• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢትዮጵያና የኬኒያ ፖሊስ ያደረጉት ስምምነት እንደምታ

February 15, 2022 10:55 am by Editor 2 Comments

ሸኔና አልሸባብ መደምሰሳቸው የጊዜ ጉዳይ ሆነ

በፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ ግብዣ የኢፌዴሪ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በዩጋንዳ በተከበረው 41ኛው የሰራዊት ቀን ላይ ተገኝተው በዚያው ከዩጋንዳ የጸጥታ ሃይላት ጋር በሁለቱ አገሮች ድንበሮች ዙሪያ በዝግ መክረው መምጣታቸውን ተከትሎ ኢትዮጵያና ኬንያ በድንበር አካባቢ የሚንቀሳቀሱ የሸኔንና የአልሸባብ ሃይሎችን በጋራ ለመመከት መስማማታቸውን ይፋ አደረጉ። ዜናው በርካታ ጉዳዮችን የሚያነካካ በመሆኑ የገዘፈ ሆኗል።

ምስራቅ አፍሪካን በንግድና በኢንቨስትመንት ለማቆራኘት እንዲቻል ቻይና በቀጥታ ከምታደርገው ከምታከናውነው ተግባሯ በተጨማሪ ቀጠናው የሰላም ኮሪዶር እንዲሆን አገራቱ ጸረ ሰላም ሃይሎችን በጋራ መመከት እንዲችሉ፣ አንዱ በሌላው ላይ ተቃዋሚ እንዳያደራጅ አቅዳ ልዩ ኮምቦይ መሰየሟን ማስታወቋ ይታወሳል። ከዚያም ቀደም ባለ ቀን ከኤርትራ ጋር ምጽዋን ለማልማት ሙሉ ስምምነት ማድረጓ አይዘነጋም።

ኢትዮጵያ ከኤርትራ፣ ከደቡብ ሱዳንና ጅቡቲ ጋር ያላት ግንኙነት አስተማማኝ እንደሆነ የሚናገሩ ክፍሎች በኬንያ እየተንቀሳቀሱ ያሉ፣ ከመካከል ሲጠቁ ወደዛ በመሸሽ የሚያገግሙ ሃይሎችን ለማክሰም ኢትዮጵያ ጥብቅ ስምምነት ማድረግ እንደሚገባት ሲያስታውቁ ቆይተዋል።

በቅርቡ የደቡብ ሱዳን ፈጥኖ ደረሽ የሚባለውን ሃይል የሚመሩትና የላዕላይ ምክር ቤቱ ምክትል ከሆኑት ጀነራል ጋር በመነጋገር ከሱዳን ጋር ያላውን ችግር በሰላም ለመፍታት ከስምምነት የደረሰችው ኢትዮጵያ ዛሬ ከኬንያ ጋር በይፋ በድነበር አካባቢ የሚነቅሳቀሱ ሃያላትን በጋራ ለመምታት ከስምምነት መድረሳቸውን ማወጃቸው ጉዳዩ ከሶማሌና ኦሮሚያ እንቅስቃሴ ጋር የሚገናኝ እንደሆነ ተመልክቷል።

ኢትዮጵያና ኬንያ በድንበር አካባቢ የሚንቀሳቀሱ የጥፋት ኃይሎችን በጋራ ለመመከት እንደሚሰሩ የሁለቱ አገራት የጸጥታ ዘርፍ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች መማማምታቸውን የመንግስት ሚዲያዎች አስታውቀዋል። ቀደም ሲል የኬንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ይህንኑ ብለው እንደነበር ይታወሳል። ዛሬ ይፋ የሆነው ዜና በድንበር በኩል ስላለው እንቅስቃሴ ያውራ እንጂ ናይሮቢ ቢሮ ያላቸውን ወገኖች አስመልክቶ ዝርዝር አላስታወቀም።

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል፤ የኬንያ ብሔራዊ ፖሊስ አገልግሎት ኢንስፔክተር ጀነራል ሄላሪ ሙትያምባይ ከዚህ ስምምነት የደረሱትና ይህንኑ ይፋ ያደረጉት አዲስ አበባ ፌዴራል ፖሊስ ጽህፈት ቤት በጋር በሰጡት መግለጫ ነው።

በውይይታቸውም በኢትዮጵያና ኬንያ ድንበር አካባቢዎች ሰላማዊ እንቅስቀሴ ለማረጋገጥ በጋራ የሚሰሯቸውን ሥራዎች ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች መምከራቸውን፣ በተለይም ደግሞ ኢትዮጵያና ኬንያ በጸጥታው ዘርፍ ተባብሮ በመሥራት በአካባቢው የሚንቀሳቀሰውን የአሸባሪው ሸኔ እኩይ ተግባር ለማክሸፍ በጋራ ለመስራት መስማማታቸውን አስታውቀዋል።

ኢንስፔክተር ጀነራል ሄላሪ ሙትያምባይ “ኢትዮጵያና ኬንያ የድንበር አካባቢዎችን ጸጥታና ሰላም ለመጠበቅ በጋራ መሥራት የሚያስችላቸው ሥምምነት ላይ ደርሰዋል” ሲሉ በጋራ መግለጫቸው ላይ በገሃድ አስታውቀዋል። አያይዘውም “የመረጃ ልውውጦችን በማሳደግና በማሻሻል በአካባቢው ያለውን ሰላም በጋራ እንጠብቃለን” ብለዋል።

ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል በበኩላቸው ኢትዮጵያና ኬንያ በድንበር አካባቢ የሚንቀሳቀሱ የጥፋት ኃይሎችን በጋራ ለመመከት መስማማታቸውን አመልክተዋል። በሁለቱ አገሮች አዋሳኝ አካባቢዎች የሸኔን እንዲሁም የአልሸባብን እንቅስቃሴ ለማስቆም የጋራ ዘመቻ እንደሚያካሂዱ ይፋ አድርገዋል። “የጋራ ዘመቻው ወይም ኦፕሬሽን ውጤታማ እንዲሆን ከአንድ ወር ባጠረ ጊዜ ኬንያ ላይ የመግባቢያ ሥምምነት እንፈራረማለን” ሲሉም ተናግረዋል።

በአካባቢው የሚንቀሳቀሰው የመከላከያ ሃይል ከትናንት በስቲያ ጀምሮ ስርነቀል ዘመቻ መጀመሩን፣ ቀደም ሲል ትኩረቱ ሁሉ ወደ ሰሜን ስለነበር ሸኔ የመስፋፋት ምልክት እንዳሳየ፣ አሁን ግን በአጭር ጊዜ ነገሮች መልካቸውን እንደሚይዙ ማስታወቃቸው ይታወሳል።

የሶማሌ ክልል ረብሻና ሁከት ለማካሄድ የሞከሩት ክፍሎች አመራሮቻቸው ዋና መኖሪያቸው ከቱርክ በተጨማሪ ኬንያ እንደሆነ በተደጋጋሚ መገለጹ ይታወሳል። ምን አልባትም ከአልሸባብ ጋር በተያያዘ በሚካሄደው ኦፕሬሽን ሊካተቱ እንደሚችሉ ይገመታል። (ETHIO12)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: federal police, Kenyan Police, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Comments

  1. gi haile says

    February 16, 2022 04:37 pm at 4:37 pm

    ዘግይተዋል ዶ/ር ኣቢይ ስልጣን በያዛ በወራት ውስጥ ይህ ድርድር ቢደረግ ኖሮ እጅግ መልካም ነበር። ኣሁንም ኣልዘገየም። የሕወኣት ዓለምአቀፍ የሕገወጥ ንግድ ስር የሰደደ የምስራቅ ኣፍሪካን ድንበር የሕገወጥ መሳሪያ ንግድ፣ሕገወጥ አደንዛዥ ዕዝ ዝወውር፣ ሕገወጥ የሰው ዝውውር፣ሕገወጥ ንግድ ለ27 ኣመታት የገነባው መረብ እጅግ ከባድ ነው ለሰው ዝውውር ከኢትዮጵያ እስካ ሰሜን ኣሜሪካ፣መካከለኛ ምስራቅ፣ኣውሮፓ፣ሰውዝ ኣፍሪካ ድረስ የዘለቀ የተደራጀ የምስጥር ድርጅት ከጀርባው ግን የውስጥም የውጭም ሃይላት ሕብረት ጋር የተቀናጀ ነው። በቀላሉ የከበሩበት መንገድ ነበር።
    ሕወኣት በሙስናና በማጭበርበር ታዋቂና ልምድ ያለው ስለሆነ የጠረፍ ፓሊሶች ጥንካሬ ገና አጠያያቂ ቢሆንም በደንብ የድንበር ፓሊሶች መንግስት ከከፈላቸው ችግሩ ቶሎ ይቀረፋል።
    Great Job Ethiopian Leader fof doung such amazing work .

    Reply
  2. hussen says

    March 5, 2022 01:50 pm at 1:50 pm

    yeh aynt hasab liberetata yigebal betam temechegn

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule