የክፋት አለቃው ህወሀት መራሹ ወንበዴ ቡድን በክፋት ሰይፉ ጉዳት ካደረሰባቸው የሰራዊት ክፍሎች መካከል ብ/ጀነራል ናስር አባዲጋ የሚመሩት የ8ኛ ሜካናይዝድ ክ/ጦር ይገኝበታል። ሜካናይዝድ ክፍለ ጦሩ የደረሰበትን የክፋት ጥቃት ተቋቁሞ ሃይሉንና ትጥቁን በመያዝ እየተዋጋ ወደ ጎረቤት ሃገር ኤርትራ ከተሻገረ በኋላ እንደገና ሃይሉንና ትጥቁን አቀናጅቶ እየተዋጋ የገባ ክፍለ ጦር ነው። እስከ ሽራሮ እየተዋጋ መጥቶም፣ ከሰሜን ምዕራብ ግንባር ዳንሻ ጀምሮ እየተዋጋ ከመጣው ምዕራብ ዕዝ ጋር በመቀናጀት እስከ መቀሌ ከዛም ጁንታው ተበጣጥሶ በረሃ እስከገባበት ጊዜ ድረስ በውጤት እርቀቱ ሆኖ ከባድ ምት በማሳረፍ የነበረው ሚና በቃላት ከሚገለፀው በላይ ነው። መቀሌን እንደተቆጣጠርን የሜካናይዝድ አዛዡን ብ/ጀነራል ናስር አባዲጋን አግኝቼ ስለ ጥቃቱ አናግሪያቸው ነበር። እሳቸውም … [Read more...] about “ለትግራይ እንደ ጫማ ሶል ሆነን ነው ስናገለግል የነበረው … ለእኛ ይህ አይገባም ነበር” – ብ/ጀነራል ናስር አባ ዲጋ
News
ዜና
መከላከያ ያገኘው የአሸባሪው ህወሃት ኮትተ
በተወሰደበት እርምጃ የጁንታው አፈ ቀላጤ ጌታቸው ረዳ ታጣቂ ኃይሉን ብቻ ሳይሆን የመዋጊያ ንብረቶቹንም ጭምር በየቦታው ማዝረክረኩን የ21ኛ ጉና ክፍለ ጦር አስታወቀ፡፡ የደቡብ ዕዝ 21ኛ ጉና ክፍለ ጦር የሠራዊት አባላት፣ የማይሰበር እልህና ወኔ ሰንቀው ጁንታው በዕብሪት ተወጥሮ በሀገራችን የጀመረውን ጦርነት በማክሸፍ የሀገራችንን ሉአላዊነት በማስከበር የህግ የበላይነትን እንዲረጋገጥ እያደረጉ እንደሚገኙ የ21ኛ ጉና ክፍለ ጦር ህብረት ዘመቻ ቡድን መሪ ሌ/ኮ ብርሃኑ ኃይሉ ተናግረዋል። ሌ/ኮ ብርሃኑ ኃይሉ ሰሞኑን በተደረገው በፈታኝ መሰናክል የታጀበ የአሰሳ ውጊያ ፣ የአካባቢውን አስቸጋሪ ተራራና አቀበት በመጋፈጥ ጠላትን ማፅዳት መቻሉን አረጋግጠዋል፡፡ በተለይም የጁንታው አፈቀላጤ የሆነው አቶ ጌታቸው ረዳ ሲፈረጥጥ አንጠባጥቧቸውና ደብቋቸው የነበሩትን ወታደራዊ ንብረቶች … [Read more...] about መከላከያ ያገኘው የአሸባሪው ህወሃት ኮትተ
“ችግኙ” ተተክሏል!
ሰኔ 14 ቀን 2013 ለኢትዮጵያ ታሪካዊ ቀን ነው። በሀገራችን የመጀመሪያ ነፃ እና ፍትሃዊ ምርጫ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች ድምፃቸውን ለማሰማት ወጥተዋል። ምስሎች አንድ ሺህ ቃላት ይናገራሉ እናም እነሱ በህዝባችን ያለውን ቅንነት፣ ለሰላም እና ለዴሞክራሲያዊ ሂደት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያሉ። ኢትዮጵያ ትናንት አሸነፈች። ኢትዮጵያ በአሸናፊነት ትቀጥላለች! - ጠ/ሚ/ር ዐቢይ አሕመድ June 21, 2021, is a historic day for Ethiopia. All sections of society have gone out to cast their voice in our nation’s first free and fair election. Pictures are worth a thousand words and they show the earnestness, commitment to peace, and the … [Read more...] about “ችግኙ” ተተክሏል!
በኦሮሚያ ክልል በ26 ታጣቂዎች ላይ ዕርምጃ ተወሰደ
በኦሮሚያ ክልል በጅማ ዞን፣ በቦረናና ጉጂ ዞኖች አካባቢ ሲንቀሳቀሱ የነበሩና የምርጫውን ሒደት ለማስተጓጎል በተንቀሳቀሱ 26 ታጣቂዎች ላይ ዕርምጃ መወሰዱ ታወቀ፡፡ ዕርምጃ ከተወሰደባቸው መካከል 20ዎቹ ታጣቂዎች ከጅማ ዞን ናቸው፡፡ ጅማ ዞን፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ (ዶ/ር) ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልነት በጎማ 2 የምርጫ ክልል ዕጩ ሆነው የቀረቡበት አካባቢ ነው፡፡ የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ጥላሁን አመንቴ ለሪፖርተር እንዳስታወቁት፣ በተለያዩ የኦሮሚያ አካባቢ ይንቀሳቀሱ የነበሩና በፓርላማ አሸባሪ ተብለው የተፈረጁ ታጣቂ ቡድኖች በምርጫው ሒደት ላይ መስተጓጎል ለመፍጠር በመሞከራቸው ዕርምጃ ተወስዶባቸዋል፡፡ የክልሉ ፖሊስ ከተለያዩ የፀጥታ አካላት ጋር በመሆን በምርጫው ሒደት የሚከሰቱ የተለያዩ ችግሮችን ለመከላከል፣ … [Read more...] about በኦሮሚያ ክልል በ26 ታጣቂዎች ላይ ዕርምጃ ተወሰደ
የመለስ ዜናዊ አካዳሚ ለ21ኛው ክፍለዘመን የማይመጥን ስም በመሆኑ ተቀየረ
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ "የመለስ ዜናዊ የአመራር አካዳሚ" "የአፍሪካ የአመራር ልህቀት ማዕከል" (‘African Leadership Excellence Academy’) በሚል መቀየሩን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው አስታውቀዋል። አካዳሚው ከስም ለውጥ ጋር የ21 ኛው ክፍለዘመን የአመራር ጥያቄዎችን ለማሟላት የሚያስችል ዐቅም ያላቸውን ልሂቃን የሚያፈራ እና የዕድገት ተኮር አስተሳሰብን የሚያንፀባርቅ የትምህርት ተቋም እንዲሆን ያለመ ነው ብለዋል። ሌሎችም ከአሸባሪው ህወሃት ጋር የተቆራኙ ስሞችና መጠሪያዎች እንዲሁ እንዲቀየሩ አስተያየት ሰጪዎች ተናግረዋል። ከዚህ በፊት አካዳሚውን እንዲመሩ የተሾሙት ዮሐንስ ቧያለው የአካዳሚው ስም በመጸየፍ አልመራም ማለታቸው ይታወሳል። ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about የመለስ ዜናዊ አካዳሚ ለ21ኛው ክፍለዘመን የማይመጥን ስም በመሆኑ ተቀየረ
“ቀኑ ለመራጮችና ለተፎካካሪ ፓርቲዎች ብቻ ሳይሆን ለአገራችንም ጥሩ ነው” ወ/ሪት ብርቱካን
የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ እኩለ ቀን ላይ ምርጫውን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ፣ ‹‹ቀኑ ለመራጮች፣ ለፓርቲዎችና በአጠቃላይ ለአገራችን ጥሩ ነው፤›› ብለዋል፡፡ በመጀመርያው ዙር የምርጫ ሒደት እስካሁን አንድም የፀጥታ ችግር አልገጠመንም፡፡ አምቦ አንድ ጣቢያ ላይ ምንም የተፈጠረ ነገር ሳይኖር ለአስፈጻሚዎች በደረሳቸው መረጃ በመደናገጥ ለጊዜው ገለል ብለዋል፡፡ ነገር ግን እናስቀጥለዋለን ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ከባድ ችግር የለም፡፡ ምርጫው መደረግ ባለባቸው ሁሉም ሥፍራዎች እየተካሄደ ነው፡፡ ዜጎችም እየመረጡ ይገኛሉ፡፡ ምርጫው መደረግ ባለባቸው ጣቢያዎች በአብዛኛው በሚባል ሁኔታ በሰዓቱ ከፍተው መራጮችን ሲያስተናግዱ ቆይተዋል፡፡ አዲስ አበባ ላይ 9 ምርጫ ጣቢያዎች ላይ ኃላፊነት የጎደላቸው አስፈጻሚዎች በቦታቸው ባለመገኘታቸው ጣቢያዎቹ ሳይከፈቱ ቆይተዋል፡፡ … [Read more...] about “ቀኑ ለመራጮችና ለተፎካካሪ ፓርቲዎች ብቻ ሳይሆን ለአገራችንም ጥሩ ነው” ወ/ሪት ብርቱካን
የሽብር ጥቃት ለመፈፀም ሲንቀሳቀሱ የነበሩ በቁጥጥር ስር ዋሉ
በአዲስ አበባና በአንዳንድ የኦሮሚያ ከተሞች የተቀናጀ የሽብር ጥቃት ለመፈፀም አቅደው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የሽብር ቡድን አባላት በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የደህንነትና ፀጥታ የጋራ ግብረ ኃይል አስታወቀ፡፡ የደህንነትና ፀጥታ የጋራ ግብረ ኃይል ለመገናኛ ብዙሃን በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው፥ በአዲስ አበባና በአንዳንድ የኦሮሚያ ከተሞች ሁከት፣ ሽብርና ትርምስ በመፍጠር ድብቅ የፖለቲካ አጀንዳቸውን ለማሳካት በሚንቀሳቀሱ የውጭ እና የውስጥ ፀረ-ሰላም ኃይሎች የሚደገፉ የሸብርተኞቹ የህወሓትና የሸኔ ቡድን አባላት በሰው ሕይወትና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ለማድረስ ሴራ ወጥነው ወደ እንቅስቃሴ ለመግባት በዝግጅት ላይ እንዳሉ በጋራ ግብረ ኃይሉ በተደረገባቸው ጥብቅና የተቀናጀ ክትትል በቁጥጥር ስር ውለዋል። ይህን እኩይ የጥፋት ሴራ ለመፈጸም ከውጭ በተለያዩ አካላት በሚደረግላቸው … [Read more...] about የሽብር ጥቃት ለመፈፀም ሲንቀሳቀሱ የነበሩ በቁጥጥር ስር ዋሉ
በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 110 ሺህ ዶላር ከነተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር ዋለ
በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እና በብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት በተደረገ ክትትል በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 1 መቶ 10 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ከነተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ በህገ ወጥ መንገድ ሲጓጓዝ የነበረው ዶላር የተያዘው ሚያዚያ 28 ለ29 አጥቢያ 2013 ዓ/ም በአዲስ አበባ የካ ክፍለ ከተማ ላምበረት መናኸሪያ ግቢ ውስጥ ከለሊቱ 10 ሰዓት ገደማ ነው፡፡ ከአዲስ አበባ ወደ ሃረር ሊጓዙ የተዘጋጁ ሁለት ተጠርጣሪዎች በያዙት ሻንጣ ላይ በተደረገ ፍተሻ በጥቁር ላስቲክ የተጠቀለለ 110 ሺህ የአሜሪካ ዶላር መገኘቱን ፖሊስ ያስታወቀው፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝም የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡ (ኢብኮ) ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 110 ሺህ ዶላር ከነተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር ዋለ
“የአውሮፓ ህብረት የምርጫ ታዛቢዎች ውዝግብን ከመጫር ባሻገር የፈየዱልን አንዳችም ነገር የለም” ፕ/ር በየነ
የአውሮፓ ህብረት የምርጫ ታዛቢዎች መምጣት አለመምጣት በአገራዊው የምርጫ ሂደት ላይ የሚያሳድረው አንዳችም ተጽዕኖ እንደሌለ የኢትዮጵያ ሶሻል ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ኢሶዴፓ)ፕሬዚዳንትና የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ አስታወቁ ። ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ በተለይም ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቁት፣ የአውሮፓ ህብረት የምርጫ ታዛቢዎች መምጣት አለመምጣት በአገራዊው የምርጫ ሂደት ላይ የሚያሳድረው አንዳችም ተጽእኖ የለም፤ ምክንያቱም ታዛቢዎች ባሉበት ባለፉት ምርጫዎች ወቅትም ውዝግብን ከመጫር ባሻገር የፈየዱልን አንዳችም ነገር የለም። በተለይም በ1997ቱ ምርጫ ወቅት የአውሮፓ ህብረት ታዘብኩ ብሎ ያወጣው መረጃ እንደ አገር ብዙ ዋጋ የከፈልንበት ብዙ ትርምስ የተፈጠረበት ከመሆኑ አንጻር አሁን ላይ አንመጣም ማለታቸው የሚያጎለው አንዳችም … [Read more...] about “የአውሮፓ ህብረት የምርጫ ታዛቢዎች ውዝግብን ከመጫር ባሻገር የፈየዱልን አንዳችም ነገር የለም” ፕ/ር በየነ
ከ6ሺ ኩንታል በላይ በቆሎ በግለሠብ መጋዘን ውስጥ ተገኘ
በደብረ ማርቆስ ከተማ ከ6ሺ ኩንታል በላይ በቆሎ በአንድ ግለሠብ መጋዘን ውስጥ ተከዝኖ ተገኘ። በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ቀበሌ ዐ5 ልዩ ቦታው ኢንዱስትሪ መንደር ውስጥ በሚገኝ ለሙጫና እጣን ማቀነባበሪያ መጋዘን ውስጥ ከ6ሺ ኩንታል በቆሎ በላይ ተከዝኖ መገኘቱን የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት ጽ/ቤት ገልጿል። የተገኘውን እህል በከተማው ለሚገኙ አስራ አራት ሸማች ህብረት ስራ ማህበራት እንደሚከፋፈል እና በዛሬው ዕለት ሁለት ሸማች ማህበራት ከአራት መቶ በላይ ኩንታል መውሰዳቸውን እና ለህብረተሰቡ እንደሚከፋፈል የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ብርሀኑ መኩሪያው ገልጸዋል። የወንጀሉ ጉዳይም ፖሊስ አስፈላጊውን ምርምራ እያጣራ መሆኑን አስረድተዋል። (የደብረ ማርቆስ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት) ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about ከ6ሺ ኩንታል በላይ በቆሎ በግለሠብ መጋዘን ውስጥ ተገኘ










