• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ

March 19, 2023 03:45 am by Editor Leave a Comment

ከአድዋ ወደ ራያ የዞረው የትግራይ አስተዳደር አዲስ መሪና ከመሪው ጀርባ የሚያጦዝ አዲስ ስብሃት ነጋን አግኝቷል። አዲሱ የስብሃት ነጋ ምትክ ንጉሥ ፈጣሪ (kingmaker) ጻድቃን ገብረ ትንሳኤ ሲሆን፣ የትግራይ ቲቪ ይፋ እንዳደረገው የትግራይ መሪ የሆነው ጌታቸው ረዳ ነው – ሁለቱም ከአማራ ከተወሰደው ራያ!!

በይፋ በሚታዩ መረጃዎች ጌታቸው ረዳ በትግራይ ታጋይ ሳይሆን ትግራይን የመራ ብቸኛ ካድሬ ሆነው ይመዘገባል። ጌታቸው ረዳ ሌላ የሚያስመዘግበው ሪኮርድ ደግሞ በጥላቻና “እረኛውን ምታ በጎቹ ይበተናሉ” በሚል መርህ የተፈለፈሉ ሚዲያ፣ አክቲቪስቶች፣ በአማራና ኦሮሚያ ክልል የብሔራቸው ተቆርቋሪ መስለው ሲንቀሳቀሱና ጥላቻን ሲያሰራጩ የነበሩ፣ በየክልሉ የክልልነት ጥያቄ በማስነሳት ግጭት እና አገር ብጥበጣ ውስጥ የገቡ፣ ሁሉ በጌታቸው አመራር ሥር ስለነበሩ ቆጣሪያቸው ይነቀላል።

ጌታቸው ረዳ የትግራይ መሪ እንደሚሆን ከተሰማ በኋላ የጥላቻውና የሁከቱ ሥርጭት መቀነሱን ኃይለማሪያም ጥበቡ ይናገራሉ። ስማቸው እንዳጠቀስ የጠየቁ አንድ የሰሜን አሜሪካ ነዋሪ “ሃብታሙና ሌሎቹን ኮተቶች ተዋቸው ይላሉ” ምክንያቱም እንደ በርሜል ተራ ጩኸት ይመስሏቸው – “ባዶዎች ናቸው” ይላሉ። አክለው “ኤርሚያስ ግን ሰግቷል” በማለት ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ጥብቅ ግንኙነት እንዳለው ይገልጻሉ። እሱ ብቻ ሳይሆን “ቴዎድሮስ ጸጋዬ፣ ጃዋር መሀመድ፣ ጃል መሮ፣ አድፋጩ ኦነግና አማራ ክልል ሤራ የሚያመርቱት ሁሉም በጌታቸው ሥር ናቸው” በማለት ይህንን ሁሉ ሤራ ጠማቂ ድባቅ በመምታት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይን ማድነቅ አለመቻል ተራ ምቀኝነት እንደሆነ ያሰምሩበታል።

የበረከት ስምዖን “ልጅ” የ360ው ኤርሚያስ፤ ከትህነጉ ጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው

ከትህነግ ቅርብ ሰዎች እንደተሰማው ከሆነ ቀደም ሲል የእነ ደብረጽዮን ቡድን ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሹመት ዝርዝር አቅርበው ነበር። ይህን ዝርዝር ለሪፖርተር ቅርበት ያላቸው የእነ ደብረጽዮን ቡድን አቀብሎ “ውስጥ አዋቂዎች ነገሩኝ” ሲል ጋዜጣው ዘግቦ ነበር።

ጻድቃንና ጌታቸው ግን ከሰላም አማራጭ የፕሪቶሪያው ስምምነት ውጭ የተደረገ መሆኑንን ገልጸው ዜናው ውሸት እንደሆነ ቢገልጹም ዜናውን የለኮሱትም ሆነ የተከፋፈሉት ይቅርታም ሆን ማስተባበያ ሳይሰሩ የአሁኑን ሹመት በነካ እጃቸው ጌታቸው የትግራይ መሪ መሆኑን በቀድሞው የውሸት ዜና ላይ ደርበው አቅርበውታል።

ጌታቸው ረዳ ጭልጥ ያለ ካድሬ ነው። ይህ ካድሬነቱ በዚህች ሁለትና ሦስት ዓመታት በሠራው ሰርከሶች የታየ በመሆኑ ዝርዝር ማብራሪያ አይጠይቅም። በአጭሩ ዐይን አውጣ ካድሬ ነው። “ከወር በኋላ ብልጽግና ወይም ሞት” ሲል ቢሰማ የሚሳቀቀው እርሱ ሳይሆን አድማጮችና ተመልካቾች ናቸው። ከዚህ በዘለለ አሁን አጓጊ የሆነው የጌታቸው ብልጽግና መሆን ሳይሆን፣ እርሱ የሚመራቸው የተቃውሞ ሚዲያዎችና በማሸበር ተግባር የተሰማሩ ተከፋይ አክቲቪስትና እዚያም እዚያ ጥይት የሚተኩሱ ወረበሎች ናቸው – ምንጫቸው ከሥሩ ሊደርቅ ነው።

የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ አርብ መጋቢት 08/2015 ዓ.ም. ባካሄደው ምርጫ ጌታቸው ረዳን የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳዳር ዋና ኃላፊ እንደሆን ይፋ ሲያደርግ ሁለት ዐበይት ጉዳዮች ወደ ፊት ብቅ ብለዋል። አንደኛው ሥልጣን ወደ ራያ ማምራቱና የትህነግ ተፈጥሯዊ ሞት መሞቱ ነው። ይህ ደግሞ የዐድዋ የበላይነትን ብቻ ሳይሆን “ተራሮችን አንቀጠቀጠ” ተብሎ የሐሰት ትርክት የተሠራለትን ልብ ወለድ ታሪክም ጭምር ወደ መቃብር የሚከት ነው።

መንግሥት ከትህነግ ጋር ድርድር በጀመረበት ወቅት ደብረጽዮን ከመድረኩ መጥፋቱና በምትኩ ጌታቸው በመሪ ተዋናይነት ብቅ ማለቱ በብዙ መልኩ የአሁኑን ጊዜ ጠቋሚ ነበር። ሆኖም በገፊና ጎታች ፖለቲካ የተጠመደው ሠራዊት አገር በማፍረስ ተጠምዶ ስለነበር የብዙዎችን ትኩረት እዚያ ላይ እንዳይሆን እንዳደረገ አስተያየት ሲሰጥ ቆይቷል። ስምምነቱ ሲደረግም ትግራይንና ትህነግን ወክሎ የፈረመው የአድዋ ሰው ሳይሆን የራያው ጌታቸው ረዳ መሆኑ የህወሓት የፖለቲካ ሞት ጅማሬ እንደሆነ ይነገራል። በጥር ወር መገባደጃ ላይ በሃላላ ኬላ የትህነግ መሪዎች ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ባቀረቡና በተገመገሙ ወቅት በጠቅላዩ በስተግራ ተቀምጦ ሲያስረዳ የነበረው ጌታቸው መሆኑ መሪው ማን እንደሚሆን ሌላ ጠቋሚ ነበር። ከጌታቸው ቀጥሎ ጻድቃን መቀመጡ ስብሃትን ተክቶ አዲሱ ንጉሥ ፈጣሪ (kingmaker) ማን እንደሆነ በግልጽ ያመላከተ ነበር።  

አፍቃሪ ትህነጉ ሰለሞን ገሪማ ይህን ይፅፋል፤ “ከዚህ በፊት ዶ/ር ደብረፅዮን በስራ ኣስፈፃሚ ተሽሞው በብዙ ተቃውሞ በማእከላይ ኮምቴ ኣይሆንም ቢባሉም “ግድ የላቹም ለኣብዪ በኣካል ሄጄ እለምነዋለሁ እምቢ ካለ ሌላ ትመርጣላቹ” ማለታቸው ሁላችን የምናስታውሰው ነው። ይህ በፌደራል መንግስት ተቀባይነት ሲያጣ በስራ ኣስፈፃሚ መሾም ቀርቶ በቀጥታ በማእከላይ ኮምቴ ትላንት የተደረገ ምርጫ የህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ ለምርጫ የተወዳደሩትና ውጤታቸው እንሆ፤

ጌታቸው ረዳ 18 ድምጽ

ዶ/ር ፍሰሃ ሃብተፅዮን 17 ድምጽ

ዶ/ር ኣማንኤል ሃይለ 3 ድምጽ

ፕሮፌሰር ህንደያ ገ/ሂወት 2 ድምጽ

ዶ/ር ሓጎስ ጎዲፋይ 0 ድምጽ

ረዳኢ ሓለፎም 0 ድምጽ ይህ ምርጫስ ተቀባይነት ያገኝ ይሆን? ኣብረን የምናየው ይሆናል” ብሏል ሰለሞን ገሪማ።

ትህነግ መንግሥት ነበር። ከአራት ኪሎ ሲወጣ ጌታቸው አሰፋን አስረክብ ሲባል ለአንድ ሰው ብሎ እምቢ በማለት ይልቁንም “እኔም ጌታቸው አሰፋ ነኝ” ብሎ ወደ መቀለ ሄደ። ከመቀለ ወደ ተፈጠረበት በረሃ ሸሸ። ከዚም አንሰራራና ተመልሶ እንዳይድን ሆኖ ተመታ፤ ከወታደራዊ ብቃት አኳያ ዱቄት ሆነ። መመታቱ ብቻ ሳይሆን ህዝቡን መከራና ስቃይ ውስጥ ከተተ። ጨለማ ውስጥ ገባ። ወጣቱን አስጨረሰ። ሲመሽበት ድሮ በፊት እምቢ ያለውን ሁሉ ትቶ “ያሻችሁን ሁሉ እሺ” ብሎ ህይወት አትርፍ ስምምነት ፈረመ። “በሒደት አብቦ ጠወለገና እንደ ቅጠል ወይቦ ሞተ” ተብሎ ከስምምነቱ በኋላ ተጽፎበት ነበር። አሁን የታየውም ይኸው ነው።

ጌታቸው መመረጡ ይፋ ከመሆኑ በፊት የፌደራሉ መንግሥት የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጥቶ ነበር። የኢትዮ 12 መረጃ ምንጮች እንዳሉት መንግሥት በፕሪቶሪያው ስምምነት መሠረት ባስቸኳይ ጊዚያዊ አስተዳደር የማይቋቋም ከሆነ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ሁኔታውን አሳውቆ፣ ለትግራይ ህዝብ አስረድቶ ራሱ የሚያምንበትን ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም እንደሚገደድ ነግሯቸው ነበር። መንግሥት ለዚህ እርምጃ ያደረሰው በጀት ለቅቆ የመንግሥት ሠራተኞች ያልተከፈላቸው ደሞዝ ተከፍሎ ወደ መደበኛ እንቅስቃሴ ለመመለስ በሚል ነው።

ሰሞኑን ደብረጽዮን የሚመራው የትግራይ ክልል የሽግግር መንግት ተመሠረተ ተብሎ የተናፈሰውን ዜና ጌታቸው በዚህ መልኩ ነበር ያስተባበለው

መንግሥት ይህ የማይሆን ከሆነ ጥይት ሳይተኩስ እምቢ ያሉትን በአውሮፕላን አሳፍሮ ወደ ማረፊያ እንደሚያስገባቸውም አስጠንቅቆ እንደነበር የገለጹት የመረጃው ባለቤቶች “የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን አዲስ አበባ የትህነግ ሰዎችን ሰብስቦ ‘ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ የሚሏችሁን አክብሩ። ከዚህ ውጭ ምንም የምናደርገው ነገር የለም’ ብለዋቸዋል። ያደረጉትም ያንን ነው” ሲሉ ነግረውናል። አዲሱ ሹመት የሚጸናው በፌደራል መንግሥቱ ቅቡል ሲሆን ብቻ እንደሆነ የፕሪቶሪያው ስምምነት ያስረዳል። እናም መንግሥት ሹመቱን ሲያጸድቀው የጌታቸው ረዳ ወንበር ይጸናል። እንደሚሰማው ከሆነ ሁሉም ነገር የመንግሥት ቅርብ ክትትል ያለበት በመሆኑ በትግራይ ክልላዊ መንግሥት ከሚያውቀው ውጭ የተለየ ፍላጎት ይስተናገዳል ተብሎ አይገመትም።

ሌላው አጓጊ ጉዳይ ትህነግ በሌላ ሰው ወይም በደብረጽዮን እንዲመራ የሚደረግ ከሆነ ነው። አስተያየት ሰጪዎች እንደሚሉት ትህነግን ከትግራይ አስተዳደር ለመገንጠልና በቀደመው አካሄድ እንዲቀጥል ከተመረጠ ዕድሉ ልክ እንደ ሰማያዊ ፓርቲ ወይም ሊሎች የቤተሰብ ፓርቲዎች መሆን ነው። በስም አስተያየት ለመስጠት ጊዜው ገና እንደሆነ የገለጹ ለኢትዮ12 የአዲስ አበባ ተባባሪ “ትህነግ አሸባሪነቱ አልተነሳም። ምርጫ ቦርድ ሰርዞታል። ሕጋዊ ዕውቅና የለውም። እዚህ ላይ ቆሞ ከትግራይ አስተዳደር ልነጠል ካል ሞቱን ሳይሆን ራሱን ተረት ወደ ማድረግ ወዷል ማለት ነው። ብዙ ማስረጃዎች ማቅረብ ይቻላል” ሲሉ ገልጸዋል። እኚህ የቀድሞ የትህነግ አባል ሰሞኑን ጉዳዩ እየጠራ ሲሄድ ዝርዝር አሳብ እንደሚሰጡም ገልጸዋል።

ጻድቃን ወታደራዊ ክንፉን የሚመራና የቀድሞውን የስብሃት ነጋን ቦታ በመያዝ ከጀርባ ሆነው የጌታቸው ረዳን አስተዳደር አባላት እንደሚያቋቁም ተወርቷል። በጻድቃን አጋዥነት ከአዲስ አበባ የቢሮ ሃላፊ ሆነው የሚሄዱ የተቀናቃኝ ፓርቲ አመራሮች እንደሚኖሩ ተሰምቷል። በትግራይ ያሉ ተቃዋሚ ድርጅቶችም ይወከላሉ ተብሏል። ወታደሩም ይገባል። (ኢትዮ 12)

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በትግራይ የነበሩ ከባድ መሣሪዎች በሙሉ ከምድር በላይ እና ከምድር በታች ተቀብረው የነበሩትንም ጨምሮ ወደ መከላከያ እየገቡ መሆኑ ተገልጾዋል። ከዚህ በታች በፎቶ እንደሚታየው የረጅም ርቀት ተተኳሾችና በክልል ደረጃ ሊኖሩ የማይገባቸው ከባድ መሣሪያዎች ገቢ እየተደረጉ ነው። በጻድቃን እና ታደሰ ወረደ የሚመራው ወታደራዊ ቡድን በፕሪቶሪያው ስምምነት መሠረት ሥራቸውን በሚገባ እያከናወኑ ይገኛሉ። በፖለቲካው ክንፍ በኩል ሲታይ የነበረው መዘግየትና ሽኩቻም በጌታቸው ረዳ ምርጫ ወደ መጠናቀቁ የደረሰ ይመስላል።

ከማኅበራዊ ሚዲያ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው የጌታቸው ረዳ በትግራ መሪነት መመረጥ የህወሃትን መንደር ለሁለት ከፍሎ እያናቆረ ነው። አንዱ ወገን ጌታቸው የቀድሞ የህወሃት/ትህነግ ታጋይ አለመሆኑ እና ህወሃትን ከበረሃ ታጋይነት ሳይሆን ከመምህርነት በቅርቡ መቀላቀሉን እያነሱ ክህደት ተፈፀመ እያለ ነው። እነዚህ በአብዛኛው የአድዋ የበላይነት ፖለቲካ አቀንቃኞችና አሁንም በመለስ የሚምሉ ሲሆኑ በአማራ አንመራም እያሉ ነው። ጌታቸው ከአማራ ክልል ከሆነው የራያ አካባቢ መሆኑ ይታወቃል። ከዚህ አንጻር “በአማራ አንመራም” ማለታቸው ራያን መሬቱን እንጂ ሰዉን አለመፈለጋቸውን ማሳበቁን የተረዱት አይመስሉም።

በሌላ በኩል የጌታቸውን መመረጥ የደገፉ በርካቶች ናቸው። መለስ ራሱ “እስከ እንጥላችን በስብሰናል” እንዳለው ህወሃት በስብሳለች ስለዚህ እንደ ጌታቸው ያለ ወጣቶችን እና ምሁራንን ያቅፋል፣ ያስጠጋል፤ የፖለቲካ ንቃቱና አረዳዱም እንደ ሽማግሌዎቹ አይደለም፤ የመናገር ችሎታውና በእንግሊዝኛ የማስረዳትና የማሳመን ችሎታው መለስን ጨምሮ ከማንኛውም የህወሓት/ትህነግ ታጋይ እጅግ የበለጠ ነው በማለት ለውጡን የደገፉ በርካታ ናቸው። የህወሃት ሥልጣን ከአድዋ መውጣቱ ብዙዎችን አስደስቷል። ይህ ካስደሰታቸው መካከል የስብሃትን አገዛዝ እጅግ የሚቃወመው ሊላይ ኃይለማርያም፣ የሰባ አንደርታ ሰዎች፣ የሽሬ ፖለቲከኞች እና በአድዋ የበላይነት ለበርካታ ዓመታት ግፍ የደረሰባቸው ሁሉ በደጋፊነት የሚጠቀሱ ሆነዋል።

የትግራይ ጉዳይ በዚህ መልኩ መጠናቀቅና የህወሓት/ትህነግ መፃዒ ዕድል ወደማይቀረው መክሰም መሄድ በቀጣይ በሻዕቢያ የበላይነት እና በለውጥ ናፋቂነት ተቆልፋ ሦስት ዐሥርተ ዓመታትን ያሳለፈችውን የኤርትራንም ቀጣይ ኅልውና በግልጽ የሚጠቁም ሆኗል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics, Slider Tagged With: abiy ahmed, ethiopian terrorists, getachew reda, operation dismantle tplf, sibhat nega, tplf, tplf terrorist, tsadkan gebretinsae

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm
  • “ሙሽራው እስኪመጣ የምትቆይ ቤተክርስቲያን እናድርጋት” ጠ/ሚ/ር ዐቢይ February 15, 2023 03:13 pm
  • በመዝገበ ቃላት የችጋር መጠሪያ የነበረችው ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ስንዴ ወደ ውጭ ላከች February 13, 2023 03:28 am
  • ውዝግቡን በሐዋሪያት መንገድ ለመፍታት ስምምነት ላይ ተደርሷል February 10, 2023 09:06 am
  • የሚከተልህ ሁሉ ወዳጅህ አይደለም – መልዕክት “ለመንፈሳዊው ቄሮ” መሪ ዘመድኩን በቀለ! February 10, 2023 12:48 am
  • በሰማዕትነት ጥሪ ቤተመንግሥቱን ባቋራጭ መቆጣጠር February 9, 2023 01:25 pm
  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule