• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢትዮጵያና የኬኒያ ፖሊስ ያደረጉት ስምምነት እንደምታ

February 15, 2022 10:55 am by Editor 2 Comments

ሸኔና አልሸባብ መደምሰሳቸው የጊዜ ጉዳይ ሆነ

በፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ ግብዣ የኢፌዴሪ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ በዩጋንዳ በተከበረው 41ኛው የሰራዊት ቀን ላይ ተገኝተው በዚያው ከዩጋንዳ የጸጥታ ሃይላት ጋር በሁለቱ አገሮች ድንበሮች ዙሪያ በዝግ መክረው መምጣታቸውን ተከትሎ ኢትዮጵያና ኬንያ በድንበር አካባቢ የሚንቀሳቀሱ የሸኔንና የአልሸባብ ሃይሎችን በጋራ ለመመከት መስማማታቸውን ይፋ አደረጉ። ዜናው በርካታ ጉዳዮችን የሚያነካካ በመሆኑ የገዘፈ ሆኗል።

ምስራቅ አፍሪካን በንግድና በኢንቨስትመንት ለማቆራኘት እንዲቻል ቻይና በቀጥታ ከምታደርገው ከምታከናውነው ተግባሯ በተጨማሪ ቀጠናው የሰላም ኮሪዶር እንዲሆን አገራቱ ጸረ ሰላም ሃይሎችን በጋራ መመከት እንዲችሉ፣ አንዱ በሌላው ላይ ተቃዋሚ እንዳያደራጅ አቅዳ ልዩ ኮምቦይ መሰየሟን ማስታወቋ ይታወሳል። ከዚያም ቀደም ባለ ቀን ከኤርትራ ጋር ምጽዋን ለማልማት ሙሉ ስምምነት ማድረጓ አይዘነጋም።

ኢትዮጵያ ከኤርትራ፣ ከደቡብ ሱዳንና ጅቡቲ ጋር ያላት ግንኙነት አስተማማኝ እንደሆነ የሚናገሩ ክፍሎች በኬንያ እየተንቀሳቀሱ ያሉ፣ ከመካከል ሲጠቁ ወደዛ በመሸሽ የሚያገግሙ ሃይሎችን ለማክሰም ኢትዮጵያ ጥብቅ ስምምነት ማድረግ እንደሚገባት ሲያስታውቁ ቆይተዋል።

በቅርቡ የደቡብ ሱዳን ፈጥኖ ደረሽ የሚባለውን ሃይል የሚመሩትና የላዕላይ ምክር ቤቱ ምክትል ከሆኑት ጀነራል ጋር በመነጋገር ከሱዳን ጋር ያላውን ችግር በሰላም ለመፍታት ከስምምነት የደረሰችው ኢትዮጵያ ዛሬ ከኬንያ ጋር በይፋ በድነበር አካባቢ የሚነቅሳቀሱ ሃያላትን በጋራ ለመምታት ከስምምነት መድረሳቸውን ማወጃቸው ጉዳዩ ከሶማሌና ኦሮሚያ እንቅስቃሴ ጋር የሚገናኝ እንደሆነ ተመልክቷል።

ኢትዮጵያና ኬንያ በድንበር አካባቢ የሚንቀሳቀሱ የጥፋት ኃይሎችን በጋራ ለመመከት እንደሚሰሩ የሁለቱ አገራት የጸጥታ ዘርፍ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች መማማምታቸውን የመንግስት ሚዲያዎች አስታውቀዋል። ቀደም ሲል የኬንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ይህንኑ ብለው እንደነበር ይታወሳል። ዛሬ ይፋ የሆነው ዜና በድንበር በኩል ስላለው እንቅስቃሴ ያውራ እንጂ ናይሮቢ ቢሮ ያላቸውን ወገኖች አስመልክቶ ዝርዝር አላስታወቀም።

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል፤ የኬንያ ብሔራዊ ፖሊስ አገልግሎት ኢንስፔክተር ጀነራል ሄላሪ ሙትያምባይ ከዚህ ስምምነት የደረሱትና ይህንኑ ይፋ ያደረጉት አዲስ አበባ ፌዴራል ፖሊስ ጽህፈት ቤት በጋር በሰጡት መግለጫ ነው።

በውይይታቸውም በኢትዮጵያና ኬንያ ድንበር አካባቢዎች ሰላማዊ እንቅስቀሴ ለማረጋገጥ በጋራ የሚሰሯቸውን ሥራዎች ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች መምከራቸውን፣ በተለይም ደግሞ ኢትዮጵያና ኬንያ በጸጥታው ዘርፍ ተባብሮ በመሥራት በአካባቢው የሚንቀሳቀሰውን የአሸባሪው ሸኔ እኩይ ተግባር ለማክሸፍ በጋራ ለመስራት መስማማታቸውን አስታውቀዋል።

ኢንስፔክተር ጀነራል ሄላሪ ሙትያምባይ “ኢትዮጵያና ኬንያ የድንበር አካባቢዎችን ጸጥታና ሰላም ለመጠበቅ በጋራ መሥራት የሚያስችላቸው ሥምምነት ላይ ደርሰዋል” ሲሉ በጋራ መግለጫቸው ላይ በገሃድ አስታውቀዋል። አያይዘውም “የመረጃ ልውውጦችን በማሳደግና በማሻሻል በአካባቢው ያለውን ሰላም በጋራ እንጠብቃለን” ብለዋል።

ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል በበኩላቸው ኢትዮጵያና ኬንያ በድንበር አካባቢ የሚንቀሳቀሱ የጥፋት ኃይሎችን በጋራ ለመመከት መስማማታቸውን አመልክተዋል። በሁለቱ አገሮች አዋሳኝ አካባቢዎች የሸኔን እንዲሁም የአልሸባብን እንቅስቃሴ ለማስቆም የጋራ ዘመቻ እንደሚያካሂዱ ይፋ አድርገዋል። “የጋራ ዘመቻው ወይም ኦፕሬሽን ውጤታማ እንዲሆን ከአንድ ወር ባጠረ ጊዜ ኬንያ ላይ የመግባቢያ ሥምምነት እንፈራረማለን” ሲሉም ተናግረዋል።

በአካባቢው የሚንቀሳቀሰው የመከላከያ ሃይል ከትናንት በስቲያ ጀምሮ ስርነቀል ዘመቻ መጀመሩን፣ ቀደም ሲል ትኩረቱ ሁሉ ወደ ሰሜን ስለነበር ሸኔ የመስፋፋት ምልክት እንዳሳየ፣ አሁን ግን በአጭር ጊዜ ነገሮች መልካቸውን እንደሚይዙ ማስታወቃቸው ይታወሳል።

የሶማሌ ክልል ረብሻና ሁከት ለማካሄድ የሞከሩት ክፍሎች አመራሮቻቸው ዋና መኖሪያቸው ከቱርክ በተጨማሪ ኬንያ እንደሆነ በተደጋጋሚ መገለጹ ይታወሳል። ምን አልባትም ከአልሸባብ ጋር በተያያዘ በሚካሄደው ኦፕሬሽን ሊካተቱ እንደሚችሉ ይገመታል። (ETHIO12)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: federal police, Kenyan Police, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Comments

  1. gi haile says

    February 16, 2022 04:37 pm at 4:37 pm

    ዘግይተዋል ዶ/ር ኣቢይ ስልጣን በያዛ በወራት ውስጥ ይህ ድርድር ቢደረግ ኖሮ እጅግ መልካም ነበር። ኣሁንም ኣልዘገየም። የሕወኣት ዓለምአቀፍ የሕገወጥ ንግድ ስር የሰደደ የምስራቅ ኣፍሪካን ድንበር የሕገወጥ መሳሪያ ንግድ፣ሕገወጥ አደንዛዥ ዕዝ ዝወውር፣ ሕገወጥ የሰው ዝውውር፣ሕገወጥ ንግድ ለ27 ኣመታት የገነባው መረብ እጅግ ከባድ ነው ለሰው ዝውውር ከኢትዮጵያ እስካ ሰሜን ኣሜሪካ፣መካከለኛ ምስራቅ፣ኣውሮፓ፣ሰውዝ ኣፍሪካ ድረስ የዘለቀ የተደራጀ የምስጥር ድርጅት ከጀርባው ግን የውስጥም የውጭም ሃይላት ሕብረት ጋር የተቀናጀ ነው። በቀላሉ የከበሩበት መንገድ ነበር።
    ሕወኣት በሙስናና በማጭበርበር ታዋቂና ልምድ ያለው ስለሆነ የጠረፍ ፓሊሶች ጥንካሬ ገና አጠያያቂ ቢሆንም በደንብ የድንበር ፓሊሶች መንግስት ከከፈላቸው ችግሩ ቶሎ ይቀረፋል።
    Great Job Ethiopian Leader fof doung such amazing work .

    Reply
  2. hussen says

    March 5, 2022 01:50 pm at 1:50 pm

    yeh aynt hasab liberetata yigebal betam temechegn

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule