• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ

April 4, 2023 10:07 am by Editor Leave a Comment

በአዲስ አበባ፣ በባህርዳር፣ በአዳማና በድሬዳዋ ከፍተኛ የመንግሥት አመራሮችን ኢላማ ያደረገ ጥቃቶች በመፈጸም ሀገራዊ ሁከትና ብጥብጥ ለማስነሳት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ቡድኖች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረሐይል  አስታወቀ፡፡

የጋራ ግብረ ሐይሉ ለመገናኛ ብዙኅን  በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፣  በአማራና በሌሎች ክልሎች ውስጥ መቀመጫቸውን ያደረጉ እንዲሁም አዲስ አበባ ጭምር የሚገኙ ምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶችን ያካተተ ህቡዕ መዋቅር በምስጢር ሲንቀሳቀስ እንደነበር ተደርሶበታል።

ዶ/ር ወንደሰን አሰፋ፣ ረዳት ፕሮፌሰር ሲሳይ አውግቸው፣ ፕሮፌሰር ማዕረጉ ቢያበይን፣ ዶ/ር መሰረት፣ ወርቁ ተስፋዬ ወ/ማርያም፣ ተስፋዬ የኋላሸት ፋሲል፣ ሰለሞን ልመንህ ከተማና መንበረ የተባሉ ግለሠቦችም በህቡዕ አደረጃጀቱ ሲሳተፉና ሲያስተባብሩ በቁጥጥር ስር ውለዋል።

ሀገራዊ ለውጡን ለማስቀጠል በከፍተኛ የባለቤትነትና የሐላፊነት መንፈስ የሚንቀሳቀሰውን ሰፊውን የአማራን ሕዝብ የማይወክሉት እና አሁን የተፈጠረው አንጻራዊ ሰላም ያልተመቻቸው እነዚህ ጽንፈኛ ቡድኖች ኅብረተሰቡ በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ ጭቆና ውስጥ ይገኛል የሚል ቅስቀሳ በማድረግ  በሃይማኖት፣ በብሔር እንዲሁም ከእኛ ውጪ ሀገሪቷን ሌላ ማስተዳደር የለበትም በሚል የፖለቲካ ፅንፈኝነት ዓላማ ዙሪያ ደጋፊዎችን ለማሰባሰብ እየሞከሩ መሆኑን መግለጫው አመልክቷል፡፡

በዚህም ሕዝቡን ነጻ እናወጣለን የሚል የአመጽ እንቅስቃሴ ለማካሄድ ሲደራጁና ሀገሪቱን ዳግም ወደነበረችበት ቀውስ ለመመለስ ሲንቀሳቀሱ እንደነበርም ጠቁሟል።

ይህንን አላማቸውን ከግብ ለማድረስ በአማራ ክልል ውስጥ በሁሉም ስፍራዎችና በአዲስ አበባ እንዲሁም በሀገሪቷ በሚገኙ ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎችን በአካባቢዎቹ ከሚኖሩ የብሔሩ ተወላጆች ጋር አስተሳስሮ የማደራጀት ሥራዎች ሢሠሩ እንደነበር መግለጫው አስታውቋል።

በተቀናጀ መልኩ ህቡዕ ወታደራዊ ክንፍ በማደራጀት በጦር መሣሪያ የታገዘ የከተማ ላይ ጥቃት የመፈፀም እቅድ እንደነበራቸው፤ በተለይ በየደረጃው የሚገኙ የመንግሥት ባለስልጣናት ላይ ጥቃት በመፈፀም ሕዝቡን የማሸበር ተልዕኮ አንግበው ሲንቀሳቀሱ መቆየታቸውን የጋራ ግብረሐይሉ መግለጫ ጠቁሟል፡፡

ከላይ በተገለጹት ህቡዕ አመራሮች የተዋቀረው የአዲስ አበባው የአደረጃጀቱ ክንፍ በየክፍለ ከተማው ለዘረጋው መዋቅሩ በርካታ የተለያዩ የነፍስ ወከፍ የጦር መሣሪያዎች፣ተቀጣጣይ ፈንጂዎችና ቦምቦችን ወደ ከተማዋ ማስገባቱንም መግለጫው አስታውቋል፡፡

ከእነዚህ ውስጥ ግዛት የተባለ ባህርዳር ዙሪያ ቁንዝላ አካባቢ መቀመጫውን ያደረገና በአዲስ ውስጥ ለሚገኘው ህቡዕ ክንፍ የተለያዩ ሎጀስቲክስ የሚያቀርብ ግለሰብ በርካታ የእጅ ቦምብ በተለያዩ ክፍለ ከተማዎች ለሚገኙት የቡድኑ አባላት እንዲያስረክብ አቅጣጫ የተሰጠው ቢሆንም፤ በተደረገውቨ ክትትል በቁጥጥር ስር እንዲውል ተደርጓል፡፡

በተጨማሪም አዲስ አበባ ጣፎ አካባቢ በሚገኝ የቡድኑ አስተባባሪ በሆነው ዳዊት አባቡ ቢተው እና አዲስ አበባ ካራ ኣሎ አካባቢ ነዋሪ በሆነው ታደሰ ወይነው ተሰማ ላይ በተደረገው ክትትል የተለያዩ የጦር መሣሪያዎችና የወታደር ዩኒፎርሞች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ መደረጉን ግብረሐይሉ ለመገናኛ ብዙኅን በላከው መግለጫ አመልክቷል፡፡

ሙሉቀን ወንዴ ቢተው ፣ ቴዎድሮስ ተሾመ አየነውና ሌሎችም በህቡዕ አደረጃጃቱ በነበራቸው ተሳትፎ መያዛቸውን ጠቁሟል፡፡

በህቡዕ አደረጃጀቱ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ሌሎች ተጠርጣሪዎችን በቁጥርር ስር የማዋሉ ተግባር በተቀናጀ መንገድ መቀጠሉን ያመለከተው የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረሐይሉ መግለጫ፤ በቀጣይ ከጉዳዩ ጋር የተያያዙ ወቅታዊ መረጃችን ለኅብረተሰቡ ተከታትሎ እንደሚያቀርብ አስታውቋል፡፡

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: amhara terrorists, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule