• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ቀኑ ለመራጮችና ለተፎካካሪ ፓርቲዎች ብቻ ሳይሆን ለአገራችንም ጥሩ ነው” ወ/ሪት ብርቱካን

June 21, 2021 11:25 pm by Editor 1 Comment

የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ እኩለ ቀን ላይ ምርጫውን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ፣ ‹‹ቀኑ ለመራጮች፣ ለፓርቲዎችና በአጠቃላይ ለአገራችን ጥሩ ነው፤›› ብለዋል፡፡ በመጀመርያው ዙር የምርጫ ሒደት እስካሁን አንድም የፀጥታ ችግር አልገጠመንም፡፡ አምቦ አንድ ጣቢያ ላይ ምንም የተፈጠረ ነገር ሳይኖር ለአስፈጻሚዎች በደረሳቸው መረጃ በመደናገጥ ለጊዜው ገለል ብለዋል፡፡ ነገር ግን እናስቀጥለዋለን ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ከባድ ችግር የለም፡፡ ምርጫው መደረግ ባለባቸው ሁሉም ሥፍራዎች እየተካሄደ ነው፡፡ ዜጎችም እየመረጡ ይገኛሉ፡፡ ምርጫው መደረግ ባለባቸው ጣቢያዎች በአብዛኛው በሚባል ሁኔታ በሰዓቱ ከፍተው መራጮችን ሲያስተናግዱ ቆይተዋል፡፡ አዲስ አበባ ላይ 9 ምርጫ ጣቢያዎች ላይ ኃላፊነት የጎደላቸው አስፈጻሚዎች በቦታቸው ባለመገኘታቸው ጣቢያዎቹ ሳይከፈቱ ቆይተዋል፡፡ ነገር ግን ቦርዱ ወዲያው መፍትሔ ወስዷል፡፡ በዘጠኙ ጣቢያዎች የተፈጠረውን ክፍተት በመሙላት 27 አስፈጻሚዎች ቃል ገብተው ተሰማርተዋል፡፡ ምርጫውም እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ 

የመዝገብ መጥፋት 

አዲስ አበባ ላይ አንድ የመራጮች መዝገብ የጠፋ ሲሆን፣ ይህንን እናጣራለን ያሉት ወ/ሪት ብርቱካን፣ ይህ መራጮችን ችግር ውስጥ እንደማያስገባና በአፋጣኝ መዝገብ ተልኮ ካርዳቸው እየታየ የምርጫ ሒደቱ መቀጠሉን ተናግረዋል፡፡ 

የቁሳቁስ እጥረት

በአንዳንድ ቦታዎች የቁሳቁስ እጥረት ገጥሟል፡፡ ይህ አታሚው ከተሰጠው ትዕዛዝ ውጪ በ50/50 ያሸጋቸው የመራጮች ወረቀቶች መኖራቸው ችግር ፈጥሮ ነበር፡፡ የታዘዘው 100/100 አንድ ላይ ተጣብቆ እንዲመጣ ነበር፡፡ ይህ ችግር የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ድምፅ መስጫ ወረቀት ላይ አልተከሰተም፡፡ ችግሩ የተከሰተው በክልል ላይ ሲሆን፣ የጎላው ደግሞ አሶሳ ላይ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት የድምፅ መስጫ ወረቀቱ ስላለቀባቸው በአየር ኃይልና በኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፋጣኝ አሶሳ እንዲደርስ እናደርጋለን ብለዋል፡፡ 

አሶሳ ላይ ለተፈጠረው የመምረጫ ወረቀት እጥረት መራጮች ላይ ለሚፈጠረው እንግልት ይቅርታ እንጠይቃለን ሲሉም ወ/ሪት ብርቱካን ተናግረዋል፡፡ 

የሲቪል ሶሳይቲ ታዛቢዎች

የሲቪል ሶሳይቲ ታዛቢዎች በየቦታው እየተንቀሳቀሱ እንደሆነ አረጋግጠናል፡፡ አንድ ሁለት ቦታ ላይ ግን ታዛቢዎችን አናስገባም ብለው ያለመቀበል ሁኔታ በቦርዱ አስፈጻሚዎች ታይቶ ነበር፡፡ ነገር ግን ለዚህ መፍትሔ ተሰጥቶ እየታዘቡ ነው፡፡ 

ያልተከፈቱ ጣቢያዎች 

በደቡብ ኡባ ደብረፀሐይ በተባለ የምርጫ ክልል አንድ ሰማያዊ ምርጫ መስጫ ሳጥን ተሰርቋል፡፡ ይህንን ፖሊስ እያጣራ ነው፡፡ ብብርና አግሊቾ ምርጫ ክልሎች ላይ (የክልል ምክር ቤት) ምርጫ ክልሎች ሆነው፣ የተወካዮች ምክር ቤትንም ይመርጣሉ፡፡ የተወካዮች ምክር ቤት ሰነድ ምንም ችግር ባይኖረውም፣ የደቡብ የምርጫ ክልሎች ዲዛይን ውስብሰብ በመሆኑ አንዱ መሄድ የነበረበት ለሌላው ሄዷል፡፡ ነገር ግን ምርጫው ሳይስተጓጎል እየተከናወነ ነው፡፡

እዚህም እዚያም የምርጫ ወረቀት ያነሳቸው የምርጫ ጣቢያዎች አሉ፡፡ ከሥር ከሥር ለማድረስ የሚያስፈልገው ዝግጅት እየተደረገ ሲሆን፣ መግለጫው ከተሰጠበት እኩለ ቀን አንስቶ የጎደለው እንደሚሟላ ተገልጿል፡፡  

ቦርዱን ያሳሰበው ጉልህ ችግር 

በየምርጫ ጣቢያው የፖለቲካ ፓርቲዎች ወኪሎቻቸውን አስቀምጠው ጉዳዩን የመታዘብ፣ የማየት፣ ችግር ከጋጠመ አስመዝግበው ወደ ሕግ የመውሰድ መብት አላቸው፡፡ ይህን በተመለከተ በአብዛኛዎቹ ክልሎች ጥሩ ሁኔታ ላይ ናቸው ማለት ቢቻልም፣ 3 ክልሎች ላይ በተለይ በሁለቱ አሳሳቢ በሆነ ደረጃ ሥጋት ታይቷል፡፡  በአማራና በደቡብ ክልሎች የፖለቲካ ፓርቲዎች ወኪሎች ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ እንዳልቻሉ፣ እየተደበደቡና ባጅ እየተቀሙ እንደሆነ፣ የገዥው ሲቀር ከሁሉም ፓርቲዎች አቤቱታ ተቀብለናል ያሉት ወ/ሪት ብርቱካን፣ ይህ እንዲፈታ ለክልሉ አስተዳዳሪዎቸ መናገራቸውን ተስተካክሎ የፓርቲ ወኪሎች በቦታቸው ካልተገኙ የምርጫውን ተዓማኒነት አደጋ ላይ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል፡፡ 

ማስተካከያ በአፋጣኝ ማድረግ እንዳባቸው፣ የታችኛው ክፍልና አንዳንዴ የሕግ አስፈጻሚዎች ተግባሩን ከመፈጸም እንዲቆጠቡ ቦርዱ እንደሚያሳስብና ይህንን የሚያደርጉ አሁኑኑ መታቀብ እንዳለባቸው ቦርዱ ያሳውቃል ብለዋል፡፡

በዕጩዎች ወኪሎች ላይ የሚደረግ ሕገወጥ ተግባራት በውጤቱ ላይ ችግር ስላለው፣ ይህንን የመንግሥት አካላት ተገንዝበው ችግሩን የሚፈጽሙትን ዛሬ የሥራ ቀን ስላልሆነ ወደ ቤታቸው እንዲገቡ እንዲያደርጉ የጠየቁት የቦርድ ሰብሳቢዋ፣ ይህ ችግር በመለስተኛ ደረጃ በአፋርም ታይቷል ብለዋል፡፡ 

በአዎንታዊ መታየት ያለበትና ለሕዝቡም ለቦርዱም ትልቅ ድል ነው የሚባለው በአብዛኛው ጣቢያዎች ከጥቂቱ በስተቀር በሰዓት ተከፍተው በሰላም ምርጫው እየተከናወነና ዜጎችም እየመረጡ መሆኑን ነው፡፡ 

የቁሳቁስ እጥረት ያለበት ሳንካ ቢሆንም፣ የማይፈታ ችግር ስላልሆነ በአጭር ጊዜ ውስጥ ይስተካከላል፣ ቀጣዩን መግለጫ ስንሰጥ ችግሮቹ ይፈታሉ ብዬ አስባለሁ ብለዋል፡፡ ከሁሉም በላይ የፓርቲ ወኪሎች በየቦታው እየተገኙ ኃላፊነታችን እንዲወጡ አስቻይ ሁኔታ እንዲጠር ጠይቀዋል፡፡ አክለውም ችግሩ በስፋት የታየበት አዲስ አበባ፣ ደቡብ ክልል በሥራቸው የሚተዳደሩ ሠራተኞቻቸውን፣ አስተዳዳሪዎቻቸውንና ተወዳዳሪዎቻቸውን ጨምሮ ከማሰናከል ተግባር እንደታቀቡ እንዲያደርጉ ቦርዱ ጥሪ ያቀርባል ብለዋል፡፡ 

የፍርድ ውሳኔ ያላረፈበት ጉዳይ ያላቸው በርካታ ሰዎች እስር ቤት ቢኖሩም፣ በእስር ቤት የተቋቋመ ጣቢያ ስለሌለ ማንም እስረኛ ሊመርጥ የሚችልበት ሁኔታ እንደሌለ፣ አዲስ አበባ ላይ ለገጠመው ክፍተት እንዲሟላ ተደርጎ ምርጫው እየተካሄደ መሆኑን፣ ዘግይተው የጀመሩ ጣቢያዎችን በተመለከተ ቦርዱ ውሳኔ ማሳለፍ ስለሚችል ዓይቶ ሰዓት የሚራዘምበት ሁኔታ ላይ ውሳኔ እንደሚያሳልፍ በመግለጽ ወ/ሪት ብርቱካን የእኩለ ቀን መግለጫቸውን አጠናቀዋል፡፡ (ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics, Right Column Tagged With: birtukan midekssa, election 2013, election 2021

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    June 24, 2021 08:09 am at 8:09 am

    እንቅፋት የሌለበት ምርጫ በየትኛውም ዓለም ላይ ታይቶ አይታወቅም። ዲሞክራሲ ማለት የሙከራ ሂሳብ ማለት ነው። ለዚያም ነው በምድር ላይ ፍጽም ዲሞክራሲ የሰፈነበት ምድር የሌለው። በጊዜው በዲሞክራሲ ስም የሚሆነውን ያየው እውቁ ፈላስፋ ፕሌቶ ዲሞክራሲን ከተጸየፉት አንድ ነበር። ወደ እኛው የመከራ ምድር ስንመለስ ደግሞ በምድሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ተብሎ የተነገረን ጉድለት የለበትም ባይባልም ጅምሩ መልካም ነው። ግን ሲዘፈን ለሚያለቅስ፤ ሲለቀስ ለሚዘፍን እቡኝ ወገን ማር ነክ ነገር ሁሉ እሬት ነው። ስለዚህ መፍትሄ ሆኖ ከመቅረብ ይልቅ በ21ኛው ክፍለ ዘመን ዛሬም የጦር መሳሪያ ይዞ በየጫካውና ገደሉ እንዘጥ እንዘጥ እያሉ ራስን አሽብሮ ህዝብን የሚያምሱ የፓለቲካ ሙታኖች የሚራወጡባት ምድር ላይ ይህ ጎደለ ያ ተዛነፈ ማለት የመፍትሄው አካል ከመሆን ይልቅ የጠላት መሳሪያ መሆንና የህዝባችን ሰቆቃ ማባባስ ነው።
    በነጮቹ የዘመን መቁጠሪያ 1874 -1876 ክፉኛ ተደቁሳ ውርደት የተከናነበችው ግብጽ ዛሬም በሱዳን በኩል ዛቻና ማስፈራራት መጣሁ ደረስኩ ግድባችሁን አጋየዋለሁ በማለት ትራፊ ወያኔን ሌሎች ወስላቶችን አስታጥቃና አሰልጥና እንደገና አስርጎ በማስገባት የፓለቲካ ሴራዋን ተያይዛዋለች። በታንዛኒያ ጅሌስ ኔሬሬ የሃይል ማመንጫ ግድብ ፍጻሜ ላይ እንዲደርስ እርዳታ ቢጤ ጣል የምታረገው ግብጽ የሃበሻው ምድር በራሱ ወንዝ የራሱን ግድብ በራሱ እንዳይሰራ የማትፈነቅለው ድንጋይና የማትሸርበው ሴራ የለም። ለዚህም ድጋፍ እንዲሆናት ወታደራዊና ኢኮኖሚያዊ ትብብር በሚል በዪጋንዳ፤ በጅቡቲ፤ በሩዋንዳ፤ በቡሩንዲና በሱዳን ትስስር ፈጥራለች። ያው በየቀኑ ስለ ወያኔ የሚጮኹት ምዕራባዊያንም አረንጓዴ መብራት ለግብጽ ካበሩላት ቆይቷል። እንግዲህ ይህ ምርጫ የተካሄደው በዚሁ ሁሉ የውጭና የሃገር ውስጥ ሴራ ተከቦ ነው። ስለሆነም ሙከራውን ከማድነቅ ውጭ ሌላው ሁሉ የውስልትና ፓለቲካ ነው። በመሰረቱ ምርጫው ገና አልተጠናቀቀም። በጸጥታና በሌላም ምክንያት ምርጫ ያልተካሄደባቸው ስፍራዎች ገና ይመርጣሉ። ለጳጉሜ ተብሏል። ቆይቶ ማየት ነው።
    በዚህ ሁሉ የፓለቲካ እሰጣ ገባ ውስጥ ግን ዛሬም ከበሮና ክራር እየደበደቡ ጀግና ነን ኑ ግጠሙን ወዪላችሁ፤ ሂሳብ እናወራርዳለን የሚሉ የቁም ሙቶች መቼ ነው አይናቸው ተከፍቶ የሞትን ሽታ ማሽተት የሚያቆሙት? ብቀላ ብቀላን ይወልዳል እንጂ የሚወራረድ ሂሳብ የለውም። ሽንፈትን አምኖ ተቀብሎ መኖርም ጸጋ ነው። ዝም ብሎ ሁሌ ለህዝቤ፤ ለወገኔ፤ ለዘሬ፤ ለሃይማኖቴ የሚሉ ሰንካላ ፓለቲከኞች አንድም በዚህ ጥላ ሥር ተሰልፈው የዘየድት ነገር የለም። አይበቃም እስከ አሁን የተገዳደልነው? ሰው እንዴት ካለፈው አይማርም። የኮንጎውን ፓትሪስ ሉቡንቧን ገድለው ስጋውን በአሲድ ያቃጠሉት ነጮች አሁን አንድ ጥርሱ ተገኝታለች ተብሎ እሱን እንመልስ አንመልስ በማለት ግብግብ ላይ ናቸው። ፍትህ አለበት በሚባለው የአሜሪካ ምድር Native Indians ላይ የደረሰው ሰቆቃ መፈጠርን ያስጠላል። በካናዳ አሁን ራሱ እየተቆፈረ የሚወጣው የዚያው ሃገር Indigenous people አጽም ገና ብዙ ያፋልማል። በግዛቷ ጸሃይ አትጠልቅም የተባለችው ታላቋ እንግሊዝ ማሰሮ ውስጥ እንዳለ አንድ እቃ በአንዲት ደሴት ላይ ብቻ ተለጥፋለች። ጊዜ ሁሉን ይሽራል። ያልቆሰለ፤ ያላቆሰል ምንም መንግሥት የለም። ብዙ ማለት ይቻላል። ጥያቄው እንደ ውሻ ከተከመረ ቆሻሻ ላይ ጥንብ እያወጡ ከመናከስ እውነቱ ታውቆ ክፉ ነገሮች እንዳይደገሙ ህግና ደንብ አውጥቶ በሰላም መኖር አማራጭ አይገኝለትም። ሌላው ሁሉ ነፋስን እንደመከተል ነው።
    አሁን በምድሪቱ ብርቅዬ የሆነው ዘሩን፤ ቋንቋውና ሃይማኖቱን ወደ ኋላ ጥሎ ለአንድ ሃገርና ህዝብ የጋራ ደህንነት ልክ እንደ እውቁ ቡልቻ ደመቅሳ ሰንበቶ የሃገሪቱን ደህንነትና ሰላም የሚሻ ነው። ጭራሽ ሰው የለም እያልኩ ሳይሆን የገደሏት እየበሉ የሞቱላት የሚራቡባት ያቺ ምድር አካሄዷን ማስተካከል ይኖርበታል። ያው ወ/ሪት ብርቱካን እንዳለችው ምርጫው ለሃገርም ለቁጥር ለበዙት የፓለቲካ ፓርቲዎችም (ተሳተፉም አልተሳተፉም) ትምህርት ሰጪ ነው። በቃኝ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule