• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ

June 28, 2022 01:07 pm by Editor Leave a Comment

የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ትህነግ)ን ማንነት የማያውቅ አንድም በሟቾች ይሸቅጣል፤ በደማቸው የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ይጣጣራል፤ ወይም ያወቀ መስሎት ይለፈልፋል፣ ይዘልፋል፣ ይዘፍናል።

ትህነግ ከአፈጣጠሩ ጀምሮ ምህረት የማያውቅ እንደሆነ “ነጻ አወጣሃለው” ባለው ሕዝብ ላይ ለዓመታት የፈጸመውን መመልከት በቂ ነበር። ስለምንረሳና እንደምረሳ ስለሚያውቅ ገድሎ ሙሾ አውራጅ ሆኖ ይመጣል። ጨፍጭፎን ስለ ሰላም ልደራደር ይላል።

በወለጋ የተከሰተውንና መቼም የማይረሳውን አረመኔያዊ ጭፍጨፋ በትህነግ ልክ ያለ አካል እና እርሱ አቡክቶ ጋግሮ የሠራው ኦነህ ሸኔ ካልሆነ ማንም ሊያደርገው እንደማይችል መገመት የማይችል ገና የኢትዮጵያ ፖለቲካ ያልገባው የፖለቲካ ሕጻን ነውና አርፎ ተቀምጦ ይማር። ሌሎች ግን አሉ አዛኝ መስለው አጀንዳ የሚፈጽሙ። ባደባባይ ከሰቆቃው ሰለባ በላይ ያለቅሳሉ፤ ከዚያ መልስ “አባላናቸው” እያሉ ከጣሪያ በላይ ይስቁብናል፣ በጅልነታችን ይሳለቁብናል።

እጅግ ልብ የሚሰብረውን የአቶ መሐመድን ሰቆቃ አል-ዐይን አስነብቦናል፤ ለታሪክ እናሰቀምጠው።

አቶ መሀመድ የሱፍ ሙሄ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ጊምቢ ወረዳ ነዋሪ ሲሆኑ ዕድሜያቸውን በትክክል እንደማያውቁት ይናገራሉ፡፡ 

የቶሌ ቀበሌ ነዋሪው አቶ መሐመድ 22 ቤተሰብ በአንድ ቀን እንደተገደለባቸው ለአል ዐይን አማርኛ ተናግረዋል፡፡ ከተገደሉባቸው ቤተሰቦቻቸው መካከል ከወለደች አራት ቀን የሆናት እመጫት ልጃቸው አንዷ መሆኗን ገልጸዋል፡፡

አቶ መሐመድ የሱፍ የአራት ቀን እመጫት ልጃቸው ከእነ ልጇ በጥይት መገደሏን ያነሱ ሲሆን፤ ገዳዮቹ ህጻኗን እንኳን አለመተዋቸው እጅግ እንዳሳዘናቸው ገልጸዋል፡፡ 

አቶ መሐመድ ልጆቻቸው ከነልጅ ልጆቻቸው መገደላቸውን የገለጹ ሲሆን የመጀመሪያና ሶስተኛ ልጆቻቸው እስከ ልጅ ልጆቻቸው አምስት፤ አምስት ሆነው መገደላቸውን ተናግረዋል፡፡ 

ሁለተኛዋ ልጃቸው ከሶስት ልጆቿ ጋር፤ እመጫቷ ልጃቸው ከሁለት ልጆቿ ጋር፤ ሌላኛዋ ልጃቸው ከአንድ ልጇ ጋር እንደተገደሉባቸው አቶ መሐመድ ለአል ዐይን አማርኛ በስልክ ተናግረዋል፡፡ በቅርቡ የተዳረችው የአቶ መሐመድ ልጅ እንዲሁም አንድ ወንድ ልጅም እንደተገደሉባቸው ነው የገለጹት፡፡

አቶ መሐመድ በአጠቃላይ ስድስት ልጆቻቸው እና 16 የልጅ ልጆቻቸው መገደላቸውን የገለጹ ሲሆን የቀበሯቸውም እራሳቸው እንደሆኑ ገልጸዋል፡፡ አሁን ላይ አዛውንቱ እናታቸውም አባታቸውም የተገደሉባቸውን ሰባት ልጆች ይዘው እዛው ቶሌ ቀበሌ መቀመጣቸውንና መሸሽ አለመቻላቸውን ገልጸዋል፡፡ 

አቶ መሐመድ በታጣቂዎች እንደተገደሉባቸው የጠቀሷቸውን ሁሉንም እራሳቸው እንደቀበሩ ገልጸዋል፡፡ ሃዘንተኛው አዛውንት የራሳቸውን ቤተሰቦችን ጨምሮ በአጠቃላይ 60 ሰዎችን መቅበራቸውን ይናገራሉ፡፡ 

“የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች የቀበርኩት እኔ ነኝ፤ በእኔ እጅ ነው የተቀበሩት ማንም አልቀበረልኝም፤ እኔ እራሴ ነኝ የቀበርኳቸው” ሲሉም ይናገራሉ አቶ መሐመድ፡፡ ከሟቾች ባለፈም የቆሰሉ ስድስት ልጆች እንዳሏቸው ገልጸዋል፡፡ አንደኛዋ ልጃቸው አዲስ አበባ ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እንደሄደች ገልጸዋል፡፡ አዲስ አበባ የሄደችው ልጃቸውእግሯ ይቆረጥ አይቆረጥ እየተባለ እንደሆነ ያነሱት አዛውንቱ የሟቾችን ስም ዝርዝር መናገር እንደሚችሉም ነው የገለጹት፡፡ 

የአቶ መሐመድ የሱፍ ሙሄ 22 የቤተሰብ አባላትን ካሳጣቸው ግድያ የተረፉት በቆሎ ማሳ ውስጥ ገብተው እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ እርሳቸው በቆሎ ማሳ ውስጥ ገብተው የተደበቁት ገዳዮቹ ሴት እና ልጅ “አይገድሉም” በሚል ግምት እንደሆነ ለአል ዐይን አማርኛ ገልጸዋል፡፡

የአቶ መሐመድ የሱፍ ሙሄ ጓደኛዬ መሐመድ አሊ በበኩላቸው የልጃቸው ሚስት ከነልጇ እንደተገደለች ያነሱ ሲሆን ጓደኛቸው አቶ መሐመድ የሱፍ ግን 22 ቤተሰቦቻቸውን ማጣታቸውን ለአል ዐይን አማርኛ ተናግረዋል፡፡

ጥቃት አድራሾቹን ያውቋቸው እንደሆነ የጠየቅናቸው አቶ መሐመድ ከግድያው በፊት ወደ ደምቢዶሎ በቶሌ ቀበሌ ማለፋቸውንና ምግብም ጠይቀው እንደነበር ገልጸዋል፡፡ ጥቃቱ ሲፈጸም ወንዶች በብዛት ወደ ስራ ሄደው እንደነበርአቶ መሀመድ ገልጸዋል፡፡ 

አሁን ላይ እናታቸውና አባታቸው የተገደሉባቸውን ሰባትት ፤ አባታቸው የተገደለባቸው አምስት በድምሩ 12 የልጅ ልጆች ይዘው ግራ በመጋባት መቀመጣቸውን የገለጹት አቶ መሐመድ የፌዴራልም የክልል ባለስልጣናት መጥተው እንዳልጠየቋቸው ተናግረዋል፡፡

በምዕራብ ወለጋ ዞን ቶሌ ቀበሌ በተፈጸመ ጭፍጨፋ የሟቾች ቁጥር 2 ሺ እንደሚደርስ አቶ መሐመድ ገልጸዋል፡፡ 

በምዕራብ ወለጋው ግድያ ላይ አስተያየት እንዲሰጡን ለኦሮሚያ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ተደጋጋሚ የስልክ ሙከራ ብናደርግም ማግኘት ባለመቻላችን ሃሳባቸውን ማካተት አልቻልንም፡፡ 

የፈዴራል መንግስት ግድያ በተደረገበት አካባቢ የሕግ ማስከበር ስራ እየሰራ መሆኑን የገለጸ ሲሆን የአማራ እና ኦሮሚያ ክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች “አሸባሪዎችን ለማጥፋት በጋራ እንሠራለን” ብለዋል፡፡

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: News, Right Column Tagged With: ethiopian terrorists, olf shanee, olf shine, operation dismantle tplf, rapist tplf, tplf terrorist, wollega

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule