• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢትዮጵያና የኬኒያ ፖሊስ ያደረጉት ስምምነት እንደምታ

February 15, 2022 10:55 am by Editor 2 Comments

ሸኔና አልሸባብ መደምሰሳቸው የጊዜ ጉዳይ ሆነ

በፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ ግብዣ የኢፌዴሪ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በዩጋንዳ በተከበረው 41ኛው የሰራዊት ቀን ላይ ተገኝተው በዚያው ከዩጋንዳ የጸጥታ ሃይላት ጋር በሁለቱ አገሮች ድንበሮች ዙሪያ በዝግ መክረው መምጣታቸውን ተከትሎ ኢትዮጵያና ኬንያ በድንበር አካባቢ የሚንቀሳቀሱ የሸኔንና የአልሸባብ ሃይሎችን በጋራ ለመመከት መስማማታቸውን ይፋ አደረጉ። ዜናው በርካታ ጉዳዮችን የሚያነካካ በመሆኑ የገዘፈ ሆኗል።

ምስራቅ አፍሪካን በንግድና በኢንቨስትመንት ለማቆራኘት እንዲቻል ቻይና በቀጥታ ከምታደርገው ከምታከናውነው ተግባሯ በተጨማሪ ቀጠናው የሰላም ኮሪዶር እንዲሆን አገራቱ ጸረ ሰላም ሃይሎችን በጋራ መመከት እንዲችሉ፣ አንዱ በሌላው ላይ ተቃዋሚ እንዳያደራጅ አቅዳ ልዩ ኮምቦይ መሰየሟን ማስታወቋ ይታወሳል። ከዚያም ቀደም ባለ ቀን ከኤርትራ ጋር ምጽዋን ለማልማት ሙሉ ስምምነት ማድረጓ አይዘነጋም።

ኢትዮጵያ ከኤርትራ፣ ከደቡብ ሱዳንና ጅቡቲ ጋር ያላት ግንኙነት አስተማማኝ እንደሆነ የሚናገሩ ክፍሎች በኬንያ እየተንቀሳቀሱ ያሉ፣ ከመካከል ሲጠቁ ወደዛ በመሸሽ የሚያገግሙ ሃይሎችን ለማክሰም ኢትዮጵያ ጥብቅ ስምምነት ማድረግ እንደሚገባት ሲያስታውቁ ቆይተዋል።

በቅርቡ የደቡብ ሱዳን ፈጥኖ ደረሽ የሚባለውን ሃይል የሚመሩትና የላዕላይ ምክር ቤቱ ምክትል ከሆኑት ጀነራል ጋር በመነጋገር ከሱዳን ጋር ያላውን ችግር በሰላም ለመፍታት ከስምምነት የደረሰችው ኢትዮጵያ ዛሬ ከኬንያ ጋር በይፋ በድነበር አካባቢ የሚነቅሳቀሱ ሃያላትን በጋራ ለመምታት ከስምምነት መድረሳቸውን ማወጃቸው ጉዳዩ ከሶማሌና ኦሮሚያ እንቅስቃሴ ጋር የሚገናኝ እንደሆነ ተመልክቷል።

ኢትዮጵያና ኬንያ በድንበር አካባቢ የሚንቀሳቀሱ የጥፋት ኃይሎችን በጋራ ለመመከት እንደሚሰሩ የሁለቱ አገራት የጸጥታ ዘርፍ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች መማማምታቸውን የመንግስት ሚዲያዎች አስታውቀዋል። ቀደም ሲል የኬንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ይህንኑ ብለው እንደነበር ይታወሳል። ዛሬ ይፋ የሆነው ዜና በድንበር በኩል ስላለው እንቅስቃሴ ያውራ እንጂ ናይሮቢ ቢሮ ያላቸውን ወገኖች አስመልክቶ ዝርዝር አላስታወቀም።

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል፤ የኬንያ ብሔራዊ ፖሊስ አገልግሎት ኢንስፔክተር ጀነራል ሄላሪ ሙትያምባይ ከዚህ ስምምነት የደረሱትና ይህንኑ ይፋ ያደረጉት አዲስ አበባ ፌዴራል ፖሊስ ጽህፈት ቤት በጋር በሰጡት መግለጫ ነው።

በውይይታቸውም በኢትዮጵያና ኬንያ ድንበር አካባቢዎች ሰላማዊ እንቅስቀሴ ለማረጋገጥ በጋራ የሚሰሯቸውን ሥራዎች ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች መምከራቸውን፣ በተለይም ደግሞ ኢትዮጵያና ኬንያ በጸጥታው ዘርፍ ተባብሮ በመሥራት በአካባቢው የሚንቀሳቀሰውን የአሸባሪው ሸኔ እኩይ ተግባር ለማክሸፍ በጋራ ለመስራት መስማማታቸውን አስታውቀዋል።

