርኩዞ መናገር አስቸጋሪ ነገር ነው ሲሉም አቶ ደበበ ተናግረዋል።

ወደ ትግራይ ክልል እየገባ ያለው የዕርዳታ አቅርቦት ከሚያስፈልገው አንጻር እጅግ አነስተኛ መሆኑን እና በዚህም ምክንያት ሞትና ረሃብ እየተስፋፋ እንደሚገኝ የትግራይ ክልል የግብርና እና ገጠር ልማት ቢሮ ኃላፊ መሆናቸውን የገለጹት ዶ/ር አትንኩት መዝገቡ፣ በቅርቡ ለቪኦኤ ተናግረዋል፡፡

ወደ ክልሉ ለሚደረገው የዕርዳታ አቅርቦት ማነስ የትግራይ ክልል አመራሮች እና አንዳንድ የረድኤት ድርጅቶች መንግሥትን ተጠያቂ አድርገዋል። ሃላፊው መንግስት በቁጥር፣ በቀን፣ በመለክያና በስም ለይቶ አንድ በአንድ ወደ ትግራይ የገባውን እርዳታ፣ እንዲሁም 76 ቢልዮን ብር አስመልክቶ ቪኦኤ ቃል በቃል ጥያቄ አላቀረበም። የቪኦኤ የትግራይ ዘጋቢ በደፈናው ሃላፊው መንግስትን እንደወነጀሉ ነው ያስታወቀው። መንግስት ውንጀላውን እንደይቀበለውም አመልክቷል።

76 ቢሊዮን ብርና እርዳታ የሚላክለት የትግራይ ክልል አስተዳዳሪ ትህነግ በስሌት ደረጃ በአገሪቱ ካሉ ክልሎች በላይ ሃብት እየተላከለት መሆኑንን መረጃው ያሳያል። እስከ ግንቦት አንድ ቀን 2014 ድረስ ለማስፈጸሚያ ወደ ትግራይ የተላከው 76 ቢልዮን ብር ከአማራ ክልል ዓመታዊ በጀት ጋር ሲነጻጸር በአራት ቢሊዮን ብቻ ነው የሚያንሰው። 50 ሚሊዮን የሚጠጋ ህዝብ ያለው አማራ ክልል በጀቱ ሰማኒያ ቢሊዮን መሆኑ ይታወቃል። በጀቱ ተጨማሪውን ሳያካትት ሲሆን ለማሳያነት ለመጠቀም እንጂ ሌላ ዓላማ የለውም። (ኢትዮ 12)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule