• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ

May 27, 2022 01:40 am by Editor Leave a Comment

በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን ጭልጋ ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ ሀብታሙ ፈለቀ የ55 ዓመት ጎልማሳ ሲሆኑ በአካባቢው በተደጋጋሚ የሚነሱት ግጭቶች ተረጋግተው እንዳይኖሩ ሲያደርጓቸው እንደቆዩ ይገልጻሉ።

በሌሎች ጊዜያት ከተነሱት ግጭቶች በላይ ባለፈው ዓመት ሚያዚያ 2013 ዓ.ም የተነሳው ግጭት አቶ ሀብታሙን ከመኖሪያ ቀያቸው እንዲፈናቀሉ እንዳደረጋቸው ገልጸዋል። ሚያዚያ 2013 ዓ.ም ግጭት ተነስቶ ንብረት ሲወድምና የሰው ህይወት ሲጠፋ አቶ ሀብታሙ አካባቢውን ለቀው ለመሄድ መነሳታቸውን ይናገራሉ።

አቶ ሀብታሙ የአማራ ብሔር ተወላጅ ሲሆኑ ቤት ንብረታቸውን ለቅማንት ብሔረሰብ ተወላጁ ጓደኛቸው አስረክበው ወደ ጎንደር ከተማ እንደመጡ ለአል ዐይን አማርኛ ገልጸዋል።

ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ በተደጋጋሚ ሲነሳ የነበረው ግጭት በማንነት ምክንያት ሆኖ ሳለ የአማራ ብሔር ተወላጅ የሆኑት አቶ ሀብታሙ ቤት ንብረታቸውን እንዲጠብቁላቸው አደራ የሰጡት ግን ለቅማንት ማህበረሰብ ተወላጁ ሀብቱ በላይ እንደሆነ ለአል ዐይን አማርኛ ተናግረዋል።

አል ዐይን አማርኛ፤ የጓደኛቸውን ቤት ላለፉት ወራት በአደራ መልክ ጠብቀው ያቆዩትና ትናንት ያስረከቡት አቶ ሀብቱ በላይ በስልክ አነጋግሯቸዋል። ላለፉት ወራት የጓደኛቸውን ቤት እንደራሳቸው አድርገው ከዘረፋና ከውድመት ሲጠብቁ መቆየታቸውን ተናግረዋል።

ግለሰቦች በዚህ ልክ አደራ የሚሰጣጡ ከሆነና የሚደማመጡ ከሆነ እንዴት በሁለቱ ወገኖች መካከል ግጭት ተከሰተ ሲል አል ዐይን ላቀረበው ጥያቄ አቶ ሀብቱ “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው፤ ቅማንት ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ቅዴፓ) የሚባል ቡድን የችግሩ ጠንሳሽ ነው” ሲሉ ነው የቅማንት ብሔረሰብ ተወላጁ የገለጹት።

ከስምንት ዓመት በፊት በማንነት ምክንያት እንደተነሱ በተገለጹ ግጭቶች አቶ ሀብታሙን ጨምሮ በርካቶች መፈናቀላቸው የሚታወስ ሲሆን፤ ከ 11 ሺህ በላይ የሚሆኑት ወደ ቀያቸው ተመልሰዋል ተብሏል።

ነዋሪዎቹ ወደ አይከል ሲመለሱ የከተማው ነዋሪዎች አቀባበል እንዳደረጉላቸው አቶ ሀብታሙ ተናግረዋል። አቶ ሀብታሙ ከተፈናቀሉበት አካባቢ ወደ ቀድሞ መኖሪያቸው ከመመለሳቸውም በላይ በአደራ መልክ የሰጡት ቤታቸውን እንደነበረ መቀበላቸውን ገልጸዋል።

በግለሰብና በህዝብ መካከል ምንም ችግር እንደሌለ የእርሳቸውና የአቶ ሀብቱ ንግግርና አደራ ማክበር ብቻውን ማሳያ እንደሚሆን ገልጸዋል።

ከአይከል ከተማ ተፈናቅለው የነበሩት ሌላኛው ግለሰብ አቶ ሽኩር መሐመድም ወደ ቀያቸው መመለሳቸውን ተናግረዋል። ወደ ከተማ ሲመለሱም ቤትና ንብረታቸውን በሰላም እንዳገኙት ለአል ዐይን አማርኛ ገልጸዋል።

አማራ እና ቅማንት በሚል ሕዝቡ እንዲጋጭ የተደረገው “የቅማንት ኮሚቴ” ተብሎ በሚጠራው ቡድን እንጅ በሕዝብ መካከል እንዳልሆነም ነው አቶ ሽኩር ያነሱት።

ወደ ቀያቸው የተመለሱት ተፈናቃዮች ጊዜያዊ ድጋፍ እና ዘላቂ ሰላም እንዲመጣ መንግሥት ሊሰራ እንደሚገባ አንስተዋል።

የአይከል ከተማ ሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት ሃላፊ መላኩ አለም አንተ ከአል ዐይን አማርኛ ጋር ባደረጉት ቆይታ በአካባቢው ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ በተከሰቱ ግጭቶች ከአካባቢ ርቀው የነበሩ ዜጎች ዛሬ አይከል ከተማ መግባታቸውን ለአል ዐይን አማርኛ አረጋግጠዋል።

አቶ መላኩ እንዳሉት ግጭቶቹ በተቀሰቀሱ ጊዜ አካባቢውን ለቀው ከተፈናቀሉ ዜጎች በተጨማሪም እጃቸው እንዳለበት የሚጠረጠሩም ወደ ከተማዋ መምጣታቸውን ተናግረዋል።

በግጭቶቹ እጃቸው እንዳበት የሚጠረጠሩ ዜጎች “መንግሥት በሚጠይቀን ለመጠየቅ ዝግጁ ነን” በማለት እጃቸውን ለመንግሥት እንደሰጡም ሃላፊው ለአል ዐይን አማርኛ ተናግረዋል።

ዜጎቹ ወደ አይከል ከተማ የተመለሱት አካባቢው ከግጭት ነጻ መሆኑ ለተፈናቃዮች በመገለጹ ሲሆን የከተማዋ ነዋሪዎችም የተፈናቀሉት ወገኖች እንዲመለሱ በመጠየቃቸው መሆኑ ተገልጿል።

በአማራ ብሔር እና በቅማንት ብሔረሰብ መካከል ግጭት እንዲነሳ ያደረገው ትህነግ መሆኑን አቶ መላኩ ገልጸዋል። አል ዐይን አማርኛ ግጭት ቀስቃሹ ትህነግ ስለመሆኑ ምን ማስረጃ እንዳላቸው የጠየቃቸው አቶ መላኩ፤ ለዚህ ማሳያ መኖሩን ገልጸው ዝርዝሩ ግን ለህግ የሚቀርብ እንደሆነ ገልጸዋል።

 “የቅማንት ኮሚቴ” በሚል ይጠራ የነበረው ቡድን ከትህነግ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት እንደነበረው ያነሱት ሃላፊው፣ የኮሚቴ አባላት ነን ያሉ አካላት ለህክምና በሚል ወደ ትግራይ መሄዳቸው መረጋገጡን አንስተዋል።

የኮሚቴው አባላት ህክምና መሄድ አስፈልጓቸው ከነበረ ቅርብ ወዳሉ የአማራ ክልል የጤና ተቋማት መሄድ ይችሉ እንደነበር የገለጹት አቶ መላኩ ወደ ትግራይ መሄዳቸው ከህወሃት ጋር ግንኑኘት እንዳላቸው ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።

የአይከል ከተማ ሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት ሃላፊ መላኩ አለም አንተ “የቅማንት ኮሚቴ” የሚባለው ቡድን ዓላማው ግጭት መፍጠር ነበር ያሉ ሲሆን፤ አሁን ግን በራሱ ጊዜ መፍረሱን ገልጸዋል።

ከዚህ በፊት የቅማንት ብሔረሰብ ተወካይ እንደሆኑ ገልጸው የነበሩ አካላት ቀበሌዎችን እንዲያስተዳድሩ ጥያቄ አቅርበው የክልሉ መንግሥት 42 ቀበሌዎችን እንዲያስተዳድሩ የፈቀደ ቢሆንም ተቃውሞ በመነሳቱ ምክንያት መጨረሻ ላይ 69 ቀበሌዎችን እንዲያስተዳድሩ ተፈቅዶ ነበር። ይሁንና ግጭቱ በዚህም ባለመቋጨቱ ላለፉት 8 ዓመታት ግጭት ሲከሰት ቆይቷል።

የክልል፣ ዞንና ከተማ አስተዳደር የሥራ ሃላፊዎች ከዚህ በኋላ ግጭቱ ዳግም እንዳይነሳ እየተሰራ መሆኑን ደጋግመው ገልጸው የነበረ ቢሆንም ችግሩ ግን ሳይፈታ ቆይቷል። የአይከል ከተማ አስተዳደር ዛሬ እንዳለው ከሆነ ከዚህ በኋላ በአካባቢው ግጭት እንዳከሰት ሕዝቡና የጸጥታ አካላት ከጠዋት እስከ ማታ፣ ከማታ እስከ ጠዋት ስምሪት አድርገው ይጠብቃሉ ብሏል።

የአማራ ክልል መንግሥት በጭልጋና አካባቢው ከሚነሱት ግጭቶች ጀርባ ህወሃት እንዳለበት በተደጋጋሚ ቢገልጽም፤ ህወሃት ግን በአማራ ክልል በሚነሱ ግጭቶች ላይ ግን ምንም ተሳትፎ እንደሌለው ይገልጻል። (አል ዐይን)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: operation dismantle tplf, qimant, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule