• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል

May 16, 2022 08:30 am by Editor Leave a Comment

50 ሚሊዮን ሕዝብ የሚኖርበት የአማራ ክልል ዓመታዊ በጀት ሰማኒያ ቢሊዮን ነው

በትግራይ ክልል ለአምስት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ሕዝብ ሰብዓዊ ድጋፍ እየተሰጠ መሆኑን የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ። እስካሁን ወደ ትግራይ የሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦት ይዘው ከሄዱ አንድ ሺህ 626 ከባድ ተሽከርካሪዎች የተመለሱት ተሽከርካሪዎች 596 ብቻ እንደሆኑ አመልክተዋል። ክልሉን የሚያስተዳድረው ትህነግ በበኩሉ የሚገባው እርዳታ ከሚፈለገው አንጻር በቂ እንዳልሆነ ገልጿል። ዕርዳታ ጭነው የሚገቡትን ከባድ ተሽከረካሪዎች ለምን እንደሚያግታቸው ምክንያት አላቀረበም።

የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ደበበ ዘውዴን ጠቅሶ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንዳስታወቀው፤ ምግብ፣ ምግብ ነክ ያልሆኑና መድኃኒት እንዲሁም የትራንስፖርትና የጥሬ ገንዘብ ዝውውርን ጨምሮ ለአምስት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን የትግራይ ሕዝብ ሰብዓዊ ድጋፍ እየተሰጠ መሆኑንን ገልጸዋል።

በትግራይ ክልል ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች በተለያዩ ድርጅቶች አማካኝነት እንዲደርሳቸው በማድረግ በኩል ሥራው የተሠራና ተፈቅዶ እንዲሄድ እየተደረገ ያለው በኢትዮጵያ መንግሥት እንደሆነ አቶ ደበበ ገልጸዋል። በዚህም በአሁን ወቅት በክልሉ ድጋፍ ለሚሹ አምስት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ሕዝብ ሰብዓዊ ድጋፍ እየተሰጠ ይገኛል ብለዋል።

ሰብዓዊ ድጋፉ በርካታ ምግብና ምግብ ነክ ያልሆኑ ድጋፎችን ያካተተ እንደሆነ፤ በዚህም በርካታ የዓለም አቀፍ ሰብዓዊ ድጋፍ ላይ የተሰለፉ አጋር አካላት ምግብን ጨምሮ መድኃኒትና ሌሎች ድጋፎችን ለክልሉ ዜጎች በመስጠት ላይ እንደሚገኙ ጠቅሰዋል።

አቶ ደበበ እንዳሉት፤ እስከ ግንቦት 1 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ በጥሬ ገንዘብ ለአስተዳደርና ለፕሮግራም ማስፈጸሚያ የሚሆን አንድ ነጥብ 76 ቢሊዮን ብር ወደ ክልሉ እንዲላክ ተደርጓል። ይሄንንም የሚያስፈጽሙት በአካባቢው የሚንቀሳቀሱ አጋር ድርጅቶች ናቸው።

202 ሺህ 79 ኪሎ ግራም የተለያዩ መድኃኒቶች በተለያዩ አጋር ድርጅቶች ሰብዓዊ ድጋፍ በአየር ትራንስፖርት ወደ ክልሉ መጓጓዙንም አቶ ደበበ ገልጸዋል።

ከዚህም ባሻገር በተለያዩ ድርጅቶች የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦት 406ሺህ 403 ኪሎ ግራም የተመጣጠነ ምግብ እና 91ሺህ 558 ኪሎ ግራም ምግብ ነክ ያልሆኑ የተለያዩ ቁሳቁሶች በአየር ትራንስፖርት እንደተጓጓዘ ተናግረዋል።

እንደ አቶ ደበበ ገለጻ፤ በሚያዚያ ወር 2014 ዓ.ም 401 ሺህ 29 ሊትር ነዳጅም ተጓጉዟል። እስካሁን ይህንን በመጓጓዝ ደረጃ በየብስ ላይ መቀሌ የደረሱ ከባድ ተሽከርካሪዎች አንድ ሺህ 626 ናቸው። ከዚህ ውስጥ የተመለሱት ተሽከርካሪዎች 596 ብቻ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

አቶ ደበበ፤ እስካሁን ለሰብዓዊ አገልግሎት 221 የአየር በረራ መከናወኑን ጠቅሰው፤ ሌሎች ክልሎች እየተላከ ካለው በበለጠ 83 ድርጅቶች በትግራይ ሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦት እየተረባረቡ እንደሚገኙ ነው የገለጹት።

ከሐምሌ 2013 ጀምሮ 50 ሺህ 921 ሜትሪክ ቶን ምግብ፤ እንደ ውሃ፣ መጠለያ፣ ቁሳቁስ፣ ንጽህና መጠበቂያ የመሳሰሉ ዘጠኝ ሺህ 563 ሜትሪክ ቶን ተጨማሪ ቁሳቁሶች በተለያዩ አጋር ድርጅቶች ሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦት አማካኝነት በየብስ ትራንስፖርት ለክልሉ ዜጎች መጓጓዙን አስታውቀዋል።

ስለ ኢትዮጵያ ሕዝብ የመናገርና አጠቃላይ መረጃ መስጠት የሚቻለው በኢትዮጵያ መንግሥት ብቻ ነው። በተለይ በሚዲያዎች በኩል ከግለሰብ ጀምሮ የሚሰሙ ነገሮችን ተመርኩዞ መናገር አስቸጋሪ ነገር ነው ሲሉም አቶ ደበበ ተናግረዋል።

ወደ ትግራይ ክልል እየገባ ያለው የዕርዳታ አቅርቦት ከሚያስፈልገው አንጻር እጅግ አነስተኛ መሆኑን እና በዚህም ምክንያት ሞትና ረሃብ እየተስፋፋ እንደሚገኝ የትግራይ ክልል የግብርና እና ገጠር ልማት ቢሮ ኃላፊ መሆናቸውን የገለጹት ዶ/ር አትንኩት መዝገቡ፣ በቅርቡ ለቪኦኤ ተናግረዋል፡፡

ወደ ክልሉ ለሚደረገው የዕርዳታ አቅርቦት ማነስ የትግራይ ክልል አመራሮች እና አንዳንድ የረድኤት ድርጅቶች መንግሥትን ተጠያቂ አድርገዋል። ሃላፊው መንግስት በቁጥር፣ በቀን፣ በመለክያና በስም ለይቶ አንድ በአንድ ወደ ትግራይ የገባውን እርዳታ፣ እንዲሁም 76 ቢልዮን ብር አስመልክቶ ቪኦኤ ቃል በቃል ጥያቄ አላቀረበም። የቪኦኤ የትግራይ ዘጋቢ በደፈናው ሃላፊው መንግስትን እንደወነጀሉ ነው ያስታወቀው። መንግስት ውንጀላውን እንደይቀበለውም አመልክቷል።

76 ቢሊዮን ብርና እርዳታ የሚላክለት የትግራይ ክልል አስተዳዳሪ ትህነግ በስሌት ደረጃ በአገሪቱ ካሉ ክልሎች በላይ ሃብት እየተላከለት መሆኑንን መረጃው ያሳያል። እስከ ግንቦት አንድ ቀን 2014 ድረስ ለማስፈጸሚያ ወደ ትግራይ የተላከው 76 ቢልዮን ብር ከአማራ ክልል ዓመታዊ በጀት ጋር ሲነጻጸር በአራት ቢሊዮን ብቻ ነው የሚያንሰው። 50 ሚሊዮን የሚጠጋ ህዝብ ያለው አማራ ክልል በጀቱ ሰማኒያ ቢሊዮን መሆኑ ይታወቃል። በጀቱ ተጨማሪውን ሳያካትት ሲሆን ለማሳያነት ለመጠቀም እንጂ ሌላ ዓላማ የለውም። (ኢትዮ 12)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule