የክፋት አለቃው ህወሀት መራሹ ወንበዴ ቡድን በክፋት ሰይፉ ጉዳት ካደረሰባቸው የሰራዊት ክፍሎች መካከል ብ/ጀነራል ናስር አባዲጋ የሚመሩት የ8ኛ ሜካናይዝድ ክ/ጦር ይገኝበታል። ሜካናይዝድ ክፍለ ጦሩ የደረሰበትን የክፋት ጥቃት ተቋቁሞ ሃይሉንና ትጥቁን በመያዝ እየተዋጋ ወደ ጎረቤት ሃገር ኤርትራ ከተሻገረ በኋላ እንደገና ሃይሉንና ትጥቁን አቀናጅቶ እየተዋጋ የገባ ክፍለ ጦር ነው። እስከ ሽራሮ እየተዋጋ መጥቶም፣ ከሰሜን ምዕራብ ግንባር ዳንሻ ጀምሮ እየተዋጋ ከመጣው ምዕራብ ዕዝ ጋር በመቀናጀት እስከ መቀሌ ከዛም ጁንታው ተበጣጥሶ በረሃ እስከገባበት ጊዜ ድረስ በውጤት እርቀቱ ሆኖ ከባድ ምት በማሳረፍ የነበረው ሚና በቃላት ከሚገለፀው በላይ ነው። መቀሌን እንደተቆጣጠርን የሜካናይዝድ አዛዡን ብ/ጀነራል ናስር አባዲጋን አግኝቼ ስለ ጥቃቱ አናግሪያቸው ነበር። እሳቸውም … [Read more...] about “ለትግራይ እንደ ጫማ ሶል ሆነን ነው ስናገለግል የነበረው … ለእኛ ይህ አይገባም ነበር” – ብ/ጀነራል ናስር አባ ዲጋ