• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ

April 4, 2023 10:07 am by Editor Leave a Comment

በአዲስ አበባ፣ በባህርዳር፣ በአዳማና በድሬዳዋ ከፍተኛ የመንግሥት አመራሮችን ኢላማ ያደረገ ጥቃቶች በመፈጸም ሀገራዊ ሁከትና ብጥብጥ ለማስነሳት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ቡድኖች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረሐይል  አስታወቀ፡፡

የጋራ ግብረ ሐይሉ ለመገናኛ ብዙኅን  በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፣  በአማራና በሌሎች ክልሎች ውስጥ መቀመጫቸውን ያደረጉ እንዲሁም አዲስ አበባ ጭምር የሚገኙ ምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶችን ያካተተ ህቡዕ መዋቅር በምስጢር ሲንቀሳቀስ እንደነበር ተደርሶበታል።

ዶ/ር ወንደሰን አሰፋ፣ ረዳት ፕሮፌሰር ሲሳይ አውግቸው፣ ፕሮፌሰር ማዕረጉ ቢያበይን፣ ዶ/ር መሰረት፣ ወርቁ ተስፋዬ ወ/ማርያም፣ ተስፋዬ የኋላሸት ፋሲል፣ ሰለሞን ልመንህ ከተማና መንበረ የተባሉ ግለሠቦችም በህቡዕ አደረጃጀቱ ሲሳተፉና ሲያስተባብሩ በቁጥጥር ስር ውለዋል።

ሀገራዊ ለውጡን ለማስቀጠል በከፍተኛ የባለቤትነትና የሐላፊነት መንፈስ የሚንቀሳቀሰውን ሰፊውን የአማራን ሕዝብ የማይወክሉት እና አሁን የተፈጠረው አንጻራዊ ሰላም ያልተመቻቸው እነዚህ ጽንፈኛ ቡድኖች ኅብረተሰቡ በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ ጭቆና ውስጥ ይገኛል የሚል ቅስቀሳ በማድረግ  በሃይማኖት፣ በብሔር እንዲሁም ከእኛ ውጪ ሀገሪቷን ሌላ ማስተዳደር የለበትም በሚል የፖለቲካ ፅንፈኝነት ዓላማ ዙሪያ ደጋፊዎችን ለማሰባሰብ እየሞከሩ መሆኑን መግለጫው አመልክቷል፡፡

በዚህም ሕዝቡን ነጻ እናወጣለን የሚል የአመጽ እንቅስቃሴ ለማካሄድ ሲደራጁና ሀገሪቱን ዳግም ወደነበረችበት ቀውስ ለመመለስ ሲንቀሳቀሱ እንደነበርም ጠቁሟል።

ይህንን አላማቸውን ከግብ ለማድረስ በአማራ ክልል ውስጥ በሁሉም ስፍራዎችና በአዲስ አበባ እንዲሁም በሀገሪቷ በሚገኙ ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎችን በአካባቢዎቹ ከሚኖሩ የብሔሩ ተወላጆች ጋር አስተሳስሮ የማደራጀት ሥራዎች ሢሠሩ እንደነበር መግለጫው አስታውቋል።

በተቀናጀ መልኩ ህቡዕ ወታደራዊ ክንፍ በማደራጀት በጦር መሣሪያ የታገዘ የከተማ ላይ ጥቃት የመፈፀም እቅድ እንደነበራቸው፤ በተለይ በየደረጃው የሚገኙ የመንግሥት ባለስልጣናት ላይ ጥቃት በመፈፀም ሕዝቡን የማሸበር ተልዕኮ አንግበው ሲንቀሳቀሱ መቆየታቸውን የጋራ ግብረሐይሉ መግለጫ ጠቁሟል፡፡

ከላይ በተገለጹት ህቡዕ አመራሮች የተዋቀረው የአዲስ አበባው የአደረጃጀቱ ክንፍ በየክፍለ ከተማው ለዘረጋው መዋቅሩ በርካታ የተለያዩ የነፍስ ወከፍ የጦር መሣሪያዎች፣ተቀጣጣይ ፈንጂዎችና ቦምቦችን ወደ ከተማዋ ማስገባቱንም መግለጫው አስታውቋል፡፡

ከእነዚህ ውስጥ ግዛት የተባለ ባህርዳር ዙሪያ ቁንዝላ አካባቢ መቀመጫውን ያደረገና በአዲስ ውስጥ ለሚገኘው ህቡዕ ክንፍ የተለያዩ ሎጀስቲክስ የሚያቀርብ ግለሰብ በርካታ የእጅ ቦምብ በተለያዩ ክፍለ ከተማዎች ለሚገኙት የቡድኑ አባላት እንዲያስረክብ አቅጣጫ የተሰጠው ቢሆንም፤ በተደረገውቨ ክትትል በቁጥጥር ስር እንዲውል ተደርጓል፡፡

በተጨማሪም አዲስ አበባ ጣፎ አካባቢ በሚገኝ የቡድኑ አስተባባሪ በሆነው ዳዊት አባቡ ቢተው እና አዲስ አበባ ካራ ኣሎ አካባቢ ነዋሪ በሆነው ታደሰ ወይነው ተሰማ ላይ በተደረገው ክትትል የተለያዩ የጦር መሣሪያዎችና የወታደር ዩኒፎርሞች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ መደረጉን ግብረሐይሉ ለመገናኛ ብዙኅን በላከው መግለጫ አመልክቷል፡፡

ሙሉቀን ወንዴ ቢተው ፣ ቴዎድሮስ ተሾመ አየነውና ሌሎችም በህቡዕ አደረጃጃቱ በነበራቸው ተሳትፎ መያዛቸውን ጠቁሟል፡፡

በህቡዕ አደረጃጀቱ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ሌሎች ተጠርጣሪዎችን በቁጥርር ስር የማዋሉ ተግባር በተቀናጀ መንገድ መቀጠሉን ያመለከተው የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረሐይሉ መግለጫ፤ በቀጣይ ከጉዳዩ ጋር የተያያዙ ወቅታዊ መረጃችን ለኅብረተሰቡ ተከታትሎ እንደሚያቀርብ አስታውቋል፡፡

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, News Tagged With: amhara terrorists, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሤራ አክሻፊው ጎንደር ለሦስተኛ ጊዜ ታሪክ ሠራ May 10, 2023 09:25 am
  • ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል May 9, 2023 09:24 am
  • ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ May 4, 2023 01:12 am
  • መረጃ ቲቪ ያጋራው አሳሳች መረጃ May 2, 2023 12:37 pm
  • “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን” April 13, 2023 10:19 am
  • በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው April 13, 2023 08:56 am
  • በትህነግ የፈረሰው የአክሱም ኤርፖርት ያስከተለው ዘርፈብዙ ኪሣራ April 13, 2023 03:21 am
  • “የከተማው ነዋሪ በመሰላቸቱ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ችግር” ገጥሟቸዋል April 12, 2023 09:23 am
  • ከዕድሜ ልክ እስከ 20 ዓመት ቅጣት ተበይኖባቸዋል April 11, 2023 02:58 pm
  • የኡጋንዳ የክልሎች ሚኒስትር በቆርቆሮ ሌብነት ተጠርጥረው ታሰሩ April 10, 2023 03:59 pm
  • ታከለ ከተነሳ በኋላ የመዐድን ሌቦች እየተያዙ ነው April 6, 2023 02:53 pm
  • አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ April 4, 2023 10:07 am
  • በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል April 4, 2023 09:26 am
  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule