• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ

March 15, 2023 04:44 pm by Editor Leave a Comment

ከኬንያ ላሙ ወደብ በመነሳት በደቡብ ሱዳን ወደ ኢትዮጵያ የሚደርሰውን የምስራቅ አፍሪካ የትራንስፖርት ኮሪደር ለመተግበር ደቡብ ሱዳን ስትራቴጂክ ፕላን ማዘጋጀቷ ተሰምቷል፡፡

ከኬንያ ላሙ ወደብ በመነሳት በደቡብ ሱዳን ወደ ኢትዮጵያ የሚደርሰውን የምስራቅ አፍሪካ የትራንስፖርት ኮሪደር ለመተግበር ደቡብ ሱዳን ስትራቴጂክ ፕላን ማዘጋጀቷ ተሰምቷል፡፡ እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ መጻኢ ዕድል አነጋጋሪ እያደረገው ነው፡፡

ደቡብ ሱዳን ቅድማያ ከምትሰጣቸው 16 ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ እንደሆነ የተነገረው ከሪደሩ፣ ምስራቅ አፍሪካን ከከምዕራብ አፍሪካ የሚያገናኝ ነው፡፡ የዚህ ኮሪደር አካል የሆነው ከላሙ ወደብ እስከ ኢሲሎ ያለው 500 ኪሎ ሜትር የሚረዝም መንገድ እየተገነባ ሲሆን፣ ከኢሲሎ በሞያሌ ሀዋሳ የሚደርስ 500 ኪሎ ሜትር የሚደርስ መንገድ ግንባታው ተጠናቅቋል፡፡

ደቡብ ሱዳን ቅድሚያ የምትስጣቸውን 16 ፕሮጀክቶች አስመልክቶ ከአገሪቱ ሚንስትሮች ጋር እንደተወያዩ ያስታወቁት በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የአፍሪካ ንግድ ማዕከል ዋና አማካሪ አዲይንካ አዲዬሚ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለአገሪቱ ድጋፍ እንደሚደርግ አስታውቀዋል፡፡

ይሁንና የሚገነባው መንገድ ምን ያህል ርዝመት እንዳለውና ስለተመደበለት በጀት የተባለ ነገር የለም፡፡

ኹሉም ፕሮጀክቶች የኮሪደሩን እንቅስቃሴ የሚያሳልጡ ናቸው ያሉት አማካሪው፣ ዓለም ባንከ በተለይም በመንገድ፣ ኃይልና ግብርና ዘርፍ ድጋፍ ለማድረግ መስማማቱን ተናግረዋል፡፡

ከአዲስ አበባ ሀዋሳ ድረስ እየተገነባ ያለው የፍጥነት መንገድ የትራንስፖርት ኮሪደሩን ውጤታማነት ከፍ ያደርጋል የተባለ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ኬንያና ደቡብ ሱዳን የሚዘረጉ መሰረተ ልማቶች ከኬንያው ላሙ ወደብ በመነሳት ምስራቅ አፍካን ከምዕራብ አፍሪካ በየብስ ያገናኛሉ፡፡ (አዲስ ማለዳ)

TEU Twenty-foot Equivalent Unit ማለት የመርከብ ጭነት ወይም ካርጎ ኮንቴይነር መለኪያ ሲሆን አንድ TEU ማለት ሃያ ኮንቴይነር ነው። በግራፉ ላይ እንደሚታየው የላሙ ወደብ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ በወደቡ በኩል የሚተላለፈው ጭነት በምን ያህል እንደሚያድግ የሚያሳይ ነው።

ከጥቂት ቀናት በፊት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የአንድ ቀን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት በደቡብ ሱዳን ጁባ ከተማ ማድረጋቸው ይታወሳል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጉብኝታቸው ከአገሪቱ መሪ ሳልቫ ኪር ማያርዲት ጋር በአገራቱ መካከል ስላለው የኹለትዮሽ ግንኙነት እና ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ መወያያታቸውና የሳልቫ ኪር ተቀናቃኝ ከሆኑት ሬክ ማቻር ጋር በመሆን ሁለቱን መሪዎች ወደ ስምምነት ማምጣታቸው ተዘግቧል።

የጠቅላዩ ጉብኝት ከወደቡ ግንባታ ጋር የተያያዘ ስለመሆኑ የተወሳ ነገር ባይኖርም በተለይ ከምዕራብ አፍሪካ የሚመጣውን የመንገድ ፕሮጀክት የምታገናኘው ደቡብ ሱዳን ጁባ በመሆኗ ፕሮጀክቱ የውይይታቸው አጀንዳ አልነበረም ለማለት አያስደፍርም የሚል አስተያየት ተሰጥቷል።

ይህ ምጽዋንና የአሰብ ወደቦችን ጥቅም ዐልባ የሚያደርግ ፕሮጀክት ኤርትራን የማያካትት ሲሆን ኤርትራ በዚህ ውስጥ መካተት የምትፈልግ ከሆነ የግድ ከኢትዮጵያ ጋር የሚያገናኛትን መስመር መዘርጋት ይጠበቅባታል። ከመሠረተ ልማት ዝርጋታው ሌላ ኤርትራ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ለውጥ ማድረግ ሌላኛዋ የቤት ሥራዋ ይሆናል። በአንዳንድ የቀጣናው ባለሙያዎች ትንታኔ መሠረት ኤርትራ ፈጣን ለውጦችን የማታደርግ ከሆነ ነጻ ከወጣች ጥቂት ዓመታት ያስቆጠረችው ደቡብ ሱዳን ጋር ለመድረስ የሚያቅታት የቀጣናው ደካማ አገር ትሆናለች ይላሉ።

የሰሜኑ ጦርነት ከተጠናቀቀ በኋላ የኢትዮጵያ ትኩረት ወደ ኢኮኖሚው በመሆኑና ለዚህም በኤርትራ ወደቦች ላይ ያላትን ፍላጎት ከጅቡቲ ሌላ ወደ በርበራ አሁን ደግሞ ወደ ላሙ ወደብ በከፍተኛ ሁኔታ ፊቷን ማዞሯ በአስመራ በኩል እጅግም ደስታን የፈጠረ አይመስልም። ጥቅም ዐልባ ከሆነው አሰብ ሌላ ምጽዋም ከኤርትራ በስተቀር የሚፈልገው የማይኖርበት ደረጃ ላይ ደርሷል።

የላሙ ወደብ እና የመሠረተ ልማት ግንባታ ሲጠናቀቅ ከአዲስ አበባ አዋሳ እስከ ሞይሌ ባለው መሥመር ላይ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ለውጥ ይኖራል ተብሎ ይጠበቃል። አዋሳ ላይ ያለው ኢንዱስትሪያል ፓርክ እና ወደ ደቡብ በሚወስደው መንገድ የሚመረቱ ፍራፍሬዎች ወደ ውጪ ምርት በቀላሉ የሚቀርቡ ሲሆን በተጓዳኝ በሚሠራው የነዳጅ ቧንቧ ኢትዮጵያ ያለ ወደብ በቀላሉ የነዳጅ ፍላጎቷን የምታሳካ ይሆናል።

ከዚህም ሌላ ኢትዮጵያ ምርቷን በምዕራብ አፍሪካ በኩል ወደ አውሮጳ፣ ሰሜን እና ደቡብ አሜሪካ እንዲሁም በምሥራቅ በላሙ የኬኒያ ወደብ በኩል ወደ ሕንድ፣ ቻይና፣ ሩቅ ምሥራቅ፣ አውስትራሊያና ኒው ዚላንድ የምታቀርብና የውጭ ምርቶችንም የምታስገባ ይሆናል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ ይሁን በሌላ የቻይና የምስራቅ አፍሪቃ ልዩ መልዕክተኛ ሰሞኑንን አዲስ አበባ ተገኝተው ከመንግስት ጋር መክረዋል። ምክክሩም ከጁባ መልስ እንደሆነ ይታወሳል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, Politics Tagged With: Lamu Port, LAPSSET, LAPSSET Corridor project

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule