• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ

May 27, 2022 01:40 am by Editor Leave a Comment

በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን ጭልጋ ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ ሀብታሙ ፈለቀ የ55 ዓመት ጎልማሳ ሲሆኑ በአካባቢው በተደጋጋሚ የሚነሱት ግጭቶች ተረጋግተው እንዳይኖሩ ሲያደርጓቸው እንደቆዩ ይገልጻሉ።

በሌሎች ጊዜያት ከተነሱት ግጭቶች በላይ ባለፈው ዓመት ሚያዚያ 2013 ዓ.ም የተነሳው ግጭት አቶ ሀብታሙን ከመኖሪያ ቀያቸው እንዲፈናቀሉ እንዳደረጋቸው ገልጸዋል። ሚያዚያ 2013 ዓ.ም ግጭት ተነስቶ ንብረት ሲወድምና የሰው ህይወት ሲጠፋ አቶ ሀብታሙ አካባቢውን ለቀው ለመሄድ መነሳታቸውን ይናገራሉ።

አቶ ሀብታሙ የአማራ ብሔር ተወላጅ ሲሆኑ ቤት ንብረታቸውን ለቅማንት ብሔረሰብ ተወላጁ ጓደኛቸው አስረክበው ወደ ጎንደር ከተማ እንደመጡ ለአል ዐይን አማርኛ ገልጸዋል።

ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ በተደጋጋሚ ሲነሳ የነበረው ግጭት በማንነት ምክንያት ሆኖ ሳለ የአማራ ብሔር ተወላጅ የሆኑት አቶ ሀብታሙ ቤት ንብረታቸውን እንዲጠብቁላቸው አደራ የሰጡት ግን ለቅማንት ማህበረሰብ ተወላጁ ሀብቱ በላይ እንደሆነ ለአል ዐይን አማርኛ ተናግረዋል።

አል ዐይን አማርኛ፤ የጓደኛቸውን ቤት ላለፉት ወራት በአደራ መልክ ጠብቀው ያቆዩትና ትናንት ያስረከቡት አቶ ሀብቱ በላይ በስልክ አነጋግሯቸዋል። ላለፉት ወራት የጓደኛቸውን ቤት እንደራሳቸው አድርገው ከዘረፋና ከውድመት ሲጠብቁ መቆየታቸውን ተናግረዋል።

ግለሰቦች በዚህ ልክ አደራ የሚሰጣጡ ከሆነና የሚደማመጡ ከሆነ እንዴት በሁለቱ ወገኖች መካከል ግጭት ተከሰተ ሲል አል ዐይን ላቀረበው ጥያቄ አቶ ሀብቱ “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው፤ ቅማንት ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ቅዴፓ) የሚባል ቡድን የችግሩ ጠንሳሽ ነው” ሲሉ ነው የቅማንት ብሔረሰብ ተወላጁ የገለጹት።

ከስምንት ዓመት በፊት በማንነት ምክንያት እንደተነሱ በተገለጹ ግጭቶች አቶ ሀብታሙን ጨምሮ በርካቶች መፈናቀላቸው የሚታወስ ሲሆን፤ ከ 11 ሺህ በላይ የሚሆኑት ወደ ቀያቸው ተመልሰዋል ተብሏል።

ነዋሪዎቹ ወደ አይከል ሲመለሱ የከተማው ነዋሪዎች አቀባበል እንዳደረጉላቸው አቶ ሀብታሙ ተናግረዋል። አቶ ሀብታሙ ከተፈናቀሉበት አካባቢ ወደ ቀድሞ መኖሪያቸው ከመመለሳቸውም በላይ በአደራ መልክ የሰጡት ቤታቸውን እንደነበረ መቀበላቸውን ገልጸዋል።

በግለሰብና በህዝብ መካከል ምንም ችግር እንደሌለ የእርሳቸውና የአቶ ሀብቱ ንግግርና አደራ ማክበር ብቻውን ማሳያ እንደሚሆን ገልጸዋል።

ከአይከል ከተማ ተፈናቅለው የነበሩት ሌላኛው ግለሰብ አቶ ሽኩር መሐመድም ወደ ቀያቸው መመለሳቸውን ተናግረዋል። ወደ ከተማ ሲመለሱም ቤትና ንብረታቸውን በሰላም እንዳገኙት ለአል ዐይን አማርኛ ገልጸዋል።

አማራ እና ቅማንት በሚል ሕዝቡ እንዲጋጭ የተደረገው “የቅማንት ኮሚቴ” ተብሎ በሚጠራው ቡድን እንጅ በሕዝብ መካከል እንዳልሆነም ነው አቶ ሽኩር ያነሱት።

ወደ ቀያቸው የተመለሱት ተፈናቃዮች ጊዜያዊ ድጋፍ እና ዘላቂ ሰላም እንዲመጣ መንግሥት ሊሰራ እንደሚገባ አንስተዋል።

የአይከል ከተማ ሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት ሃላፊ መላኩ አለም አንተ ከአል ዐይን አማርኛ ጋር ባደረጉት ቆይታ በአካባቢው ከ2006 ዓ.ም ጀምሮ በተከሰቱ ግጭቶች ከአካባቢ ርቀው የነበሩ ዜጎች ዛሬ አይከል ከተማ መግባታቸውን ለአል ዐይን አማርኛ አረጋግጠዋል።

አቶ መላኩ እንዳሉት ግጭቶቹ በተቀሰቀሱ ጊዜ አካባቢውን ለቀው ከተፈናቀሉ ዜጎች በተጨማሪም እጃቸው እንዳለበት የሚጠረጠሩም ወደ ከተማዋ መምጣታቸውን ተናግረዋል።

በግጭቶቹ እጃቸው እንዳበት የሚጠረጠሩ ዜጎች “መንግሥት በሚጠይቀን ለመጠየቅ ዝግጁ ነን” በማለት እጃቸውን ለመንግሥት እንደሰጡም ሃላፊው ለአል ዐይን አማርኛ ተናግረዋል።

ዜጎቹ ወደ አይከል ከተማ የተመለሱት አካባቢው ከግጭት ነጻ መሆኑ ለተፈናቃዮች በመገለጹ ሲሆን የከተማዋ ነዋሪዎችም የተፈናቀሉት ወገኖች እንዲመለሱ በመጠየቃቸው መሆኑ ተገልጿል።

በአማራ ብሔር እና በቅማንት ብሔረሰብ መካከል ግጭት እንዲነሳ ያደረገው ትህነግ መሆኑን አቶ መላኩ ገልጸዋል። አል ዐይን አማርኛ ግጭት ቀስቃሹ ትህነግ ስለመሆኑ ምን ማስረጃ እንዳላቸው የጠየቃቸው አቶ መላኩ፤ ለዚህ ማሳያ መኖሩን ገልጸው ዝርዝሩ ግን ለህግ የሚቀርብ እንደሆነ ገልጸዋል።

 “የቅማንት ኮሚቴ” በሚል ይጠራ የነበረው ቡድን ከትህነግ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት እንደነበረው ያነሱት ሃላፊው፣ የኮሚቴ አባላት ነን ያሉ አካላት ለህክምና በሚል ወደ ትግራይ መሄዳቸው መረጋገጡን አንስተዋል።

የኮሚቴው አባላት ህክምና መሄድ አስፈልጓቸው ከነበረ ቅርብ ወዳሉ የአማራ ክልል የጤና ተቋማት መሄድ ይችሉ እንደነበር የገለጹት አቶ መላኩ ወደ ትግራይ መሄዳቸው ከህወሃት ጋር ግንኑኘት እንዳላቸው ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።

የአይከል ከተማ ሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት ሃላፊ መላኩ አለም አንተ “የቅማንት ኮሚቴ” የሚባለው ቡድን ዓላማው ግጭት መፍጠር ነበር ያሉ ሲሆን፤ አሁን ግን በራሱ ጊዜ መፍረሱን ገልጸዋል።

ከዚህ በፊት የቅማንት ብሔረሰብ ተወካይ እንደሆኑ ገልጸው የነበሩ አካላት ቀበሌዎችን እንዲያስተዳድሩ ጥያቄ አቅርበው የክልሉ መንግሥት 42 ቀበሌዎችን እንዲያስተዳድሩ የፈቀደ ቢሆንም ተቃውሞ በመነሳቱ ምክንያት መጨረሻ ላይ 69 ቀበሌዎችን እንዲያስተዳድሩ ተፈቅዶ ነበር። ይሁንና ግጭቱ በዚህም ባለመቋጨቱ ላለፉት 8 ዓመታት ግጭት ሲከሰት ቆይቷል።

የክልል፣ ዞንና ከተማ አስተዳደር የሥራ ሃላፊዎች ከዚህ በኋላ ግጭቱ ዳግም እንዳይነሳ እየተሰራ መሆኑን ደጋግመው ገልጸው የነበረ ቢሆንም ችግሩ ግን ሳይፈታ ቆይቷል። የአይከል ከተማ አስተዳደር ዛሬ እንዳለው ከሆነ ከዚህ በኋላ በአካባቢው ግጭት እንዳከሰት ሕዝቡና የጸጥታ አካላት ከጠዋት እስከ ማታ፣ ከማታ እስከ ጠዋት ስምሪት አድርገው ይጠብቃሉ ብሏል።

የአማራ ክልል መንግሥት በጭልጋና አካባቢው ከሚነሱት ግጭቶች ጀርባ ህወሃት እንዳለበት በተደጋጋሚ ቢገልጽም፤ ህወሃት ግን በአማራ ክልል በሚነሱ ግጭቶች ላይ ግን ምንም ተሳትፎ እንደሌለው ይገልጻል። (አል ዐይን)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: operation dismantle tplf, qimant, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule