
የክፋት አለቃው ህወሀት መራሹ ወንበዴ ቡድን በክፋት ሰይፉ ጉዳት ካደረሰባቸው የሰራዊት ክፍሎች መካከል ብ/ጀነራል ናስር አባዲጋ የሚመሩት የ8ኛ ሜካናይዝድ ክ/ጦር ይገኝበታል።
ሜካናይዝድ ክፍለ ጦሩ የደረሰበትን የክፋት ጥቃት ተቋቁሞ ሃይሉንና ትጥቁን በመያዝ እየተዋጋ ወደ ጎረቤት ሃገር ኤርትራ ከተሻገረ በኋላ እንደገና ሃይሉንና ትጥቁን አቀናጅቶ እየተዋጋ የገባ ክፍለ ጦር ነው።
እስከ ሽራሮ እየተዋጋ መጥቶም፣ ከሰሜን ምዕራብ ግንባር ዳንሻ ጀምሮ እየተዋጋ ከመጣው ምዕራብ ዕዝ ጋር በመቀናጀት እስከ መቀሌ ከዛም ጁንታው ተበጣጥሶ በረሃ እስከገባበት ጊዜ ድረስ በውጤት እርቀቱ ሆኖ ከባድ ምት በማሳረፍ የነበረው ሚና በቃላት ከሚገለፀው በላይ ነው።
መቀሌን እንደተቆጣጠርን የሜካናይዝድ አዛዡን ብ/ጀነራል ናስር አባዲጋን አግኝቼ ስለ ጥቃቱ አናግሪያቸው ነበር። እሳቸውም የሚከተለውን ብለውኛል።
ሰራዊቱ የገባውን ቃል ኪዳን ለመፈፀም ምሽግ ላይ በነበረበት ከጀርባው ቃላት በማይገልፀው ጭካኔ በጥይት ተመቷል, በሳንጃ ታርዷል። በውድቅት ሌሊት በተኛበት እጅ ወደ ላይ እያሉ ከልጁ እና ከሚስቱ እየነጠሉ በክፋታቸው በልተውታል። ድርጊቱ የሰው ልጅ ሆኖ ሰው ላይ የሚፈፀም አይደለም። በውትድርና አገልግሎት ዘመኔ እንደዚህ አይነት ክህደትም ጭካኔም አይቼም ሰምቼም አላውቅም። ድርጊታቸው አረመኔያዊ ነው።
ለምሳሌ ታንክ ሾፌር በምንም አይነት ጭንቅላቱን አይመታም። ጠላት ከገባ ቦንብ ወርውሮ ታንክ ጋር ምድብተኛውን ያቃጥላል እንጂ። በነፍስ ወከፍ ጥይት ግን ጭንቅላት አይመታም። ይህን ያደረገ ውስጣችን የተደራጀ ጠላት ነው። የጠነከረብንም ውስጣችን የተደራጀው ጠላት ነው። በዚህም ብዙ ጎድተውናል። ነገሩ በጣም ዘግናኝ ነው።
ጥቃቱን የፈፀሙበት እለት መብራትና ኔትወርክ አጥፍተው ነበር። ሃሳባቸው በተኛንበት የቻሉትን ገድለው የቻሉትን ማርከው መሳሪያ መቀበል ነበር። ግን አልተሳካላቸውም። የመጣ መኪና ከ40 በላይ ነው። ለሰላሳ ሰዓታት ያክልም ያለማቋረጥ ተዋግተናል። ውጊያውን ማሸነፍ እንደማይችሉ ሲያውቁ ልዩ ሃይል ኮማንዶ ከቤተ መንግስት እናስመጣለን እያሉ ነበር። ይህም ጀግንነታችን አላስቆመውም።
መጨረሻ ላይ ሙሉ ሃይላችንን ይዘን ወደ ጎረቤት ሃገር ኤሪትራ ተሻገርን። እንደ ክፍለ ጦር እስታፍ ደግሞ 85 ፐርሰንቱ ትግሪኛ ተናጋሪዎች ነበሩ – በተለይ በሀላፊነት ቦታ። ውጊያው ከነዚህ ጋርም በመሆኑ ነው የከበደን። ነገሩን ይፋ ሳያወጡ ውስጥ ለውስጥ ብዙ ነገሮችን ሰርተዋል። መገናኛ አካባቢ ትልቅ እንቅፋት ፈጥረዋል።
ግምጃ ቤትም ከፍተው አስታጥቀዋል። ንብረት ጫን አትጫንም ከፍተኛ ችግር ፈጥረዋል። የተሽከርካሪ ነዳጅ ለመሙላት ብዙ አስተጓጉለውናል። መጨረሻም ዝገግጅታችን ጨርሰን ወደ ጓል ባድመ ተንቀሳቀስን። ወደዛ እየሄድን እንደሆነ እኔ እና ኮሚቴዬ ነበር የምናውቀው። ኮሚቴዬ ግን የምናደርገውን ሁሉ ለጁንታው አለቆች ያሳውቅ ነበር። በጉዟችንም ብዙ እንቅፋቶች ተፈጥረዋል።
እንቅፋቶችን እያስወገድን ጓል ባድመ እንደደረስንም ከሌሎች አሃዶች ጋር መልሶ መቋቋም አድርገን እንዋጋለን ብለን ተነሳን። ከማዕከል ከመጡ አመራሮቻችን ጋር ተገናኝተን ስለ ሁኔታው ተነጋገርን። በጥቃቱ ሰራዊቱ እጅግ ተቆጥቷል። ፈጥነን ገብተን ለምን አንደመስስም የሚል ከፍተኛ ተነሳሽነት ፈጥሯል።
ለሰዎቹ የመጨረሻ ቅጣት ሞት ቢባል እንኳ ሞት ያንሳል። አንድ ሺ ጊዜ ቢሞቱም ቅጣት አይሆንም። ቤተሰብ ነበርን። አንድ ነበርን። ብዙ ነገሮችን አብረን አሳልፈናል። እኔ ወደ ትግራይ ምድር የገባሁት ከኢትዮ-ኤሪትራ ውጊያ ጀምሮ ነው። ያ ማለት ወደ ሃያ ሶስት ዓመት ያክል ሆኖኛል ማለት ነው። በዚህ ዓመት ውስጥ የሰራነው ቀላል አይደለም። ትግራይ ለማች የምትባለው በኢትዮጵያ ህዝብ ንብረት ነው። በወታደሩ ደሞዝ ጭምር ነው። በተለይ መከላከያን ይመለከታል።
ትግራይ በተፈጥሮ ሃብት ልማት ተሸላሚ ነበረች። ማንም የተከለው አይደለም። 80 ፐርሰንት ሰራዊቱ በጉልበቱና በገንዘቡ የተከላቸው ችግኞች ናቸው። ብዙ ትምህርት ቤቶችና መንገዶች ሰርተናል። ከጀርባ ሊወጉን እየተዘጋጁ እንኳ ት/ቤት ገንቡልን የሚል ጥያቄ አንስተዋል። ለዚህ ግንባታ ነው ሰራዊት ቀስቅሰን ብር እየሰበሰብን የነበረው። ሽሬ ላይ ለሚኖሩ አካል ጉዳተኞች የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት እስከ አራተኛ ፎቅ ድረስ ገንብተናል። ለዚህ ግንባታ ኮሚቴው እኔ ነኝ የነበርኩት። ሰራዊቱም ገንዘቡን ለማዋጣት አይሰስትም ነበር።
ሰራዊታችን ከዓመት ዓመት ሙሉ ደመወዙን ወስዶ አያውቅም። ጥቃቱ የደረሰ ዕለት እንኳ በክልሉ በስፋት የተከሰተውን አንበጣ ለመከላከል ከህዝቡ ጋር ስራ ነው የዋልነው። በአጠቃላይ ለትግራይ እንደ ጫማ ሶል ሆነን ነው ስናገለግል የነበረው። አንድም ቀን እነሱን የሚጎዳ ነገር አስበንም አድርገንም አናውቅም።
ለእኛ ይህ አይገባም ነበር። ሰራዊቱን ያስቆጣውም ያነሳሳውም ይህ ነው። ሁሉንም አውዶች በጀግንነት ነው ሲፈፅሞ የነበረው። ውጊያው በአጭር ጊዜ የተቋጨውም ለዚህ ነው። በተገኘው ድል ደግሞ ከምናገረው በላይ ደስተኛ ነኝ። የሜካናይዝድ ክፍለ ጦሩ አባላትም እንደዛው። አሸናፊው የኢትዮጵያ ህዝብ ነውና!
ታገል አልማው
ፎቶግራፍ ሽመልስ እሸቱ (መከላከያ ፌስቡክ)
TPLF is brutal and inhuman. For long Ethiopians debated that TPLF and Tigray people are not one & the same. But now situations are indicating that most are lining behind the terrorist TPLF and fighting the national defense force that brings nothing to the poor Tigrean excepting suffering while TPLF fighting for power and misappropriation of national wealth as seen while they were in power. Even if they request for referendum for session, they end up in unbelievable suffering of the poor and nothing more.
ቂል ብቻ ነው ወያኔን አምኖ የሚጠጋ። ከበረህ እስከ ከተማ ያለው ታሪካቸው በደም የተጨማለቀ ነው። ግፍ ለእነርሱ ምሳና ቁርስ ነው። በአንጃ ስም በየጊዜው በትግራይ በረሃ የተገደሉ የትግራይ ልጆች ደም ዛሬም ለፍትህ ይጮሃል። ሰሚ ግን የለም። ግን በመንጋ አስተሳሰብ ለሚንጋጋ የዘርና የጎሳ ፓለቲከኛ እውነትን ፍትሾ ከእውነት ጋር መሰልፍ አዳጋች ነው። ያው አንድ እንቁራሪት ሲንጫጫ ሌላው እንደሚንጫጫው ሁሉ አብሮ መንጎድ ነው። አሁን ከጌታቸው ረዳ ጋር አብራ ፎቶ ተነሳች የተባለችው የእርዳታ ሰራተኛ በእኔ ግምት ትጥቅና ስንቅ አቀባይ እንጂ እርዳታ ሰጪ አይደለችም። ይህ በፊትም ሲሰራበት የኖረ ነው። ወያኔ የኢትዮጵያን ስም በዓለም መድረክ ላይ አጠልሽቶ ራሱን በጉቦና በሌላም መንገድ እያጎላ ለዘመናት መለያየትን ሲያራምድ ቆይቷል። ለነጩ ዓለም የተሰበከለት እኛ አናሳዎች ስለሆን ለዘመናት በአማራ ተጨቁነናል እያሉ ነው። በትግራይ መሬት አሁን የሚንጋጉት ስመ እርዳታ ሰጪ ድርጅቶች ይበልጦቹ የስለላ መሳሪያዎች ናቸው። ይህን ካለፈ ታሪክ ጋር ማመሳከር እውነትን ለመረዳት ይረዳል። ለትግራይ ህዝብ ተላከ፤ ተሰጠ፤ እየተባለ በየሚዲያው የሚናፋው የምግብና የልብስ አልፎም የገንዘብ እርዳታ ለህዝቡ እንዳለ አይደርስም። ካርቱም ገቢያ ላይ ያለውን እቃ፤ ገዳሪፍ ላይ ያለውን የእህልና የቁሳቁስ በግልጽ ሽያጭ ያየ ምን እንደምል ሊገባው ይችላል። እነዚህ እርዳታ ሰጪ ድርጅቶች በየምክንያቱ የእርዳታውን መጠን ካመነመኑት በህዋላ ተራፊው ደግሞ በሃገር ውስጥ ሌቦች ተመዝብሮና በወያኔ የጠለፋ ቡድን ተጠልፎ ትንሽዬ ነገር ብቻ ናት ለተረጂው ህዝብ የሚደርሰው። አሁን ጉልበቴን አጠናክሬ ይህን ሥፍራ ነጻ አወጣሁ፤ ያን ያዝኩ፤ ደመሰስኩ፤ ገደልኩ የሚሉት የወያኔ አፈ ቀላጤዎች በውጭና በሃገር ውስጥ አፍቃሪ ኢትዮጵያ የሆኑ ድህረ ገጾችን በማበላሽት፤ በመጥለፍ፤ በማሰናከል የተሳሳተ መረጃ ለዓለም ህዝብ በመበተን፤ ለትምህርት ተቋማትና ለሥራ ቦታዎች የፈጠራ ወሬ ያዘለ ደብዳቤ በመጻፍ፤ ሰዎችን ከመኖሪያ ቤታቸው ድረስ በመሄድ በማስፈራራት፤ በስልክ ወዪልህ እንገልሃለን/ልሻለን በማለት አጥብቀው እየሰሩ እንደሆነ ጎልቶ ይታያል። ሲልላቸው በደቦ ተሰባስበው አንድን ምስኪን ወይም አንዷን ምስኪን በመቀጥቀጥ የትግራይን ህዝብ መከራ እናስቆማለን ብለው የሚያስቡ ወራዶች በዓለም ዙሪያ ይራወጣሉ። የችግሩ ፈጣሪ እኛ፤ የችግሩም መፍትሄ በእጃችን ነው የሚሉት እነዚህ ጎዶች መብረቃዊው ጥቃታቸው በራሳቸው ላይ ቶርኔዶ ሲሆንባቸው ከእብደታቸው መማር እንዴት እንዳልቻሉ ይገርመኛል። በወያኔ አሳሩን የሚበላው የትግራይ ህዝብ አንዴ ሻቢያ መጣብህ፤ ሌላ ጊዜ ብልጽግና ሊያርድህ ነው ሲባል ሁሌ ውሸት እንደጋቱት ይኽው ለዚህ በቅተናል። እኔ የሻቢያም ሆነ የብልጽግና ጠበቃ አይደለሁም። ፓለቲከኛ ሆኖ በድርጅት ራሱን አስጠልሎ ሽንክ ያልሆነ ፍጡር በምድር አይገኝም። ግን ሰው ሰው መሆኑ ቀርቶ እንስሳ ሲሆን ማየት ምንኛ ያሳዝናል። የሰሜን እዝ ለትግራይ ህዝብ ያልሆነለት የለም። ብዙ አርገናል ይባላል። ያን ማን ከዳ? የትግራይ ህዝብ እኮ አፍ አውጥቶ ምንም ያረጋቹሁት የለም አላለም። እናውቅልሃለን የሚሉት የወያኔ ስብስቦች ባላወቀው ጦርነት ውስጥ ማግደው አሁን እንሆ ባይተዋር አድርገውታል። ሰው ከዘሩ ውጭ በተሰላ አስተሳሰብ ካልተራመደ አጥርቶ ማየት አይቻለውም። የአሁን የነጮች ጋጋታና ከልክ ያለፈ የሚዲያ ሽፋን ሌላ ላቅ ያለ ወሬ ሲገኝ የወያኔው ጉዳይ ማገዶ ይሆናል። እንዴት ጥቁር ህዝብ የነጭንና የዓረብን ተንኮል መረዳት ይሳነዋል? ዋናው የእነርሱ መሪ ቃል “እሾህን በእሾህ” ነው። እንድንገዳደል፤ ቤታችን እንድናቃጥል ሁሌ የእነርሱ ተመጽዋች እንድንሆን ይሻሉ። በፊትም ዛሬም ያደረጉትና የሚያደርጉት ይህኑ ነው።
ጄ/ሉ ለትግራይ እንደ ጫማ ሶል ሆነን ነው ያገለገልነው ማለታቸው ያው ህዝብን የሚያገለግል ብሄራዊ ሃይል እንደዛ ነው ተግባሩ። ግን ወያኔ ያን ያህል ተደራጅቶ በሰራዊቱ አደጋ እስኪያደርስ ድረስ ምንም ጭምጭምታ አለማግኘቱ ምን ያህል የወያኔ አመራሮች ሰራዊቱን ኩበት ለቀማ ይልኩት እንደነበር ያሳያል። የሰራዊቱ የስለላ መረብ ፍሬ ቢስ እንደሆነም ነው የሚያመላክተው። ተተኪውን ጄ/ል ከመቀሌ አየር ማረፊያ ሲመልሷቸው እንዴት ሰው አይነቃም? ጡረታ የወጡት የወያኔ አመራሮች መቀሌን ሲያጨናንቋት የታሰበ ነገር እንዳለ እንዴት መገመት ይከብዳል። አንድ መኮነን ሲናገሩ “እኛ ከውስጥ እንወጋለን ብለን አስበን አናውቅም”። ታዲያ ማንን ነበር በመቀሌው ሰልፍ ላይ ኑና ግጠሙን እናሳያችሁሃለን እያሉ ወያኔ ሲፎክር የነበረው። ይገርማል። በእውነት የሰሜን እዝም ሆነ ሌላው የሰራዊት ክፍል ከዚህ ስህተት ተምሮ ጠንካራ የስለላ መረብ ይዘረጋ ይሆን? ይመስለኛል። ካለሆነ ተመልሶ መሸወድ ነው። ጊንጥ ኪሱ ከቶ አልነደፍም የሚል ሰው እብድ ነው። ወያኔ ሰው ገድሎ የሚያፋልግ ከጀርመኑ ናዚ ጋር የሚነጻጸር ከሰው ስብዕና የወጣ የቡድን ድርጅት ነው። አሁንም የትግራይን ልጆች የሚያስጨርሰው ከዚያው ከመቀሌ በፓሊስ፤ በሲቪል፤ በጊዜአዊ መንግስት ተቋም ውስጥ ተሰግስገው የሚገኙ ወያኔ አፍቃሪ ሃይሎች በሚያቀብሉት መረጃ ነው ሰው በየደረሰበት እንደ እርድ ከብት ተቆራርጦ የሚጣለው። ይህ ለትግራይ ህዝብ ማሰብ ከሆነ የቁም እብደት ነው። እውነቱ ግን ለራስ ስልጣን የሚያስብ ማንም መንግስት/ሃይል ቢሆን በደም መታጠብን እንደ ውሃ ነው የሚቆጥረው። ተልካሻና ትርፍ የለሽ ፓለቲካ ከዘመናት በህዋላ ዞሮ ተመልሶ ገድልና ጫካ ቤቴ ነው ብሎ በእርጅና ይታገላል። የሮም አወዳደቅ ይሉሃል እንዲህ ነው። በሌላው ሞት መሳቅ የራስ ቀን እስኪመጣ ድረስ!
ወያኔ የተበተነ ድቄት፤ ተደመሰሰ፤ ሃገር ጥሎ ጠፋ፤ ታሰረ ተፈታ ገል መሌ መባሉ ሁሉ ወሬ ነው። ወያኔ ማለት የካብ እባብ ማለት ነው። አንድ ጋ ታይቶ ሌላ ጋ። ምንም የሚሞቱ አይደሉም። ክፋት መሪያቸው ነው። ነጩና አረቡ አለም ምግባቸው ነው። ዛሬም ወደፊትም ሲገድሉ፤ ሲያፈርሱ፤ ሲገዳደሉ ይኖራሉ። ለወያኔ መዘናጋት ሞትን መጋበዝ ነው። መምጫቸው አይታወቅም። ነጭ ይልኩብሃል። አረብ ይቀጥራሉ። አማራውን ይደልላሉ፤ ኦሮሞውንና ሌላው ተጨቆንክ ና እኛ ቀን እናወጣልሃለን እያሉ መላሾ ይሰጣሉ። ልብ ያለው ሁሉን ይመረምራል። እስቲ ይታያችሁ እንዴት ባለ ሂሳብ ነው ወደ ኤርፓርት የሚሄድ ኢንጂኒየር ተጠልፎ ስጋው ተቆራርጦ በመቀሌ የተገኘው። እንቅስቃሴውን የሚከታተሉ በየጊዜው ሪፓርት የሚያረጉ እዚያው ከጸጥታ አስከባሪዎች መካከል ወያኔዎች አሉ። ይከፈላቸዋል። የደም ሃብት ይሉሃል እሱ ነው። ፍትህ ለትግራይ ህዝብ። ሞት ለወያኔ! በቃኝ!