• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ

June 28, 2022 01:07 pm by Editor Leave a Comment

የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ትህነግ)ን ማንነት የማያውቅ አንድም በሟቾች ይሸቅጣል፤ በደማቸው የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ይጣጣራል፤ ወይም ያወቀ መስሎት ይለፈልፋል፣ ይዘልፋል፣ ይዘፍናል።

ትህነግ ከአፈጣጠሩ ጀምሮ ምህረት የማያውቅ እንደሆነ “ነጻ አወጣሃለው” ባለው ሕዝብ ላይ ለዓመታት የፈጸመውን መመልከት በቂ ነበር። ስለምንረሳና እንደምረሳ ስለሚያውቅ ገድሎ ሙሾ አውራጅ ሆኖ ይመጣል። ጨፍጭፎን ስለ ሰላም ልደራደር ይላል።

በወለጋ የተከሰተውንና መቼም የማይረሳውን አረመኔያዊ ጭፍጨፋ በትህነግ ልክ ያለ አካል እና እርሱ አቡክቶ ጋግሮ የሠራው ኦነህ ሸኔ ካልሆነ ማንም ሊያደርገው እንደማይችል መገመት የማይችል ገና የኢትዮጵያ ፖለቲካ ያልገባው የፖለቲካ ሕጻን ነውና አርፎ ተቀምጦ ይማር። ሌሎች ግን አሉ አዛኝ መስለው አጀንዳ የሚፈጽሙ። ባደባባይ ከሰቆቃው ሰለባ በላይ ያለቅሳሉ፤ ከዚያ መልስ “አባላናቸው” እያሉ ከጣሪያ በላይ ይስቁብናል፣ በጅልነታችን ይሳለቁብናል።

እጅግ ልብ የሚሰብረውን የአቶ መሐመድን ሰቆቃ አል-ዐይን አስነብቦናል፤ ለታሪክ እናሰቀምጠው።

አቶ መሀመድ የሱፍ ሙሄ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ወለጋ ዞን ጊምቢ ወረዳ ነዋሪ ሲሆኑ ዕድሜያቸውን በትክክል እንደማያውቁት ይናገራሉ፡፡ 

የቶሌ ቀበሌ ነዋሪው አቶ መሐመድ 22 ቤተሰብ በአንድ ቀን እንደተገደለባቸው ለአል ዐይን አማርኛ ተናግረዋል፡፡ ከተገደሉባቸው ቤተሰቦቻቸው መካከል ከወለደች አራት ቀን የሆናት እመጫት ልጃቸው አንዷ መሆኗን ገልጸዋል፡፡

አቶ መሐመድ የሱፍ የአራት ቀን እመጫት ልጃቸው ከእነ ልጇ በጥይት መገደሏን ያነሱ ሲሆን፤ ገዳዮቹ ህጻኗን እንኳን አለመተዋቸው እጅግ እንዳሳዘናቸው ገልጸዋል፡፡ 

አቶ መሐመድ ልጆቻቸው ከነልጅ ልጆቻቸው መገደላቸውን የገለጹ ሲሆን የመጀመሪያና ሶስተኛ ልጆቻቸው እስከ ልጅ ልጆቻቸው አምስት፤ አምስት ሆነው መገደላቸውን ተናግረዋል፡፡ 

ሁለተኛዋ ልጃቸው ከሶስት ልጆቿ ጋር፤ እመጫቷ ልጃቸው ከሁለት ልጆቿ ጋር፤ ሌላኛዋ ልጃቸው ከአንድ ልጇ ጋር እንደተገደሉባቸው አቶ መሐመድ ለአል ዐይን አማርኛ በስልክ ተናግረዋል፡፡ በቅርቡ የተዳረችው የአቶ መሐመድ ልጅ እንዲሁም አንድ ወንድ ልጅም እንደተገደሉባቸው ነው የገለጹት፡፡

አቶ መሐመድ በአጠቃላይ ስድስት ልጆቻቸው እና 16 የልጅ ልጆቻቸው መገደላቸውን የገለጹ ሲሆን የቀበሯቸውም እራሳቸው እንደሆኑ ገልጸዋል፡፡ አሁን ላይ አዛውንቱ እናታቸውም አባታቸውም የተገደሉባቸውን ሰባት ልጆች ይዘው እዛው ቶሌ ቀበሌ መቀመጣቸውንና መሸሽ አለመቻላቸውን ገልጸዋል፡፡ 

አቶ መሐመድ በታጣቂዎች እንደተገደሉባቸው የጠቀሷቸውን ሁሉንም እራሳቸው እንደቀበሩ ገልጸዋል፡፡ ሃዘንተኛው አዛውንት የራሳቸውን ቤተሰቦችን ጨምሮ በአጠቃላይ 60 ሰዎችን መቅበራቸውን ይናገራሉ፡፡ 

“የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች የቀበርኩት እኔ ነኝ፤ በእኔ እጅ ነው የተቀበሩት ማንም አልቀበረልኝም፤ እኔ እራሴ ነኝ የቀበርኳቸው” ሲሉም ይናገራሉ አቶ መሐመድ፡፡ ከሟቾች ባለፈም የቆሰሉ ስድስት ልጆች እንዳሏቸው ገልጸዋል፡፡ አንደኛዋ ልጃቸው አዲስ አበባ ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እንደሄደች ገልጸዋል፡፡ አዲስ አበባ የሄደችው ልጃቸውእግሯ ይቆረጥ አይቆረጥ እየተባለ እንደሆነ ያነሱት አዛውንቱ የሟቾችን ስም ዝርዝር መናገር እንደሚችሉም ነው የገለጹት፡፡ 

የአቶ መሐመድ የሱፍ ሙሄ 22 የቤተሰብ አባላትን ካሳጣቸው ግድያ የተረፉት በቆሎ ማሳ ውስጥ ገብተው እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ እርሳቸው በቆሎ ማሳ ውስጥ ገብተው የተደበቁት ገዳዮቹ ሴት እና ልጅ “አይገድሉም” በሚል ግምት እንደሆነ ለአል ዐይን አማርኛ ገልጸዋል፡፡

የአቶ መሐመድ የሱፍ ሙሄ ጓደኛዬ መሐመድ አሊ በበኩላቸው የልጃቸው ሚስት ከነልጇ እንደተገደለች ያነሱ ሲሆን ጓደኛቸው አቶ መሐመድ የሱፍ ግን 22 ቤተሰቦቻቸውን ማጣታቸውን ለአል ዐይን አማርኛ ተናግረዋል፡፡

ጥቃት አድራሾቹን ያውቋቸው እንደሆነ የጠየቅናቸው አቶ መሐመድ ከግድያው በፊት ወደ ደምቢዶሎ በቶሌ ቀበሌ ማለፋቸውንና ምግብም ጠይቀው እንደነበር ገልጸዋል፡፡ ጥቃቱ ሲፈጸም ወንዶች በብዛት ወደ ስራ ሄደው እንደነበርአቶ መሀመድ ገልጸዋል፡፡ 

አሁን ላይ እናታቸውና አባታቸው የተገደሉባቸውን ሰባትት ፤ አባታቸው የተገደለባቸው አምስት በድምሩ 12 የልጅ ልጆች ይዘው ግራ በመጋባት መቀመጣቸውን የገለጹት አቶ መሐመድ የፌዴራልም የክልል ባለስልጣናት መጥተው እንዳልጠየቋቸው ተናግረዋል፡፡

በምዕራብ ወለጋ ዞን ቶሌ ቀበሌ በተፈጸመ ጭፍጨፋ የሟቾች ቁጥር 2 ሺ እንደሚደርስ አቶ መሐመድ ገልጸዋል፡፡ 

በምዕራብ ወለጋው ግድያ ላይ አስተያየት እንዲሰጡን ለኦሮሚያ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ተደጋጋሚ የስልክ ሙከራ ብናደርግም ማግኘት ባለመቻላችን ሃሳባቸውን ማካተት አልቻልንም፡፡ 

የፈዴራል መንግስት ግድያ በተደረገበት አካባቢ የሕግ ማስከበር ስራ እየሰራ መሆኑን የገለጸ ሲሆን የአማራ እና ኦሮሚያ ክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች “አሸባሪዎችን ለማጥፋት በጋራ እንሠራለን” ብለዋል፡፡

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: ethiopian terrorists, olf shanee, olf shine, operation dismantle tplf, rapist tplf, tplf terrorist, wollega

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule