የሰብዓዊ መብት ተከራካሪ ተቋማት፣ የሴቶች ማህበራትና ድርጀቶች እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎች መንግስት ከደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ወደ ቤተሰቦቻቸው ሲመለሱ በታገቱ ተማሪዎች ጉዳይ ግልፅ መረጃ እንዲሰጥ ግፊት እያደረጉ አይደለም ተብሏል። በዛሬው (ማክሰኞ) ዕለት ተማሪዎቹ ከታገቱ ከ300 ቀናት ማለፉን አስመልክቶ በተሰናዳ የፓናል ውይይት ተካሂዷል። በውይይቱ የተለያዩ የሲቪል ማህበራት የሥራ ኃላፊዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮችና ታዋቂ ግለሰቦች ተካፍለዋል። የተማሪዎቹ የእገታ ጉዳይ መንግሥት የዜጎችን ሰብአዊ መብቶች በማስከበር እና የዜጎችን ደህንነት በማስጠበቅ ረገድ ያለበትን ክፍተት ያሳያል ተብሏል። በተለይም በተለያዩ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች እና በፀጥታው ዘርፍ በኩል ሲሰጡ የነበሩ የተጣረሱ መረጃዎች ከፍተኛ ክፍተት የታየባቸው እንደነበሩ ተነስቷል። ከመንግሥት … [Read more...] about ተማሪዎቹ ከታገቱ ከ300 ቀናት አለፉ!