• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ተማሪዎቹ ከታገቱ ከ300 ቀናት አለፉ!

September 29, 2020 07:54 pm by Editor Leave a Comment

የሰብዓዊ መብት ተከራካሪ ተቋማት፣ የሴቶች ማህበራትና ድርጀቶች እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎች መንግስት ከደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ወደ ቤተሰቦቻቸው ሲመለሱ በታገቱ ተማሪዎች ጉዳይ ግልፅ መረጃ እንዲሰጥ ግፊት እያደረጉ አይደለም ተብሏል።

በዛሬው (ማክሰኞ) ዕለት ተማሪዎቹ ከታገቱ ከ300 ቀናት ማለፉን አስመልክቶ በተሰናዳ የፓናል ውይይት ተካሂዷል። በውይይቱ የተለያዩ የሲቪል ማህበራት የሥራ ኃላፊዎች፣ የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮችና ታዋቂ ግለሰቦች ተካፍለዋል።

የተማሪዎቹ የእገታ ጉዳይ መንግሥት የዜጎችን ሰብአዊ መብቶች በማስከበር እና የዜጎችን ደህንነት በማስጠበቅ ረገድ ያለበትን ክፍተት ያሳያል ተብሏል።

በተለይም በተለያዩ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች እና በፀጥታው ዘርፍ በኩል ሲሰጡ የነበሩ የተጣረሱ መረጃዎች ከፍተኛ ክፍተት የታየባቸው እንደነበሩ ተነስቷል።

ከመንግሥት ባሻገር በሌሎች የሴቶች እና የህፃናት ጉዳዮች ላይ በጉልህ ሲንቀሳቀሱ የሚታዩ የሚመለከታቸው አካላትም ይህን ጉዳይ በተለየ ችላ ማለታቸው በውይይቱ ተነግሯል።

አሁንም ቢሆን የታጋች ተማሪዎቹ ነገር እልባት እንዲያገኝ በመንግሥት ላይ ጫና ማሳደር ያስፈልጋል ተብሏል፡፡ መንግስትም በጉዳዩ ላይ ያለውን መረጃ ግልፅ ሊያደርግ እና የዜጎችን ደህንነት የመጠበቅ ኃላፊነቱን ሊወጣ እንደሚገባ ተነግሯል። (ሸገር ኤፍኤም)

እነዚህ ተማሪዎች በታገቱ ሰሞን ጎልጉል ““ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች” በሚል ርዕስ ቢቢሲን በመጥቀስ አንድ መረጃ አውጥቶ ነበር። እንዲህ ይነበባል፤

ዓይን አፍጥጦ ወጥቶ የነበረ ነገርግን ሆን ተብሎ ትኩረት እንዳይሰጥበት የተደረገው ነገር ቢቢሲ አስቀድሞ ያወጣውና ከታጋች ወላጆች መካከል አንድኛው አባት የተናገሩት ነበር፤ “… ከእንግዲህ ከሷ ጋር መገናኘት እንደማልችል ነገረችኝ” ካሉ በኋላ “እና ታዲያ ምን አሏችሁ? ብዬ ስላት “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን”” አለችኝ ብለው ነበር ምስክርነታቸውን የሰጡት። ይህ ፍንትው ያለ እውነታ ለምን ትኩረት አልባ ሆነ?    

አሁንም የእነዚህን ታጋቾች በተመለከተ ያልተነገረ ብዙ ምሥጢር አንዳለ ሲነገር ይሰማል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Left Column, Politics, Social Tagged With: dembidolo university, kidnapped students

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule