• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ

May 27, 2022 01:40 am by Editor Leave a Comment

በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን ጭልጋ ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ ሀብታሙ ፈለቀ የ55 ዓመት ጎልማሳ ሲሆኑ በአካባቢው በተደጋጋሚ የሚነሱት ግጭቶች ተረጋግተው እንዳይኖሩ ሲያደርጓቸው እንደቆዩ ይገልጻሉ።

በሌሎች ጊዜያት ከተነሱት ግጭቶች በላይ ባለፈው ዓመት ሚያዚያ 2013 ዓ.ም የተነሳው ግጭት አቶ ሀብታሙን ከመኖሪያ ቀያቸው እንዲፈናቀሉ እንዳደረጋቸው ገልጸዋል። ሚያዚያ 2013 ዓ.ም ግጭት ተነስቶ ንብረት ሲወድምና የሰው ህይወት ሲጠፋ አቶ ሀብታሙ አካባቢውን ለቀው ለመሄድ መነሳታቸውን ይናገራሉ።

አቶ ሀብታሙ የአማራ ብሔር ተወላጅ ሲሆኑ ቤት ንብረታቸውን ለቅማንት ብሔረሰብ ተወላጁ ጓደኛቸው አስረክበው ወደ ጎንደር ከተማ እንደመጡ ለአል ዐይን አማርኛ ገልጸዋል።

ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ በተደጋጋሚ ሲነሳ የነበረው ግጭት በማንነት ምክንያት ሆኖ ሳለ የአማራ ብሔር ተወላጅ የሆኑት አቶ ሀብታሙ ቤት ንብረታቸውን እንዲጠብቁላቸው አደራ የሰጡት ግን ለቅማንት ማህበረሰብ ተወላጁ ሀብቱ በላይ እንደሆነ ለአል ዐይን አማርኛ ተናግረዋል።

አል ዐይን አማርኛ፤ የጓደኛቸውን ቤት ላለፉት ወራት በአደራ መልክ ጠብቀው ያቆዩትና ትናንት ያስረከቡት አቶ ሀብቱ በላይ በስልክ አነጋግሯቸዋል። ላለፉት ወራት የጓደኛቸውን ቤት እንደራሳቸው አድርገው ከዘረፋና ከውድመት ሲጠብቁ መቆየታቸውን ተናግረዋል።

ግለሰቦች በዚህ ልክ አደራ የሚሰጣጡ ከሆነና የሚደማመጡ ከሆነ እንዴት በሁለቱ ወገኖች መካከል ግጭት ተከሰተ ሲል አል ዐይን ላቀረበው ጥያቄ አቶ ሀብቱ “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው፤ ቅማንት ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ቅዴፓ) የሚባል ቡድን የችግሩ ጠንሳሽ ነው” ሲሉ ነው የቅማንት ብሔረሰብ ተወላጁ የገለጹት።

ከስምንት ዓመት በፊት በማንነት ምክንያት እንደተነሱ በተገለጹ ግጭቶች አቶ ሀብታሙን ጨምሮ በርካቶች መፈናቀላቸው የሚታወስ ሲሆን፤ ከ 11 ሺህ በላይ የሚሆኑት ወደ ቀያቸው ተመልሰዋል ተብሏል።

ነዋሪዎቹ ወደ አይከል ሲመለሱ የከተማው ነዋሪዎች አቀባበል እንዳደረጉላቸው አቶ ሀብታሙ ተናግረዋል። አቶ ሀብታሙ ከተፈናቀሉበት አካባቢ ወደ ቀድሞ መኖሪያቸው ከመመለሳቸውም በላይ በአደራ መልክ የሰጡት ቤታቸውን እንደነበረ መቀበላቸውን ገልጸዋል።

በግለሰብና በህዝብ መካከል ምንም ችግር እንደሌለ የእርሳቸውና የአቶ ሀብቱ ንግግርና አደራ ማክበር ብቻውን ማሳያ እንደሚሆን ገልጸዋል።

ከአይከል ከተማ ተፈናቅለው የነበሩት ሌላኛው ግለሰብ አቶ ሽኩር መሐመድም ወደ ቀያቸው መመለሳቸውን ተናግረዋል። ወደ ከተማ ሲመለሱም ቤትና ንብረታቸውን በሰላም እንዳገኙት ለአል ዐይን አማርኛ ገልጸዋል።

አማራ እና ቅማንት በሚል ሕዝቡ እንዲጋጭ የተደረገው “የቅማንት ኮሚቴ” ተብሎ በሚጠራው ቡድን እንጅ በሕዝብ መካከል እንዳልሆነም ነው አቶ ሽኩር ያነሱት።

ወደ ቀያቸው የተመለሱት ተፈናቃዮች ጊዜያዊ ድጋፍ እና ዘላቂ ሰላም እንዲመጣ መንግሥት ሊሰራ እንደሚገባ አንስተዋል።

የአይከል ከተማ ሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት ሃላፊ መላኩ አለም አንተ ከአል ዐይን አማርኛ ጋር ባደረጉት ቆይታ በአካባቢው ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ በተከሰቱ ግጭቶች ከአካባቢ ርቀው የነበሩ ዜጎች ዛሬ አይከል ከተማ መግባታቸውን ለአል ዐይን አማርኛ አረጋግጠዋል።

አቶ መላኩ እንዳሉት ግጭቶቹ በተቀሰቀሱ ጊዜ አካባቢውን ለቀው ከተፈናቀሉ ዜጎች በተጨማሪም እጃቸው እንዳለበት የሚጠረጠሩም ወደ ከተማዋ መምጣታቸውን ተናግረዋል።

በግጭቶቹ እጃቸው እንዳበት የሚጠረጠሩ ዜጎች “መንግሥት በሚጠይቀን ለመጠየቅ ዝግጁ ነን” በማለት እጃቸውን ለመንግሥት እንደሰጡም ሃላፊው ለአል ዐይን አማርኛ ተናግረዋል።

ዜጎቹ ወደ አይከል ከተማ የተመለሱት አካባቢው ከግጭት ነጻ መሆኑ ለተፈናቃዮች በመገለጹ ሲሆን የከተማዋ ነዋሪዎችም የተፈናቀሉት ወገኖች እንዲመለሱ በመጠየቃቸው መሆኑ ተገልጿል።

በአማራ ብሔር እና በቅማንት ብሔረሰብ መካከል ግጭት እንዲነሳ ያደረገው ትህነግ መሆኑን አቶ መላኩ ገልጸዋል። አል ዐይን አማርኛ ግጭት ቀስቃሹ ትህነግ ስለመሆኑ ምን ማስረጃ እንዳላቸው የጠየቃቸው አቶ መላኩ፤ ለዚህ ማሳያ መኖሩን ገልጸው ዝርዝሩ ግን ለህግ የሚቀርብ እንደሆነ ገልጸዋል።

 “የቅማንት ኮሚቴ” በሚል ይጠራ የነበረው ቡድን ከትህነግ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት እንደነበረው ያነሱት ሃላፊው፣ የኮሚቴ አባላት ነን ያሉ አካላት ለህክምና በሚል ወደ ትግራይ መሄዳቸው መረጋገጡን አንስተዋል።

የኮሚቴው አባላት ህክምና መሄድ አስፈልጓቸው ከነበረ ቅርብ ወዳሉ የአማራ ክልል የጤና ተቋማት መሄድ ይችሉ እንደነበር የገለጹት አቶ መላኩ ወደ ትግራይ መሄዳቸው ከህወሃት ጋር ግንኑኘት እንዳላቸው ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።

የአይከል ከተማ ሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት ሃላፊ መላኩ አለም አንተ “የቅማንት ኮሚቴ” የሚባለው ቡድን ዓላማው ግጭት መፍጠር ነበር ያሉ ሲሆን፤ አሁን ግን በራሱ ጊዜ መፍረሱን ገልጸዋል።

ከዚህ በፊት የቅማንት ብሔረሰብ ተወካይ እንደሆኑ ገልጸው የነበሩ አካላት ቀበሌዎችን እንዲያስተዳድሩ ጥያቄ አቅርበው የክልሉ መንግሥት 42 ቀበሌዎችን እንዲያስተዳድሩ የፈቀደ ቢሆንም ተቃውሞ በመነሳቱ ምክንያት መጨረሻ ላይ 69 ቀበሌዎችን እንዲያስተዳድሩ ተፈቅዶ ነበር። ይሁንና ግጭቱ በዚህም ባለመቋጨቱ ላለፉት 8 ዓመታት ግጭት ሲከሰት ቆይቷል።

የክልል፣ ዞንና ከተማ አስተዳደር የሥራ ሃላፊዎች ከዚህ በኋላ ግጭቱ ዳግም እንዳይነሳ እየተሰራ መሆኑን ደጋግመው ገልጸው የነበረ ቢሆንም ችግሩ ግን ሳይፈታ ቆይቷል። የአይከል ከተማ አስተዳደር ዛሬ እንዳለው ከሆነ ከዚህ በኋላ በአካባቢው ግጭት እንዳከሰት ሕዝቡና የጸጥታ አካላት ከጠዋት እስከ ማታ፣ ከማታ እስከ ጠዋት ስምሪት አድርገው ይጠብቃሉ ብሏል።

የአማራ ክልል መንግሥት በጭልጋና አካባቢው ከሚነሱት ግጭቶች ጀርባ ህወሃት እንዳለበት በተደጋጋሚ ቢገልጽም፤ ህወሃት ግን በአማራ ክልል በሚነሱ ግጭቶች ላይ ግን ምንም ተሳትፎ እንደሌለው ይገልጻል። (አል ዐይን)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: operation dismantle tplf, qimant, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule