መስከረም 20፤ 2013 ዓም የትውልድ ዋርካ፤ የዘመናት ዕንቁ የሆኑትን የኔታ መስፍን ወልደ ማርያም ማረፋቸው ተሰምቷል። ስለ እርሳቸው ብዙ ማለት ይቻላል። ሞት ለማንም የማይቀር ቢሆንም ስለ እርሳቸው ዕረፍት እኛ ከምንናገረው በላይ ራሳቸው ስለ ሞት የተናገሩትን አትመነዋል። ከሁሉ በላይ “ዛሬም እንደ ትናንት” የተሰኘውን የመጨረሻ መጽሐፋቸውን ከሁለት ሳምንታት በፊት አሳትመው ማረፋቸው ለአገራቸው እስከመጨረሻው የተጉ የዘመናችን ዕንቁ! የኔታ መስፍን! የቅኔ ጌታ! የዕውቀት ገበታ! ቢባልላቸው በፍጹም የሚያንስባቸው አይደለም። የዛሬ ሦስት ዓመት ተኩል አካባቢ ጥር/2009 ስለራሳቸው ህይወትና ጻዕረሞት የጻፉትን በድጋሚ በማተም የስንብት ሐዘናችንን እንገልጻለን። ለቤተሰብ፣ ለዘመድ፣ ለወዳጅ፣ ለመላው የአገራችን ሕዝብ መጽናናትን እንመኛለን። ጎልጉል የድረገጽ … [Read more...] about የኔታ መስፍን ወልደ ማርያም የዘመን ዕንቁ! የትውልድ ዋርካ!
Archives for September 2020
“ጌታቸው አሰፋ ትሬዲንግ” በቢሊዮን የሚቆጠር የኮንትሮባንድ ዕቃዎች አስመጪና አከፋፋይ!
አቶ ፍፁም አባዲ በኢትዮጵያ አየርመንገድ የካርጎ ክፍል ሃላፊ፣ ምክትሉ አቶ ናትናኤል ጎበና እና የጌታቸው አሰፋ የቅርብ ዘመድ የሆነው አቶ ዮሃንስ አረጋይ በአየርመንገዱ የካርጎ ክፍል የሚሰሩ “የጌታቸው አሰፋ ትሬዲግ” ሰራተኞች ናቸው። በዱባይና ቻይና የሚገኙ የኢትዮጵያ አየርመንገድ የጭነት ወኪሎች፣ የቦሌ ጉሙሩክ ሃላፊ ከነበረው ከአቶ ገብረማርያም እስከ ጥበቃ ክፍል ሰራተኞች የሚደርሰው ሰንሰለት የጌታቸው አሰፋ የኮንትሮባንድ ንግድ ሰንሰለት ነው። እነ ጌታቸው አሰፋ ከስልጣን የተወገዱበትን ሚስጥር፤ ከሁሉም በላይ ደግሞ በህወሓቶች ስለሚፈፀመው ዘረፋና የኮንትሮባንድ ንግድ በተጨባጭ ማስረጃ የተደገፈ መረጃ ይፋ ወጥቷል። “የጌታቸው አሰፋ ትሬዲንግ” ከሶስት ወር ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ የ800 ሚሊዮን ብር ኮንትሮባንድ ዕቃዎችን በአየርመንገድ በኩል ግብር ሆነ ታሪፍ … [Read more...] about “ጌታቸው አሰፋ ትሬዲንግ” በቢሊዮን የሚቆጠር የኮንትሮባንድ ዕቃዎች አስመጪና አከፋፋይ!
ከአገር ሊወጣ የነበረ ከ132 ሺህ በላይ የአሜሪካን ዶላር 9.2 ኪሎ ኮኬይን በቁጥጥር ሥር ዋለ
በህገ-ወጥ መንገድ ከአገር ሊወጣ የነበረ 132 ሺህ 860 የአሜሪካን ዶላር እና 9.2 ኪሎ ግራም የሚመዝን ኮኬይን የተሰኘ አደንዛዥ እፅ በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት አስታውቋል። በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በቴክኖሎጂ ተደገፎ በተደረገ ጥብቅ ፍተሻና ክትትል ከአዲስ አበባ ወደ ናይጄሪያ ሊጓጓዝ የነበረ 9.2 ኪሎ ግራም ኮኬይን እንዲሁም መዳረሻውን ዝምባብዌ ያደረገ 132 ሺህ 860 የአሜሪካን ዶላር በቁጥጥር ስር መዋሉ ነው የተገለፀው። የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ለኢቲቪ በላከው መረጃ እንደገለጸው፤ በህገወጥ ድርጊቱ ተጠርጥረው የተያዙት ግለሰቦች በኢትዮጵያ ለቀናት ባደረጉት ቆይታ ከግብረአበሮቻቸው ጋር ግንኙነት በመፍጠር በህቡዕ ሲንቀሳቀሱ ነበር። ህገወጥ እንቅስቃሴዎችን ለመግታት መረጃዎችን መሰረት በማድረግ ክትትል … [Read more...] about ከአገር ሊወጣ የነበረ ከ132 ሺህ በላይ የአሜሪካን ዶላር 9.2 ኪሎ ኮኬይን በቁጥጥር ሥር ዋለ
በሙስና ተመዝብሮ በአገር ውስጥና በውጭ 130 ቢሊዮን ብር ተደብቆ እንደሚገኝ ተጠቆመ
መንግሥት በተለያዩ ሁኔታዎች በሙስና ወንጀል የተመዘበሩ ሀብቶችን ለማስመለስ ጥረት እያደረገ ቢሆንም፣ እስካሁን በተደረገ ጥናት በአገር ውስጥና በውጭ አገሮች ተደብቆ የሚገኝ ከ130 ቢሊዮን ብር በላይ ሀብት እንዳለ ተጠቆመ። የአመራር ለውጥ ከተደረገ ከሁለት ዓመታት ወዲህ ሙስናን ለመዋጋት መንግሥት የአገሪቱ ተቀዳሚ ተግባር አድርጎ እየተንቀሳቀሰ፣ የፖለቲካ ጣልቃ ገብነትም በተወሰነ ሁኔታ እየቀነሰና አጋር መንግሥታትና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ድጋፍና ተነሳሽነት የጨመረ ቢሆንም፣ በአገሪቱ ያለውን አለመረጋጋት እንደ ጥሩ አጋጣሚ በመውሰድ የሙስና ወንጀል በተደራጀ መልኩ እየተፈጸመ መሆኑም ተገልጿል። ሙስና በከፍተኛ ሁኔታ በተደራጀ ሁኔታ ተጠናክሮ መቀጠሉ የተነገረው፣ የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ከባለድርሻ አካላት ጋር መስከረም 14 ቀን 2013 ዓ.ም. በኢሊሌ ሆቴል ለሁለት ቀናት … [Read more...] about በሙስና ተመዝብሮ በአገር ውስጥና በውጭ 130 ቢሊዮን ብር ተደብቆ እንደሚገኝ ተጠቆመ
160 ሰዎች የሞቱበት፣ 360 ሰዎች የተጎዱበት፣ ከ4.6 ቢሊዮን ብር በላይ ንብረት የወደመበት የነጃዋር ክስ የወንጀል እንጂ የፖለቲካ እንዳልሆነ ተጠቆመ
ከድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ሥር ውለውና ክስ ተመሥርቶባቸው የሚገኙ ግለሰቦች ፖለቲከኞች ቢሆኑም፣ የታሰሩት በፖለቲካ እንቅስቃሴያቸው አለመሆኑን ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ አስታወቀ። የኢፌዴሪ ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) መስከረም 14 ቀን 2013 ዓ.ም. በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽሕፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪያት የውጭ ቋንቋዎችና ሚዲያ ኃላፊዋ ቢልለኔ ሥዩም ጋር በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደገለጹት፣ የጉዳዮች መገናኘት ካልሆነ በስተቀር፣ የታሰሩ ግለሰቦች ፖለቲከኞች ቢሆኑም ከፖለቲካ አመለካከትቸና እንቅስቃሴያቸው የታሰሩ እንዳልሆነ አብራርተዋል። ሰኔ 23 ቀን 2012 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ልዩ ስሙ ገላን ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በጥይት ተመትቶ የተገደለው ድምፃዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ ሞት ተከትሎ፣ በአዲስ አበባና በኦሮሚያ ክልል ከተከሰቱ አመፆችና … [Read more...] about 160 ሰዎች የሞቱበት፣ 360 ሰዎች የተጎዱበት፣ ከ4.6 ቢሊዮን ብር በላይ ንብረት የወደመበት የነጃዋር ክስ የወንጀል እንጂ የፖለቲካ እንዳልሆነ ተጠቆመ
አሸባሪነትን ለመዋጋት ፔንታጎን ከኢትዮጵያ መከላከያ ጋር በትብብር እየሠራ ነው
አሜሪካ 2 ነጥብ 9 ሚሊየን ዶላር የሚያወጡ የልምምድና ሌሎች ወታደራዊ ቁሳቀሶችን ለኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ድጋፍ ማድረጓን በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ አስታወቀ። ይህ ድጋፍ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በሶማሊያ የሚንቀሳቀሰው አልሸባብ የሽብር ቡድን እና ሌሎች የሽብር ድርጅቶችን ሊፈጥሩት የሚችሉትን አደጋዎች ለመመከት የሚያግዘው መሆኑ ተጠቁሟል። የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር (ፔንታጎን) ከኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስቴር ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን የገለፀው ኤምባሲው በተያዘው ዓመት የተደረገው ድጋፍም የዚሁ አካል ነው ተብሏል። ድጋፉም አምቡላንስ፣ ላንድ ክሮዘር፣ የእቃና የነዳጅ መጫኛ ተሸከርካሪዎችን እንዲሁም የምሽት አጉሊ መነፀር እንደሚያካትት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። ሽብርተኝነትን ከመከላከል ጋር ተያይዞ የተደረገ አንደኛው የድጋፍ አይነት ነው … [Read more...] about አሸባሪነትን ለመዋጋት ፔንታጎን ከኢትዮጵያ መከላከያ ጋር በትብብር እየሠራ ነው
ፌዴራል ፖሊስ የራሱ ሄሊኮፕተር እንዲኖረው ጠየቀ
የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በሲሲቲቪ እና በድሮን የታገዘ የጸጥታ ጥበቃ ስራዎችን ሊያከናውን መሆኑን አስታወቀ። ኮሚሽኑ ለህዝብ ጥያቄ ፈጣን ምላሽ ለመስጠት የሚስያችሉ ቴክኖሎጂዎችን ሊጠቀም መሆኑን አስታውቋል። ኮሚሽኑ ለህዝብ ጥያቄ ፈጣን ምላሽና አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ማሟላት ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫው መሆኑን አስታውቋል። የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ጀይላን አብዲ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንዳሉት የወንጀል መከላከል ስራን በሲሲ ቲቪ ካሜራ የተደገፈ እንዲሆን ማድረግ፣ ዘመናዊ የመገናኛ ራዲዮችን መጠቀም እንዲሁም ለወንጀል ምርመራ የሚስያፈልጉ በተለይ ለፎረንሲክ ምርመራ የሚውሉ ቴክኖሎጂዎችን፣ መሳሪያዎች፣ ሶፍትዌሮችን በማሟላት አገልግሎት ላይ እንዲውሉ ለማድረግ እየተሰራ ነው ብለዋል። ከዚህ ቀደም ፖሊስ በሀገሪቱ የሚከናወኑ ሀገራዊ፣ … [Read more...] about ፌዴራል ፖሊስ የራሱ ሄሊኮፕተር እንዲኖረው ጠየቀ
ተማሪዎቹ ከታገቱ ከ300 ቀናት አለፉ!
የሰብዓዊ መብት ተከራካሪ ተቋማት፣ የሴቶች ማህበራትና ድርጀቶች እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎች መንግስት ከደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ወደ ቤተሰቦቻቸው ሲመለሱ በታገቱ ተማሪዎች ጉዳይ ግልፅ መረጃ እንዲሰጥ ግፊት እያደረጉ አይደለም ተብሏል። በዛሬው (ማክሰኞ) ዕለት ተማሪዎቹ ከታገቱ ከ300 ቀናት ማለፉን አስመልክቶ በተሰናዳ የፓናል ውይይት ተካሂዷል። በውይይቱ የተለያዩ የሲቪል ማህበራት የሥራ ኃላፊዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮችና ታዋቂ ግለሰቦች ተካፍለዋል። የተማሪዎቹ የእገታ ጉዳይ መንግሥት የዜጎችን ሰብአዊ መብቶች በማስከበር እና የዜጎችን ደህንነት በማስጠበቅ ረገድ ያለበትን ክፍተት ያሳያል ተብሏል። በተለይም በተለያዩ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች እና በፀጥታው ዘርፍ በኩል ሲሰጡ የነበሩ የተጣረሱ መረጃዎች ከፍተኛ ክፍተት የታየባቸው እንደነበሩ ተነስቷል። ከመንግሥት … [Read more...] about ተማሪዎቹ ከታገቱ ከ300 ቀናት አለፉ!
ለተከሳሽ ጃዋርና ግብረአበሮቹ “ማንኛውም ሰው በሕግ ፊት እኩል ነው” የሚል ምላሽ ተሰጠ
ባለፈው ሳምንት ሰኞ መስከረም 11 ቀን 2013 ዓ.ም. አሥር የተለያዩ ክሶች የተመሠረተባቸው አቶ ጃዋር መሐመድን ጨምሮ 24 ተከሳሾች ክሱ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 20 ድንጋጌ መሠረት የተሰጣቸው ቢሆንም፣ በሥነ ሥርዓት ሕጉ አንቀጽ 129 ድንጋጌ መሠረት ክሱ ለተከሳሾቹ በችሎት መነበብ ስላለበት፣ በችሎት ለማንበብ ለመስከረም 20 ቀን 2013 ዓ.ም. ቀጠሮ ተሰጣቸው። ፍርድ ቤቱ ተከሳሾን ለመስከረም 14 ቀን 2013 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው፣ መስከረም 11 ቀን 2013 ዓ.ም. ያልቀረቡ ተከሳሾችን የፌዴራል ፖሊስ እንዲያቀርብና ክስ እንዲነበብላቸው የነበረ ቢሆንም ሳያቀርብ ቀርቷል። በእነ አቶ ጃዋር የክስ መዝገብ አምስተኛ ተከሳሽ የሆኑት አቶ ደጀኔ ጣፋ፣ 14ኛ ተከሳሽና በአሜሪካ አገር ነዋሪ የሆኑት አቶ ብርሃነ መስቀል አበበና አውስትራሊያ እንደሚኖሩ የሚነገረው አቶ ፀጋዬ … [Read more...] about ለተከሳሽ ጃዋርና ግብረአበሮቹ “ማንኛውም ሰው በሕግ ፊት እኩል ነው” የሚል ምላሽ ተሰጠ
ወደ ንግድ ባንክ በየቀኑ በአማካኝ ከ351 ሚሊዮን ብር በላይ ይገባል
ከብር ኖት ለውጡ ጋር በተያያዘ በአማካኝ በቀን ከ16 ሺ 700 በላይ ሰዎች አዲስ የሒሳብ ደብተር እንደሚከፍቱ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ። በየእለቱ በአማካኝ ከ351 ሚሊዮን ብር በላይ ወደ ንግድ ባንኩ ገቢ እንደሚሆን ገለጸ። የባንኩ የኮርፖሬት ኮሚኒኬሽን ተጠባባቂ ዳይሬክተር አቶ የአብስራ ከበደ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቁት፤ የብር ኖቱ መቀየሩ በባንኮች የሚቆጠበውንም ሆነ የሚቀመጠውን ብር ሆነ የደንበኞችን ቁጥር ያሳድጋል። ባንኩ ከ5ሺ ብር በላይ ለቅያሬ ይዘው የሚመጡ ሰዎች የቁጠባ ደብተር እንዲከፍቱ እያደረገ መሆኑን አመልክተው ፣ የቁጠባ ሒሳብ ደብተር የሚከፍቱ ሰዎች ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩን አስታውቀዋል። በቀን በአማካኝ ከ16ሺህ 700 በላይ ሰዎች የቁጠባ ሒሳብ እንዲከፈቱ ጠቁመው ፣ የቁጠባ ሂሳቡ በየእለቱ ከ351 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ … [Read more...] about ወደ ንግድ ባንክ በየቀኑ በአማካኝ ከ351 ሚሊዮን ብር በላይ ይገባል