• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢትዮጵያና የኬኒያ ፖሊስ ያደረጉት ስምምነት እንደምታ

February 15, 2022 10:55 am by Editor 2 Comments

ሸኔና አልሸባብ መደምሰሳቸው የጊዜ ጉዳይ ሆነ

በፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ ግብዣ የኢፌዴሪ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በዩጋንዳ በተከበረው 41ኛው የሰራዊት ቀን ላይ ተገኝተው በዚያው ከዩጋንዳ የጸጥታ ሃይላት ጋር በሁለቱ አገሮች ድንበሮች ዙሪያ በዝግ መክረው መምጣታቸውን ተከትሎ ኢትዮጵያና ኬንያ በድንበር አካባቢ የሚንቀሳቀሱ የሸኔንና የአልሸባብ ሃይሎችን በጋራ ለመመከት መስማማታቸውን ይፋ አደረጉ። ዜናው በርካታ ጉዳዮችን የሚያነካካ በመሆኑ የገዘፈ ሆኗል።

ምስራቅ አፍሪካን በንግድና በኢንቨስትመንት ለማቆራኘት እንዲቻል ቻይና በቀጥታ ከምታደርገው ከምታከናውነው ተግባሯ በተጨማሪ ቀጠናው የሰላም ኮሪዶር እንዲሆን አገራቱ ጸረ ሰላም ሃይሎችን በጋራ መመከት እንዲችሉ፣ አንዱ በሌላው ላይ ተቃዋሚ እንዳያደራጅ አቅዳ ልዩ ኮምቦይ መሰየሟን ማስታወቋ ይታወሳል። ከዚያም ቀደም ባለ ቀን ከኤርትራ ጋር ምጽዋን ለማልማት ሙሉ ስምምነት ማድረጓ አይዘነጋም።

ኢትዮጵያ ከኤርትራ፣ ከደቡብ ሱዳንና ጅቡቲ ጋር ያላት ግንኙነት አስተማማኝ እንደሆነ የሚናገሩ ክፍሎች በኬንያ እየተንቀሳቀሱ ያሉ፣ ከመካከል ሲጠቁ ወደዛ በመሸሽ የሚያገግሙ ሃይሎችን ለማክሰም ኢትዮጵያ ጥብቅ ስምምነት ማድረግ እንደሚገባት ሲያስታውቁ ቆይተዋል።

በቅርቡ የደቡብ ሱዳን ፈጥኖ ደረሽ የሚባለውን ሃይል የሚመሩትና የላዕላይ ምክር ቤቱ ምክትል ከሆኑት ጀነራል ጋር በመነጋገር ከሱዳን ጋር ያላውን ችግር በሰላም ለመፍታት ከስምምነት የደረሰችው ኢትዮጵያ ዛሬ ከኬንያ ጋር በይፋ በድነበር አካባቢ የሚነቅሳቀሱ ሃያላትን በጋራ ለመምታት ከስምምነት መድረሳቸውን ማወጃቸው ጉዳዩ ከሶማሌና ኦሮሚያ እንቅስቃሴ ጋር የሚገናኝ እንደሆነ ተመልክቷል።

ኢትዮጵያና ኬንያ በድንበር አካባቢ የሚንቀሳቀሱ የጥፋት ኃይሎችን በጋራ ለመመከት እንደሚሰሩ የሁለቱ አገራት የጸጥታ ዘርፍ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች መማማምታቸውን የመንግስት ሚዲያዎች አስታውቀዋል። ቀደም ሲል የኬንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ይህንኑ ብለው እንደነበር ይታወሳል። ዛሬ ይፋ የሆነው ዜና በድንበር በኩል ስላለው እንቅስቃሴ ያውራ እንጂ ናይሮቢ ቢሮ ያላቸውን ወገኖች አስመልክቶ ዝርዝር አላስታወቀም።

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል፤ የኬንያ ብሔራዊ ፖሊስ አገልግሎት ኢንስፔክተር ጀነራል ሄላሪ ሙትያምባይ ከዚህ ስምምነት የደረሱትና ይህንኑ ይፋ ያደረጉት አዲስ አበባ ፌዴራል ፖሊስ ጽህፈት ቤት በጋር በሰጡት መግለጫ ነው።

በውይይታቸውም በኢትዮጵያና ኬንያ ድንበር አካባቢዎች ሰላማዊ እንቅስቀሴ ለማረጋገጥ በጋራ የሚሰሯቸውን ሥራዎች ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች መምከራቸውን፣ በተለይም ደግሞ ኢትዮጵያና ኬንያ በጸጥታው ዘርፍ ተባብሮ በመሥራት በአካባቢው የሚንቀሳቀሰውን የአሸባሪው ሸኔ እኩይ ተግባር ለማክሸፍ በጋራ ለመስራት መስማማታቸውን አስታውቀዋል።

ኢንስፔክተር ጀነራል ሄላሪ ሙትያምባይ “ኢትዮጵያና ኬንያ የድንበር አካባቢዎችን ጸጥታና ሰላም ለመጠበቅ በጋራ መሥራት የሚያስችላቸው ሥምምነት ላይ ደርሰዋል” ሲሉ በጋራ መግለጫቸው ላይ በገሃድ አስታውቀዋል። አያይዘውም “የመረጃ ልውውጦችን በማሳደግና በማሻሻል በአካባቢው ያለውን ሰላም በጋራ እንጠብቃለን” ብለዋል።

ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል በበኩላቸው ኢትዮጵያና ኬንያ በድንበር አካባቢ የሚንቀሳቀሱ የጥፋት ኃይሎችን በጋራ ለመመከት መስማማታቸውን አመልክተዋል። በሁለቱ አገሮች አዋሳኝ አካባቢዎች የሸኔን እንዲሁም የአልሸባብን እንቅስቃሴ ለማስቆም የጋራ ዘመቻ እንደሚያካሂዱ ይፋ አድርገዋል። “የጋራ ዘመቻው ወይም ኦፕሬሽን ውጤታማ እንዲሆን ከአንድ ወር ባጠረ ጊዜ ኬንያ ላይ የመግባቢያ ሥምምነት እንፈራረማለን” ሲሉም ተናግረዋል።

በአካባቢው የሚንቀሳቀሰው የመከላከያ ሃይል ከትናንት በስቲያ ጀምሮ ስርነቀል ዘመቻ መጀመሩን፣ ቀደም ሲል ትኩረቱ ሁሉ ወደ ሰሜን ስለነበር ሸኔ የመስፋፋት ምልክት እንዳሳየ፣ አሁን ግን በአጭር ጊዜ ነገሮች መልካቸውን እንደሚይዙ ማስታወቃቸው ይታወሳል።

የሶማሌ ክልል ረብሻና ሁከት ለማካሄድ የሞከሩት ክፍሎች አመራሮቻቸው ዋና መኖሪያቸው ከቱርክ በተጨማሪ ኬንያ እንደሆነ በተደጋጋሚ መገለጹ ይታወሳል። ምን አልባትም ከአልሸባብ ጋር በተያያዘ በሚካሄደው ኦፕሬሽን ሊካተቱ እንደሚችሉ ይገመታል። (ETHIO12)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: federal police, Kenyan Police, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Comments

  1. gi haile says

    February 16, 2022 04:37 pm at 4:37 pm

    ዘግይተዋል ዶ/ር ኣቢይ ስልጣን በያዛ በወራት ውስጥ ይህ ድርድር ቢደረግ ኖሮ እጅግ መልካም ነበር። ኣሁንም ኣልዘገየም። የሕወኣት ዓለምአቀፍ የሕገወጥ ንግድ ስር የሰደደ የምስራቅ ኣፍሪካን ድንበር የሕገወጥ መሳሪያ ንግድ፣ሕገወጥ አደንዛዥ ዕዝ ዝወውር፣ ሕገወጥ የሰው ዝውውር፣ሕገወጥ ንግድ ለ27 ኣመታት የገነባው መረብ እጅግ ከባድ ነው ለሰው ዝውውር ከኢትዮጵያ እስካ ሰሜን ኣሜሪካ፣መካከለኛ ምስራቅ፣ኣውሮፓ፣ሰውዝ ኣፍሪካ ድረስ የዘለቀ የተደራጀ የምስጥር ድርጅት ከጀርባው ግን የውስጥም የውጭም ሃይላት ሕብረት ጋር የተቀናጀ ነው። በቀላሉ የከበሩበት መንገድ ነበር።
    ሕወኣት በሙስናና በማጭበርበር ታዋቂና ልምድ ያለው ስለሆነ የጠረፍ ፓሊሶች ጥንካሬ ገና አጠያያቂ ቢሆንም በደንብ የድንበር ፓሊሶች መንግስት ከከፈላቸው ችግሩ ቶሎ ይቀረፋል።
    Great Job Ethiopian Leader fof doung such amazing work .

    Reply
  2. hussen says

    March 5, 2022 01:50 pm at 1:50 pm

    yeh aynt hasab liberetata yigebal betam temechegn

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule