• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ

March 15, 2023 04:44 pm by Editor Leave a Comment

ከኬንያ ላሙ ወደብ በመነሳት በደቡብ ሱዳን ወደ ኢትዮጵያ የሚደርሰውን የምስራቅ አፍሪካ የትራንስፖርት ኮሪደር ለመተግበር ደቡብ ሱዳን ስትራቴጂክ ፕላን ማዘጋጀቷ ተሰምቷል፡፡

ከኬንያ ላሙ ወደብ በመነሳት በደቡብ ሱዳን ወደ ኢትዮጵያ የሚደርሰውን የምስራቅ አፍሪካ የትራንስፖርት ኮሪደር ለመተግበር ደቡብ ሱዳን ስትራቴጂክ ፕላን ማዘጋጀቷ ተሰምቷል፡፡ እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ መጻኢ ዕድል አነጋጋሪ እያደረገው ነው፡፡

ደቡብ ሱዳን ቅድማያ ከምትሰጣቸው 16 ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ እንደሆነ የተነገረው ከሪደሩ፣ ምስራቅ አፍሪካን ከከምዕራብ አፍሪካ የሚያገናኝ ነው፡፡ የዚህ ኮሪደር አካል የሆነው ከላሙ ወደብ እስከ ኢሲሎ ያለው 500 ኪሎ ሜትር የሚረዝም መንገድ እየተገነባ ሲሆን፣ ከኢሲሎ በሞያሌ ሀዋሳ የሚደርስ 500 ኪሎ ሜትር የሚደርስ መንገድ ግንባታው ተጠናቅቋል፡፡

ደቡብ ሱዳን ቅድሚያ የምትስጣቸውን 16 ፕሮጀክቶች አስመልክቶ ከአገሪቱ ሚንስትሮች ጋር እንደተወያዩ ያስታወቁት በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የአፍሪካ ንግድ ማዕከል ዋና አማካሪ አዲይንካ አዲዬሚ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለአገሪቱ ድጋፍ እንደሚደርግ አስታውቀዋል፡፡

ይሁንና የሚገነባው መንገድ ምን ያህል ርዝመት እንዳለውና ስለተመደበለት በጀት የተባለ ነገር የለም፡፡

ኹሉም ፕሮጀክቶች የኮሪደሩን እንቅስቃሴ የሚያሳልጡ ናቸው ያሉት አማካሪው፣ ዓለም ባንከ በተለይም በመንገድ፣ ኃይልና ግብርና ዘርፍ ድጋፍ ለማድረግ መስማማቱን ተናግረዋል፡፡

ከአዲስ አበባ ሀዋሳ ድረስ እየተገነባ ያለው የፍጥነት መንገድ የትራንስፖርት ኮሪደሩን ውጤታማነት ከፍ ያደርጋል የተባለ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ኬንያና ደቡብ ሱዳን የሚዘረጉ መሰረተ ልማቶች ከኬንያው ላሙ ወደብ በመነሳት ምስራቅ አፍካን ከምዕራብ አፍሪካ በየብስ ያገናኛሉ፡፡ (አዲስ ማለዳ)

TEU Twenty-foot Equivalent Unit ማለት የመርከብ ጭነት ወይም ካርጎ ኮንቴይነር መለኪያ ሲሆን አንድ TEU ማለት ሃያ ኮንቴይነር ነው። በግራፉ ላይ እንደሚታየው የላሙ ወደብ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ በወደቡ በኩል የሚተላለፈው ጭነት በምን ያህል እንደሚያድግ የሚያሳይ ነው።

ከጥቂት ቀናት በፊት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የአንድ ቀን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት በደቡብ ሱዳን ጁባ ከተማ ማድረጋቸው ይታወሳል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጉብኝታቸው ከአገሪቱ መሪ ሳልቫ ኪር ማያርዲት ጋር በአገራቱ መካከል ስላለው የኹለትዮሽ ግንኙነት እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ መወያያታቸውና የሳልቫ ኪር ተቀናቃኝ ከሆኑት ሬክ ማቻር ጋር በመሆን ሁለቱን መሪዎች ወደ ስምምነት ማምጣታቸው ተዘግቧል።

የጠቅላዩ ጉብኝት ከወደቡ ግንባታ ጋር የተያያዘ ስለመሆኑ የተወሳ ነገር ባይኖርም በተለይ ከምዕራብ አፍሪካ የሚመጣውን የመንገድ ፕሮጀክት የምታገናኘው ደቡብ ሱዳን ጁባ በመሆኗ ፕሮጀክቱ የውይይታቸው አጀንዳ አልነበረም ለማለት አያስደፍርም የሚል አስተያየት ተሰጥቷል።

ይህ ምጽዋንና የአሰብ ወደቦችን ጥቅም ዐልባ የሚያደርግ ፕሮጀክት ኤርትራን የማያካትት ሲሆን ኤርትራ በዚህ ውስጥ መካተት የምትፈልግ ከሆነ የግድ ከኢትዮጵያ ጋር የሚያገናኛትን መስመር መዘርጋት ይጠበቅባታል። ከመሠረተ ልማት ዝርጋታው ሌላ ኤርትራ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ለውጥ ማድረግ ሌላኛዋ የቤት ሥራዋ ይሆናል። በአንዳንድ የቀጣናው ባለሙያዎች ትንታኔ መሠረት ኤርትራ ፈጣን ለውጦችን የማታደርግ ከሆነ ነጻ ከወጣች ጥቂት ዓመታት ያስቆጠረችው ደቡብ ሱዳን ጋር ለመድረስ የሚያቅታት የቀጣናው ደካማ አገር ትሆናለች ይላሉ።

የሰሜኑ ጦርነት ከተጠናቀቀ በኋላ የኢትዮጵያ ትኩረት ወደ ኢኮኖሚው በመሆኑና ለዚህም በኤርትራ ወደቦች ላይ ያላትን ፍላጎት ከጅቡቲ ሌላ ወደ በርበራ አሁን ደግሞ ወደ ላሙ ወደብ በከፍተኛ ሁኔታ ፊቷን ማዞሯ በአስመራ በኩል እጅግም ደስታን የፈጠረ አይመስልም። ጥቅም ዐልባ ከሆነው አሰብ ሌላ ምጽዋም ከኤርትራ በስተቀር የሚፈልገው የማይኖርበት ደረጃ ላይ ደርሷል።

የላሙ ወደብ እና የመሠረተ ልማት ግንባታ ሲጠናቀቅ ከአዲስ አበባ አዋሳ እስከ ሞይሌ ባለው መሥመር ላይ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ለውጥ ይኖራል ተብሎ ይጠበቃል። አዋሳ ላይ ያለው ኢንዱስትሪያል ፓርክ እና ወደ ደቡብ በሚወስደው መንገድ የሚመረቱ ፍራፍሬዎች ወደ ውጪ ምርት በቀላሉ የሚቀርቡ ሲሆን በተጓዳኝ በሚሠራው የነዳጅ ቧንቧ ኢትዮጵያ ያለ ወደብ በቀላሉ የነዳጅ ፍላጎቷን የምታሳካ ይሆናል።

ከዚህም ሌላ ኢትዮጵያ ምርቷን በምዕራብ አፍሪካ በኩል ወደ አውሮጳ፣ ሰሜን እና ደቡብ አሜሪካ እንዲሁም በምሥራቅ በላሙ የኬኒያ ወደብ በኩል ወደ ሕንድ፣ ቻይና፣ ሩቅ ምሥራቅ፣ አውስትራሊያና ኒው ዚላንድ የምታቀርብና የውጭ ምርቶችንም የምታስገባ ይሆናል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ ይሁን በሌላ የቻይና የምስራቅ አፍሪቃ ልዩ መልዕክተኛ ሰሞኑንን አዲስ አበባ ተገኝተው ከመንግስት ጋር መክረዋል። ምክክሩም ከጁባ መልስ እንደሆነ ይታወሳል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, Politics Tagged With: Lamu Port, LAPSSET, LAPSSET Corridor project

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule