በኢትዮጵያ ጥልቅ አሳቢና ሩቅ አላሚ ትውልድ ለመፍጠር የንባብ ባህልን ማዳበር እንደሚገባ የአዲስ አበባ ባህል ኪነጥበባትና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ሂሩት ካሳ ገለጹ። የንባብ ባህልን ለማጎልበት ጥረት ቢደረግም የአንባቢው ቁጥር እስካሁን የሚታሰበውን ያክል አልደረሰም ብለዋል። “ንባብ ለሠላምና ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት በሚል” መሪ ሃሳብ በአብርኆት ቤተ-መጻሕፍት ከየካቲት 9 እስከ የካቲት 11 ቀን 2014 ዓ.ም የሚቆይ የንባብ ባህል ሳምንት ተጀምሯል። ለ4ተኛ ጊዜ በተካሄደው የንባብ ባህል ሳምንት ላይ የተገኙት ዶ/ር ሂሩት ካሳ፤ የንባብ ባህልን ለማጎልበት ጥረት ቢደረግም የአንባቢው ቁጥር የሚታሰበውን ያክል አልጨመረም ብለዋል። በንባብ ሳምንት ዝግጅቱ ላይ በርካታ አንባቢያን እንዲሳተፉ የተለያዩ ማነቃቂያዎች ቢደረጉም በርካታ አንባቢዎችን ለማፍራት አለመቻሉን … [Read more...] about የትግሬ ወራሪ ለ፳፯ ዓመት ያደነቆረውን ትውልድ ለመታደግ አዲስ የጸረ መሃይምነት ዘመቻ ሊጀመር ይገባል
News
ዜና
Deputy UN chief left near tears by “TPLF” rape accounts in Ethiopia
Press Conference by Deputy Secretary-General Amina Mohammed at United Nations Headquarters Following is a transcript of UN Deputy Secretary-General Amina Mohammed’s press conference on Ethiopia, held in New York today: Thank you very much. I did begin to speak with the press, for which I’m grateful, just as I left Addis [Ababa] — day before yesterday? I’m lost on time. I’m really just coming back from a country — it’s an incredible, amazing country that I was able to … [Read more...] about Deputy UN chief left near tears by “TPLF” rape accounts in Ethiopia
በአየርና በውሃ አካል ላይ የታገዘ ተልዕኮ ለመወጣት የሚያስችል ሥልጠና ባሕር ኃይል እየሰጠ ነው
የኢትዮጵያ ባህር ሃይል ዋና አዛዥ ተወካይ ኮሞዶር ዋላፃ ዋቻ፣ የሀገርን ደህንነት ለማስጠበቅ የሚያስችልና ከውስጥና ከውጭ የሚመጡ ችግሮችን የሚመክት ዘመናዊ ባህር ሃይል መገንባት፣ ማደራጀትና ማሰልጠን አስፈላጊ መሆኑን ተናገሩ፡፡ ኮሞዶሩ በባህር ዳር ተገኝተው የባህር ሃይል መሠረታዊ ባህረኞች በውሃ አካል ላይ የሚሰጡ ግዳጆችን ለመወጣት የሚያስችል የውሃ ዋና ሥልጠና ባስጀመሩበት ወቅት እንደተናገሩት፣ የውጭ ሃገራት የእጩ መኮንን ሥልጠናዎችን እና ደብረ ዘይት ባቦጋያ ት/ቤት የውሃ ዋና እና የመርከብ የተግባር ሥልጠናዎችን ማከናወን መቻሉን አስረድተዋል፡፡ አሁን የሚሰጣችሁ ሥልጠና በመርከብ ላይ ሊደረጉ የሚገቡ የጥንቃቄ፤ የአደጋ መከላከል ደንቦችና በውሃ አካል ላይ የሚሰጡ ግዳጆችን ሊያሳልጥ የሚችል ትምህርት በመሆኑ ጠቀሜታው የጎላ ነው ብለዋል፡፡ ይህ የስልጠና አቅም … [Read more...] about በአየርና በውሃ አካል ላይ የታገዘ ተልዕኮ ለመወጣት የሚያስችል ሥልጠና ባሕር ኃይል እየሰጠ ነው
የኢትዮጵያና የኬኒያ ፖሊስ ያደረጉት ስምምነት እንደምታ
ሸኔና አልሸባብ መደምሰሳቸው የጊዜ ጉዳይ ሆነ በፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ ግብዣ የኢፌዴሪ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በዩጋንዳ በተከበረው 41ኛው የሰራዊት ቀን ላይ ተገኝተው በዚያው ከዩጋንዳ የጸጥታ ሃይላት ጋር በሁለቱ አገሮች ድንበሮች ዙሪያ በዝግ መክረው መምጣታቸውን ተከትሎ ኢትዮጵያና ኬንያ በድንበር አካባቢ የሚንቀሳቀሱ የሸኔንና የአልሸባብ ሃይሎችን በጋራ ለመመከት መስማማታቸውን ይፋ አደረጉ። ዜናው በርካታ ጉዳዮችን የሚያነካካ በመሆኑ የገዘፈ ሆኗል። ምስራቅ አፍሪካን በንግድና በኢንቨስትመንት ለማቆራኘት እንዲቻል ቻይና በቀጥታ ከምታደርገው ከምታከናውነው ተግባሯ በተጨማሪ ቀጠናው የሰላም ኮሪዶር እንዲሆን አገራቱ ጸረ ሰላም ሃይሎችን በጋራ መመከት እንዲችሉ፣ አንዱ በሌላው ላይ ተቃዋሚ እንዳያደራጅ አቅዳ ልዩ ኮምቦይ መሰየሟን ማስታወቋ … [Read more...] about የኢትዮጵያና የኬኒያ ፖሊስ ያደረጉት ስምምነት እንደምታ
የኢትዮጵያ ደኅንነት የደቡብ ሱዳን ደኅነቶችን አሠልጥኖ አስመረቀ
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ከደቡብ ሱዳን አቻው ናሽናል ሴኩሪቲ ሰርቪስ ጋር በጋራ ለመስራት በደረሰው ስምምነት መሰረት ለሀገሪቱ የደኅንነት ተቋም አመራሮች በከፍተኛ የመረጃና ደህንነት አመራር ኪነሙያ ስልጠና በመስጠት አስመርቋል፡፡በብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ስር በሚገኘው ብሔራዊ የመረጃና ደኅንነት ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ስልጠና የወሰዱት የደቡብ ሱዳን የደኅንነት ተቋም አባላት የምረቃ ሥነ ስርዓት ላይ የተገኙት የአገልግሎት መሥሪያ ቤቱ ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ተመስገን ጥሩነህ የሁለቱ ሀገራት የደህንነት ተቋማት በመረጃ ልውውጥ፤ ሽብርተኝነትን በመዋጋት፤ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን በመቆጣጠር እና ህገወጥ የገንዘብ ዝውውርን በመከላከል ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን በጋራ ሲሰሩ መቆየታቸውን አስታውሰዋል፡፡አገልግሎት መሥሪያ ቤቱ የጋራ የደኅንነት ስጋቶችን ለማስወገድ እንዲሁም … [Read more...] about የኢትዮጵያ ደኅንነት የደቡብ ሱዳን ደኅነቶችን አሠልጥኖ አስመረቀ
ሸኔን ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እየተሰራ ነው
በፌደራል እና በክልል የፀጥታ ኃይሎች ጠንካራ እርምጃ ተወስዶበት ከተበታተነ በኋላ ንፁሃን ላይ ጥቃት እየፈፀመ ያለውን አሸባሪው ሸኔን ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እየተሰራ ነው ሲል የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ አስታወቀ። ጠንካራ የህዝብ አደረጃጀት በመፍጠር በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች በተሰራው ኦፕሬሽን የሽብር ቡድኑ ከበፊት ቁመናው እና ይዞታው መዳከሙን የቢሮው ኃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ጠቅሰዋል። ጠንካራ እርምጃ ተወስዶበት የተበታተነው አሸባሪው ቡድን በተለያዩ ቦታዎች ንፁሃንን የማጥቃት የተለመደ የጥፋት ድርጊቱን እየፈፀመ ነው ብለዋል። ይህን የጥፋት ድርጊቱን ለማስቆም በፌደራል እና በክልል የፀጥታ ኃይሎች በተቀናጀ መልኩ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ ቀጥሏል ነው ያሉት። በመንግሥት መዋቅር ላይ ሆነው ከአሸባሪው ሸኔ ጋር በማበር በህዝብ እና … [Read more...] about ሸኔን ለማጥፋት የተቀናጀ ስራ እየተሰራ ነው
የቦይንግ አዉሮፕላን በተከሰከሰበት ስፍራ ለተጎጂዎች መታሰቢያ ሊገነባ ነው
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ቁጥር ኢቲ 302 ቦይንግ 737-800 ማክስ አውሮፕላን የመከስከስ አደጋ በደረሰበት ስፍራ ለሚገነባው ሀውልትና ፓርክ የወጣውን ዓለም አቀፍ የንድፍ ውድድር የኢትዮጵያዊው አርክቴክት አለበል ደስታ ድርጅት አሸናፊ መሆኑ ታውቋል። በምስራቅ ሸዋ ዞን ግምቢቹ ወረዳ ለሚሰራው ይሄው የመታሰቢያ ሀውልት እና ፓርክ በ4 ሄክታር መሬት ላይ ሊገነባ የታሰበ ሲሆን ቦታው የማስታወሻ፣ የአረንጓዴ ቦታና የውጪ መሰብሰቢያ ስፍራ ያካተተ ነው ተብሏል። የአርክቴክት አለበል ደስታ ድርጅት ውድድሩን በማሸነፉ የ10 ሺህ ዶላር ሽልማት ሲያገኝ ሁለተኛ የወጣው ባይቦን አማካሪ አርክቴክቶችና መሀንዲሶች ድርጅት 7ሺህ ዶላር እንዲሁም በረከት ተስፋዬ አማካሪ አርክቴክቶችና መሀንዲሶች ድርጅት ሶስተኛ በመውጣት የ5 ሺህ ዶላር ተሸላሚ ሆነዋል። አርክቴክቱ ከዚህ ቀደምም … [Read more...] about የቦይንግ አዉሮፕላን በተከሰከሰበት ስፍራ ለተጎጂዎች መታሰቢያ ሊገነባ ነው
“ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ተቀራርበን እንሠራለን” የከተማ አስተዳደሩና ቤተክርስቲያኗ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በዛሬው ዕለት ውይይት አድርገዋል። ከውይይታቸው በኋላም የጋራ መግለጫ ሰጥተዋል። የመግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል። ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ እና ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጋራ የተሰጠ መግለጫ በዛሬው እለት የካቲት 8 ቀን 2014 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች በመስቀል አደባባይና በጃንሜዳ ባህረ ጥምቀት ቦታዎች በቀረቡ ጥያቄዎች ላይ የጋራ ውይይት አድርገናል፡፡ ውይይቱ በፍጹም ቅን ልቡና፣ መደማመጥና መግባባት በተሞላበት ስሜት ተካሂዷል፡፡ በመሆኑም በውይይቱ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመስቀል አደባባይና … [Read more...] about “ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ተቀራርበን እንሠራለን” የከተማ አስተዳደሩና ቤተክርስቲያኗ
ወደ ጎንደር ከተማ ሊገባ የነበረ 76 ቱርክ ሰራሽ ሽጉጥና 19 ሺህ ጥይት በቁጥጥር ሥር ዋለ
ከማዕከላዊ ጎንደር ዞን ሳንጃ ከተማ በሁለት ባጃጆች ተጭኖ በድብቅ ወደ ጎንደር ከተማ ሊገባ የነበረ 76 ቱርክ ሰራሽ ሽጉጥና 19 ሺህ ጥይት በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ፖሊስ አስታወቀ። ሽጉጡና ጥይቱ በቁጥጥር ሥር የዋለው በላይ አርማጭሆ ወረዳ ልዩ ስሙ "ኢትዮጵያ ካርታ" በተባለው ቦታ መሆኑን የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ፖሊስ መምሪያ የኮሙኒኬሽን ሚዲያ ዋና ክፍል ሃላፊ ኮማንደር እንየው ውብነህ ተናግረዋል። ትናንት ከቀኑ 7 ሰዓት አካባቢ በባጃጆች ተጭኖ ወደ ጎንደር ከተማ ለማስገባት ሲሞከር የፀጥታ ሃይሉ ባደረገው ድንገተኛ ፍተሻ መቆጣጠር መቻሉን አስታውቀዋል። ሽጉጡና ጥይቱ በሰሌዳ ቁጥር 1-25591 እና 1-39321 አ.ማ በሆኑ ሁለት ባለ ሦስት እግር ባጃጆች አማካኝነት ተደብቆ በመጓጓዝ ላይ ሳለ እንደተገኘ ኮማንደሩ ገልጸዋል። ኮማንደር እንየው እንዳሉት፤ በአሁኑ ወቅት … [Read more...] about ወደ ጎንደር ከተማ ሊገባ የነበረ 76 ቱርክ ሰራሽ ሽጉጥና 19 ሺህ ጥይት በቁጥጥር ሥር ዋለ
የትምህርት ሚኒስቴር እና ኢንሳ በጋራ ለመስራት መከሩ
ፈተና መስረቅ መላ ሊበጅለት ይሆን? የትምህርት ሚኒስቴር እና ኢመደኤ የሳይበር ደህንነትን ለማስጠበቅ በሚያስችሉ የምርምር፣ ልማት እና ስልጠናዎች ላይ በጋራ መስራት መከሩ። የትምህርትሚኒስቴር እና የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲን (ኢመደኤ) የሳይበር ደህንነትን ለማስጠበቅ በሚያስችሉ የምርምር፣ ልማት እና ስልጠናዎች ላይ በጋራ መስራት በሚያስችላቸዉ ጉዳይ ላይ መምከራቸው ተገለፀ። የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲን (ኢመደኤ) ጎብኝተዋል። በጉብኝታቸው ወቅት የኤጀንሲውን የሳይበር ተሰጥዎ ልማት ማዕከልን፣ በኤጀንሲዉ ለምተዉ በዲጂታል ኤግዚብሽን ማዕከል የቀረቡ ምርት እና አገልግሎትን እንዲሁም የኢመደኤ ሠራተኞችና የኃላፊዎችን ቢሮዎች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። ከጉብኝቱ ጎን ለጎን ሚኒስትሩ ከኢመደኤ ከፍተኛ … [Read more...] about የትምህርት ሚኒስቴር እና ኢንሳ በጋራ ለመስራት መከሩ










