• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ

April 4, 2023 10:07 am by Editor Leave a Comment

በአዲስ አበባ፣ በባህርዳር፣ በአዳማና በድሬዳዋ ከፍተኛ የመንግሥት አመራሮችን ኢላማ ያደረገ ጥቃቶች በመፈጸም ሀገራዊ ሁከትና ብጥብጥ ለማስነሳት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ቡድኖች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረሐይል  አስታወቀ፡፡

የጋራ ግብረ ሐይሉ ለመገናኛ ብዙኅን  በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፣  በአማራና በሌሎች ክልሎች ውስጥ መቀመጫቸውን ያደረጉ እንዲሁም አዲስ አበባ ጭምር የሚገኙ ምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶችን ያካተተ ህቡዕ መዋቅር በምስጢር ሲንቀሳቀስ እንደነበር ተደርሶበታል።

ዶ/ር ወንደሰን አሰፋ፣ ረዳት ፕሮፌሰር ሲሳይ አውግቸው፣ ፕሮፌሰር ማዕረጉ ቢያበይን፣ ዶ/ር መሰረት፣ ወርቁ ተስፋዬ ወ/ማርያም፣ ተስፋዬ የኋላሸት ፋሲል፣ ሰለሞን ልመንህ ከተማና መንበረ የተባሉ ግለሠቦችም በህቡዕ አደረጃጀቱ ሲሳተፉና ሲያስተባብሩ በቁጥጥር ስር ውለዋል።

ሀገራዊ ለውጡን ለማስቀጠል በከፍተኛ የባለቤትነትና የሐላፊነት መንፈስ የሚንቀሳቀሰውን ሰፊውን የአማራን ሕዝብ የማይወክሉት እና አሁን የተፈጠረው አንጻራዊ ሰላም ያልተመቻቸው እነዚህ ጽንፈኛ ቡድኖች ኅብረተሰቡ በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ ጭቆና ውስጥ ይገኛል የሚል ቅስቀሳ በማድረግ  በሃይማኖት፣ በብሔር እንዲሁም ከእኛ ውጪ ሀገሪቷን ሌላ ማስተዳደር የለበትም በሚል የፖለቲካ ፅንፈኝነት ዓላማ ዙሪያ ደጋፊዎችን ለማሰባሰብ እየሞከሩ መሆኑን መግለጫው አመልክቷል፡፡

በዚህም ሕዝቡን ነጻ እናወጣለን የሚል የአመጽ እንቅስቃሴ ለማካሄድ ሲደራጁና ሀገሪቱን ዳግም ወደነበረችበት ቀውስ ለመመለስ ሲንቀሳቀሱ እንደነበርም ጠቁሟል።

ይህንን አላማቸውን ከግብ ለማድረስ በአማራ ክልል ውስጥ በሁሉም ስፍራዎችና በአዲስ አበባ እንዲሁም በሀገሪቷ በሚገኙ ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎችን በአካባቢዎቹ ከሚኖሩ የብሔሩ ተወላጆች ጋር አስተሳስሮ የማደራጀት ሥራዎች ሢሠሩ እንደነበር መግለጫው አስታውቋል።

በተቀናጀ መልኩ ህቡዕ ወታደራዊ ክንፍ በማደራጀት በጦር መሣሪያ የታገዘ የከተማ ላይ ጥቃት የመፈፀም እቅድ እንደነበራቸው፤ በተለይ በየደረጃው የሚገኙ የመንግሥት ባለስልጣናት ላይ ጥቃት በመፈፀም ሕዝቡን የማሸበር ተልዕኮ አንግበው ሲንቀሳቀሱ መቆየታቸውን የጋራ ግብረሐይሉ መግለጫ ጠቁሟል፡፡

ከላይ በተገለጹት ህቡዕ አመራሮች የተዋቀረው የአዲስ አበባው የአደረጃጀቱ ክንፍ በየክፍለ ከተማው ለዘረጋው መዋቅሩ በርካታ የተለያዩ የነፍስ ወከፍ የጦር መሣሪያዎች፣ተቀጣጣይ ፈንጂዎችና ቦምቦችን ወደ ከተማዋ ማስገባቱንም መግለጫው አስታውቋል፡፡

ከእነዚህ ውስጥ ግዛት የተባለ ባህርዳር ዙሪያ ቁንዝላ አካባቢ መቀመጫውን ያደረገና በአዲስ ውስጥ ለሚገኘው ህቡዕ ክንፍ የተለያዩ ሎጀስቲክስ የሚያቀርብ ግለሰብ በርካታ የእጅ ቦምብ በተለያዩ ክፍለ ከተማዎች ለሚገኙት የቡድኑ አባላት እንዲያስረክብ አቅጣጫ የተሰጠው ቢሆንም፤ በተደረገውቨ ክትትል በቁጥጥር ስር እንዲውል ተደርጓል፡፡

በተጨማሪም አዲስ አበባ ጣፎ አካባቢ በሚገኝ የቡድኑ አስተባባሪ በሆነው ዳዊት አባቡ ቢተው እና አዲስ አበባ ካራ ኣሎ አካባቢ ነዋሪ በሆነው ታደሰ ወይነው ተሰማ ላይ በተደረገው ክትትል የተለያዩ የጦር መሣሪያዎችና የወታደር ዩኒፎርሞች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ መደረጉን ግብረሐይሉ ለመገናኛ ብዙኅን በላከው መግለጫ አመልክቷል፡፡

ሙሉቀን ወንዴ ቢተው ፣ ቴዎድሮስ ተሾመ አየነውና ሌሎችም በህቡዕ አደረጃጃቱ በነበራቸው ተሳትፎ መያዛቸውን ጠቁሟል፡፡

በህቡዕ አደረጃጀቱ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ሌሎች ተጠርጣሪዎችን በቁጥርር ስር የማዋሉ ተግባር በተቀናጀ መንገድ መቀጠሉን ያመለከተው የጸጥታና ደኅንነት የጋራ ግብረሐይሉ መግለጫ፤ በቀጣይ ከጉዳዩ ጋር የተያያዙ ወቅታዊ መረጃችን ለኅብረተሰቡ ተከታትሎ እንደሚያቀርብ አስታውቋል፡፡

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Left Column, News Tagged With: amhara terrorists, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule