በመጀመሪያ ደረጃ መተማመን ያለብህ በራስህ አቅም ነው። አቅም አልባ ከሆንክ ማንም የማይፈልግህ ውዳቂ ትሆናለህ። የራስህን አቅም በሚገባ ከገመገምክ በኋላ ማን ነው አጋሬ ወደሚለው ትዞራለህ። አጋርህ ከጠላትህ እና ከአንተ ጋር ያለውን መስተጋብር ትገመግማለህ። አጋርህ ከጠላትህ ይልቅ አንተን ለምን እንደመረጠ አንተም ለምን እንደመረጥከው በተጨባጭ መረጃ ላይ ተንተርሰህ መገምገም የአንተ ድርሻ ነው። አንተም ለምን አጋርህ እንዳደረከው ማወቅ ይኖርብሃል። ታማኝ አጋር እንደምትሻ ሁሉ ለአጋርህ ታማኝ መሆንም የግድ ነው። እዚህም እዚያም የምትዘል ከሆነ ለአጋርነት አትመጥንም ብሎ ሜዳ ላይ ያሰጣሃል አንዳንዴ የጠላቴ ጠላት አጋሬ ነው የሚለው ብሂል ገዥ ነው። ዘላቂ ጠላትም ሆነ ዘላቂ ወዳጅ እንደሌለ ተረድተህ ግምገማህን በየጊዜው መተንተን ግን ከአንተ የሚጠበቅ ነው። ያልተተነተነ ፖለቲካ … [Read more...] about የፕሪቶሪያው ስምምነት ትርጉም 360 ለዞረባችሁ
tplf terrorist
ጥቅምት 24 “የክህደት ቀን” ተብሎ በግንቦት 20 መቃብር ላይ ይተከልልን!
በራሳቸው ሕዝብ ላይ ሲደርስ ሰማይ የሚደፋባቸውና ዓለም ሁሉ አብሯቸው እንዲያለቅስ የሚፈልጉት ምዕራባውያን በሌሎች ላይ ለሚደርሰው ሰቆቃ ቅንጣት ታህል ግድ አይላቸውም። አንድ ማሳያ እንጥቀስ፤ የዛሬ 80 ዓመት አካባቢ ጃፓን የአሜሪካንን ድንበር ጥሳ ከሐዋይ ደሴቶች አንደኛዋ ላይ የሚገኘውን ወታደራዊውን የፐርል ወደብ ገና በጠዋቱ በድንገት አጠቃች፤ በወደቡ ላይ የነበሩት 8 መርከቦች ጉዳት ደረሰባቸው፤ አራቱ ሰጠሙ፤ በአጠቃላይ ወደ 20 የሚደርሱ መርከቦችና ጀልባዎች ከጥቅም ውጪ ሆኑ፤ ከ300 በላይ የሚሆኑ አውሮፕላኖች፣ ጀቶችና ሔሊኮፕተሮች ከፍተኛ ጉዳት ደረሰባቸው፤ ከሁሉ በላይ ከ2,400 በላይ የሚሆኑ ባሕረኞች፣ ወታደሮችና ሰላማዊ ሰዎች ሕይወታቸውን አጡ፤ ከ1,000 በላይ የሚሆኑ ደግሞ ቆሰሉ። በቀጣዩ ቀን ዲሴምበር 8፣ 1941 የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ፍራንክሊን ሩዝቬልት … [Read more...] about ጥቅምት 24 “የክህደት ቀን” ተብሎ በግንቦት 20 መቃብር ላይ ይተከልልን!
የአማራ ሕዝብ በይፋ ይቅርታ ሊጠየቅ ይገባዋል!
አሸባሪው ትህነግ ትጥቅ ይፍታ ተብሏል። አባላቱና ደጋፊዎቹ ትጥቅ አንፈታም እያሉ ነው። እፈታለሁ ቢል እንኳን ትህነግ ትጥቅ ዘርፎ ሲደብቅ የኖረ ድርጅት ነው። የትህነግ ዋናው ትጥቅ ግን የጦር መሳርያ አይደለም። የትህነግ የነፍስ መከፍ፣ የቡድን፣ ከባድ መሳርያው ፀረ አማራ ጥላቻ ነው። እስካሁን የፈፀመው ውድመት በፀረ አማራ ትርክት የተፈፀመ ነው። 1) አሸባሪው ትህነግ ተመስርቶ፣ የጎለመሰው በአማራ ጥላቻ ነው። በግላጭ አማራን የሚረግም ማንፌስቶ አርቅቆ፣ አባላቱን ብቻ ሳይሆን ህዝብን ወዝ የጠገበ ጥላቻ አስታጥቋል። ይህን ትጥቅ መፍታት አለበት። ይህ ትጥቅ የሚፈታው የአማራን ህዝብ ይቅርታ በመጠየቅ ነው። 2) የትህነግ ፀረ አማራ ጥላቻ ለአማራ ህዝብ ብቻ የተወሰነ አይደለም። ፀረ ኢትዮጵያም ነው። የኢትዮጵያ ታሪክን ከአማራ ጥላቻ ጋር አጋምዶ ኢትዮጵያን ቅኝ ገዥ አድርጓ … [Read more...] about የአማራ ሕዝብ በይፋ ይቅርታ ሊጠየቅ ይገባዋል!
ከ300 ሺህ ዶላር በላይ ወደ ውጭ ሃገር ለማስወጣት የሞከረ አሽከርካሪ ተያዘ
በአዳማ ከተማ ከ300 ሺህ ዶላር በላይ ወደ ውጭ ሃገር ለማስወጣት የሞከረ አሽከርካሪ መያዙን የከተማዋ ፖሊስ መመሪያ አስታወቀ። አሽከርካሪው የተያዘው ኮድ 3/89158 ኢ.ት በሆነ ሎቤድ መኪና ገንዘቡን ከአዲስ አበባ ወደ ጅቡቲ በስውር ደብቆ ሲያጓጉዝ ነው።በአዳማ ከተማ ዳቤ ክፍለ ከተማ ዳቤ ሶሎቄ ልዩ ቦታው ኬላ ፍተሻ ላይ የተያዘው የገንዘብ መጠንም 302ሺህ 400 የአሜሪካን ዶላር መሆኑን 2015የመመሪያው የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ ምክትል እንስፔክተር ወርቅነሽ ገልሜቻ ገልጸዋል።በብሔራዊ ደህንነትና በአዳማ ከተማ የፀጥታ ሃይሎች ትብብር በ23/2/2015 ዓ.ም ከቀኑ 11:00 ላይ የተያዘው ይሄ ገንዘብ ወደ ውጭ ሃገር በሚጓዝ የኮንቴይነር ጭነት ስር በስውር ቦታ ተደብቆ መሆኑንና አሽከርካሪውም በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን ነው ያስረዱት። (Tikvah) ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about ከ300 ሺህ ዶላር በላይ ወደ ውጭ ሃገር ለማስወጣት የሞከረ አሽከርካሪ ተያዘ
ባለፉት ሦስት ወራት የተያዘ ህገ ወጥ ሲሚንቶና ነዳጅ
በመጀመሪያው ሩብ ዓመት በህገ ወጥ መልኩ ሲዘዋወር የነበረ ከ71 ሺህ ኩንታል በላይ ሲሚንቶ እና 500,153 ሊትር ነዳጅ ተይዟል። በዚህም መሰረት፦- በአዲስ አበባ 54,976 ኩንታል ሲሚንቶ- በኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት 14,094 ኩንታል ሲሚንቶ፣ እና 49,520 ሊትር ነዳጅ- በአማራ ክልላዊ መንግስት 1,914 ኩንታል እና 39,8505 ሊትር ነዳጅ- በሶማሌ ክልላዊ መንግስት 530 ኩንታል እና 12,560 ሊትር ነዳጅ- በደቡብ ምዕራብ 39,568 ሊትር ነዳጅ በድምሩ 71,514 ኩንታል ሲሚንቶ እና 500,153 ሊትር ነዳጅ በህገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወር ተገኘቶ በህገ ወጥ አካላት ላይም አስተዳደራዊ እርምጃ ተወስዶባቸዋል፡፡ በዚህ ህገ-ወጥ ድርጊት ላይ ተሳተፎ ባደረጉ አካላት ላይ ድርጅት የማሸግ እንዲሁም ምርት የመውረስ … [Read more...] about ባለፉት ሦስት ወራት የተያዘ ህገ ወጥ ሲሚንቶና ነዳጅ
ክብር ለጀግኖቻችን!
ትህነግ አሸንፎ ቢሆን ኖሮ … ድርድሩ የተደረገው ትህነግ ደብረብርሃንን፣ ባህርዳርን፣ ጎንደርን ይዞ ቢሆን ኖሮ ትጥቅ ይፍታ ይባል የነበረው ጥምር ጦሩ ነበር። ክብር ለጀግኖቻችን ይሁንና ድርድሩ የተደረገው ባለፈው አመት ምዕራባውያን ዲፕሎማቶቻቸውን ባስወጡበት ወቅት ቢሆን ኖሮ ጥምር ጦሩ ያለ እንቅፋት ወደ መቀሌ ይግባ ሳይሆን፣ ትህነግ ወደ አዲስ አበባ ይግባ ነበር የሚባለው። ክብር ለጀግኖቻችን ይሁንና፣ አምና ትህነግ እንደወረረን የባሰ ገፍቶ ቢሆን ኖሮ የጊዜያዊ አስተዳዳሪ መዳቢው ትህነግ ነበር። ያውም እንደህዝብ እንድንኖር ከፈቀደልን። ክብር ለጀግኖቻችን ይሁንና እንደ ጠላቶቻችን ቢሆን ኖሮ የትህነግ ጀኔራሎች ነበሩ ትጥቅ አስፈችዎች። ክብር ለጀግኖቻችንና ወልዲያና፣ ላሊበላን፣ ጋሸናና ደባርቅን ይዘው አልተደራደሩም። ክብር ለጀግኖቻችን ይሁንና አላማጣ … [Read more...] about ክብር ለጀግኖቻችን!
መንግሥት መሠረተ ቢስ ውንጀላዎችን ፈጽሞ እንደማይታገስ አስታወቀ
”የሰብአዊ መብት ባለሙያዎች ኮሚሽን ኢትዮጵያ ላይ ጫና ማሳደር የተቋቋመ ስብስብ ነው” ሲሉ አምባሳደር ታዬ ኃላፊነት የጎደላቸው አካላት ለአደገኛ የፖለቲካ አጀንዳ ሲባል እየፈጠሯቸው የሚገኙ መሠረተ ቢስ ውንጀላዎችን ኢትዮጵያ ታወግዛለችበምዕራባውያን የተለያዩ አካላት አማካኝነት በኢትዮጵያ ላይ የሚነዙ የሐሰት ስም ማጥፋቶችን የኢትዮጵያ መንግሥት ፈጽሞ አይታገሥም። እነዚህ አካላት ኢትዮጵያ ውስጥ የከፉ ወንጀሎች ሊፈጸሙ ይችላሉ በሚል የሕወሐትን ጊዜ ያለፈበት ፕሮፓጋንዳ እንደ በቀቀንመድገማቸው አሳፋሪ ነው። እነዚህ አካላት የሚከሱት ፍንጮችን ወይም ተጨባጭ ክስተቶችን መሠረት አድርገውአይደለም፤ የመፈጸም ዕድል አለ በሚል ያልተጨበጠ ግምት እንጂ። እጅግ የሚያሳዝነው ደግሞ የተሻለ ስም ያላቸው ተቋማት ሳይቀሩ ይሄንን በኢትዮጵያ ላይ ተቀነባብሮ የሚለቀቅ ፕሮፓጋንዳ ለመቃወም … [Read more...] about መንግሥት መሠረተ ቢስ ውንጀላዎችን ፈጽሞ እንደማይታገስ አስታወቀ
የትህነግ ታጣቂዎችና የጦር አመራሮች የጅምላ መቃብር ስፍራ የተገኘ
በመከላከያ ሰራዊት መስዋዕትነት ከህወሓት እየተላቀቁ በሚገኙት አካባቢዎች የአሸባሪው ህወሓት ድብቅ ገመና መጋለጡን ቀጥሏል። የሽብር ቡድኑ ቁንጮ አመራሮች አስገድደው በጦርነት ላሰለፏቸው ታጣቂዎች እንኳ ምንም አይነት ርህራሄ እንደሌላቸው በጨርጨር የተገኘው ጅምላ መቃብር ለዚህ ማሳያ ነው፡፡ ከጨርጨር ከተማ በስተምስራቅ በኩል በሺዎች የሚቆጠሩ የሽብር ቡድኑ ታጣቂዎችና የጦር አመራሮች የጅምላ መቃብር ስፍራ የተገኘ ሲሆን፥ ይህም የሽብር ቡድኑ ቁንጮ አመራሮች በትግራይ ህዝብ ደም በስልጣን ለመቆየት የማይፈነቅሉት ድንጋይ እንደሌለ ማሳያ ሆኗል፡፡ የጅምላ መቃብር ስፍራው መለያ ኮድ ያለውና በአንዳንዱ መቃብር ከ3 እስከ 5 አስከሬን በጋራ የተቀበረበት ሲሆን፥ የሽብር ቡድኑ ታጣቂዎቹን የቀበራቸው እንደ ኃላፊነታቸው እና ማዕረግ ደረጃቸው በመቃብራቸው ላይ ምልክቶችን በማድረግ … [Read more...] about የትህነግ ታጣቂዎችና የጦር አመራሮች የጅምላ መቃብር ስፍራ የተገኘ
ነገረ ወዲ ገብረ ትንሳኤ – ”አባዬ ምን በድለን ነው ህወሃት የምትቀጣን?”
ወደ ገደለው ስንሄድ፦ የራያው ልጅ ፃድቃን ገብረ ትንሳኤ አራት ኪሎ የባዮሎጂ ተማሪ ነበረ። ከዛም ትግል ስታይሌ ነው አለና ደደቢት በረሃ ወረደ።[ውጊያ ተለማመደ]ወያኔ ከደርግ ጋራ ስትዋጋ ከጦር ፊታውራሪዎች አንዱ ሆነ፤ ፃድቃን ገብረትንሳኤ። ከገቡም በኋላ ለአስር አመታት ያህል፣ በሌተና ጀነራል ማዕረግ፣ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የጦር ኤታማዦር ሹም (Chief of Staff) ነበረ።ፃድቃን ቀጥተኛ፣ ቅን እና ሆደ ቡቡ ነው ይሉታል የሚያውቁት።[አንዴ]የካህሳይ አብርሃን 'የአሲምባ ፍቅር' መፅሃፍን ካነበብክ፣ ያኔ ኢህአሠ አሲምባ እንደገባ በብሄር ፌድራሊዝም ጉዳይ ኢህአፓና ህወሃት ሲከራከሩ፣ ''የብሄር ፌዴራሊዝም የታክቲክ ጉዳይ ነው። ማታገያ ነው እንጂ End አይደለም'' ብሎ የሞገተ ነው። ''የትግራይ ገባር የመሬት ላራሹ ጥያቄው ስለተመለሰለት፣ አሁን መደብ ምናምን ከምንለው ጨቋኝ … [Read more...] about ነገረ ወዲ ገብረ ትንሳኤ – ”አባዬ ምን በድለን ነው ህወሃት የምትቀጣን?”
ሳሚ ዶላር አንዱ ነው፤ ሌሎቹስ ዶላር አጣቢዎች? ምነው ዝም ተባሉ?
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኅብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማና ባደረገው ብርቱ ክትትል በህገ-ወጥ መንገድ ከ5.1 ቢሊዮን ብር (ከአምስት ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር) በላይ ሲያንቀሳቅስ የነበረ ግለሰብ ከ25 ግብረ-አበሮቹ ጋር በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራባቸው መሆኑን ገለፀ፡፡ ዜናውን የሰሙ “በነካ እጃችሁ ወኪሎቹ ጋር ጎራ በሉ” ሲሉ ተደምጠዋል። በወንጀሉ የተጠረጠረው ሳሙኤል እጓለ አለሙ በቅፅል ስሙ ሳሚ ዶላር የሚባል ሲሆን ነዋሪነቱን በአዲስ አበባ ከተማ በማድረግ ወደ አሜሪካን ሀገር በተደጋጋሚ የሚመላለስ የኤሌክትሪክ መሳሪያዎች፣ የቤት እና የቢሮ እቃዎችእንዲሁም ተዛማጅ መገልገያዎች የችርቻሮ ንግድ ፍቃድን ሽፋን በማድረግ ሕገ-ወጥ የውጭ ምንዛሬና በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር ወንጀል ተጠርጥሮ በራሱና ዮዲት እጓለ አለሙ ከተባለች እህቱ ጋር በመሆን በስማቸው በተለያዩ ባንኮች … [Read more...] about ሳሚ ዶላር አንዱ ነው፤ ሌሎቹስ ዶላር አጣቢዎች? ምነው ዝም ተባሉ?