ኢንስፔክተር ጀነራል ሄላሪ ሙትያምባይ “ኢትዮጵያና ኬንያ የድንበር አካባቢዎችን ጸጥታና ሰላም ለመጠበቅ በጋራ መሥራት የሚያስችላቸው ሥምምነት ላይ ደርሰዋል” ሲሉ በጋራ መግለጫቸው ላይ በገሃድ አስታውቀዋል። አያይዘውም “የመረጃ ልውውጦችን በማሳደግና በማሻሻል በአካባቢው ያለውን ሰላም በጋራ እንጠብቃለን” ብለዋል።

ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል በበኩላቸው ኢትዮጵያና ኬንያ በድንበር አካባቢ የሚንቀሳቀሱ የጥፋት ኃይሎችን በጋራ ለመመከት መስማማታቸውን አመልክተዋል። በሁለቱ አገሮች አዋሳኝ አካባቢዎች የሸኔን እንዲሁም የአልሸባብን እንቅስቃሴ ለማስቆም የጋራ ዘመቻ እንደሚያካሂዱ ይፋ አድርገዋል። “የጋራ ዘመቻው ወይም ኦፕሬሽን ውጤታማ እንዲሆን ከአንድ ወር ባጠረ ጊዜ ኬንያ ላይ የመግባቢያ ሥምምነት እንፈራረማለን” ሲሉም ተናግረዋል።

በአካባቢው የሚንቀሳቀሰው የመከላከያ ሃይል ከትናንት በስቲያ ጀምሮ ስርነቀል ዘመቻ መጀመሩን፣ ቀደም ሲል ትኩረቱ ሁሉ ወደ ሰሜን ስለነበር ሸኔ የመስፋፋት ምልክት እንዳሳየ፣ አሁን ግን በአጭር ጊዜ ነገሮች መልካቸውን እንደሚይዙ ማስታወቃቸው ይታወሳል።

የሶማሌ ክልል ረብሻና ሁከት ለማካሄድ የሞከሩት ክፍሎች አመራሮቻቸው ዋና መኖሪያቸው ከቱርክ በተጨማሪ ኬንያ እንደሆነ በተደጋጋሚ መገለጹ ይታወሳል። ምን አልባትም ከአልሸባብ ጋር በተያያዘ በሚካሄደው ኦፕሬሽን ሊካተቱ እንደሚችሉ ይገመታል። (ETHIO12)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: federal police, Kenyan Police, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Comments

  1. gi haile says

    February 16, 2022 04:37 pm at 4:37 pm

    ዘግይተዋል ዶ/ር ኣቢይ ስልጣን በያዛ በወራት ውስጥ ይህ ድርድር ቢደረግ ኖሮ እጅግ መልካም ነበር። ኣሁንም ኣልዘገየም። የሕወኣት ዓለምአቀፍ የሕገወጥ ንግድ ስር የሰደደ የምስራቅ ኣፍሪካን ድንበር የሕገወጥ መሳሪያ ንግድ፣ሕገወጥ አደንዛዥ ዕዝ ዝወውር፣ ሕገወጥ የሰው ዝውውር፣ሕገወጥ ንግድ ለ27 ኣመታት የገነባው መረብ እጅግ ከባድ ነው ለሰው ዝውውር ከኢትዮጵያ እስካ ሰሜን ኣሜሪካ፣መካከለኛ ምስራቅ፣ኣውሮፓ፣ሰውዝ ኣፍሪካ ድረስ የዘለቀ የተደራጀ የምስጥር ድርጅት ከጀርባው ግን የውስጥም የውጭም ሃይላት ሕብረት ጋር የተቀናጀ ነው። በቀላሉ የከበሩበት መንገድ ነበር።
    ሕወኣት በሙስናና በማጭበርበር ታዋቂና ልምድ ያለው ስለሆነ የጠረፍ ፓሊሶች ጥንካሬ ገና አጠያያቂ ቢሆንም በደንብ የድንበር ፓሊሶች መንግስት ከከፈላቸው ችግሩ ቶሎ ይቀረፋል።
    Great Job Ethiopian Leader fof doung such amazing work .

    Reply
  2. hussen says

    March 5, 2022 01:50 pm at 1:50 pm

    yeh aynt hasab liberetata yigebal betam temechegn

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule