• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች

February 11, 2020 07:53 pm by Editor Leave a Comment

የሙያው ባለቤቶችና ተመራማሪዎች ታጋቾችን ማስለቀቅ ራሱን የቻለ ታላቅ ጥበብና ስልት ይጠይቃል ይላሉ። የአጋቾችን ስነልቡና ለመስረቅ፣ ለማለስለስ፣ ወዘተ አደራዳሪዎች ፈጽሞ ሊታሰቡ የማይችሉ የሚባሉ ዘዴዎችን ሲጠቀሙ ይስተዋላሉ። የአጋቾቹን ፍቅረኛ ወይም እናት ወይም ሌላ ተወዳጅ የቤተሰብ አባል ወደ ዕገታው ቦታ በማምጣት በድምጽ ማጉያ የተማጽንዖ ቃል እንዲናገሩ ይደረጋሉ። የሃይማኖት መሪዎች፣ ሽማግሌዎች፣ ሌሎች ተጽዕኖና አመኔታ ሊጣልባቸው የሚችሉ ሰዎች በዚህ እንዲሳተፉ ይደረጋል። ይህንና ሌሎች መሰል ተግባራትን በመጠቀም የታገቱት ያለ አንዳች ችግር በነጻ እንዲወጡ ሙከራ ይደረጋል። በዚህም ምክንያት ረጅም ጊዜ የሚወስድ ዕገታ በሰላም የመጠናቀቅ ዕድሉ በጣም ከፍተኛ ነው ይባላል። 

ማፈን፣ ማገት፣ ሰዎችን ያለፈቃዳቸው በቁጥጥር ሥር ማዋል፣ ወዘተ ያልተለመደ ተግባር አይደለም። በአብዛኛው የጤና ችግር ያለባቸው፣ አእምሯቸው የተቃወሰ፣ ከአእምሮ ሐኪም ቤት ያመለጡ ወይም መግባት ሲገባቸው ሳይገቡ የቀሩ፣ አሸባሪዎች፣ የጥቃት ሰለባዎች፣ ወንጀለኞች፣ እስረኞች፣ የፖለቲካ ዓላማ ያላቸው እና ሌሎችም በማገት ተግባራት እንደሚሰማሩ በየጊዜው የሚወጡ ዘገባዎች ይጠቁማሉ። የአብዛኛዎቹ ዓላማም በሰላማዊና ሕጋዊ መንገድ ለማስከበር ያልቻሉትን እጅ በመጠምዘዝ ለማስፈጸም ሲሆን ጥቂት የማይባሉ ደግሞ ተፈጸመብን የሚሉትን ግፍ ለመበቀል የሚፈጽሙት ተግባር ሆኖ እናገኘዋለን። በየትኛውም መንገድ ቢሆን አእምሮው እጅግ የተቃወሰበት፣ የሚፈልገውን የማያውቅ፣ ካልሆነ በስተቀር አጋች ዓላማ አለው፤ በተለይ ደግሞ የፖለቲካ አጋቾች በምክንያት ነው የሚያግቱት፤ ይህንንም ዓለም እንዲሰማቸው የሚችሉትን ያህል “ይጮኻሉ”።

በዓለማችን በየቀኑ ከሁለት ሺህ በላይ ህጻናት የደረሱበት እንደማይታወቅ ይህም ከማገት ጀምሮ እስከ ሕገወጥ የሰው ዝውውር እስከ ግድያ እንደሚደርስ ዘገባዎች ያስረዳሉ። በሌላው በኩል ከፖለቲካ ጋር የተያያዙ ዕገታዎች ለዘመናት ሲፈጸሙ የኖሩ ሲሆን አንዳንዶቹ ከጥቂት ሰዓታት በላይ ያልወሰዱ ቢሆንም ሌሎች ብዙዎች ግን በርካታ ዓመታትን ያስቆጠሩ ሆነዋል።

ቴሪ ዌይት የተባለ የእንግሊዝ ቤ/ክ ተደራዳሪ በሊባኖስ የታገቱ አራት ሰዎችን በሽምግልና ለማስለቀቅ ወደ ሊባኖስ ካመራ በኋላ ሒዝቦላ ሰላይ ነው ብሎ በመጠርጠር አገተው። በመጨረሻም ለ1,763 (ከአራት ½ ዓመት) በኋላ ከታገቱት ጋር ተለቅቋል። “የኢራን የዕገታ ቀውስ” ተብሎ በሚጠራው ኢራን ያገተቻቸውን አሜሪካውያን ከ444 ቀናት በኋላ ለቅቃለች። ቼቺኒያ ከሩሲያ ጋር ጦርነት ውስጥ በነበረችበት ጊዜ በርካታ ሰዎች (ህጻናትም ጭምር) የሞቱበት የተለያዩ ዕገታዎች ተካሂደዋል፤ 800 ሰዎች የታገቱበትና ከመቶ በላይ ሞተው የተጠናቀቀው የሞስኮ ቴአትር ዕገታ እንዲሁም ከ350 በላይ ህጻናትን ህይወት የቀጠፈው የቤስላን ት/ቤት ዕገታ ጥቂቶቹ ተጠቃሾች ናቸው። በእነዚህና ሌሎች ዕገታና አፈናዎች ሁሉ አፋኞቹ ወይም አጋቾቹ ፍላጎታቸው ምን እንደሆነ በግልጽ ይናገራሉ፤ ዓለም እንዲሰማላቸውም ያደርጋሉ። 

ለበርካታ ቀናት ባልታወቁ “ሽፍቶች” የታገቱት የደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከታገቱ በርካታ ሳምንታት በኋላ ሚዲያውን አጨናነቀ። ባልታሰበ ፍጥነት እያደገም መጥቶ በአገርና ዓለም አቀፍ ደረጃ የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ አስደረገ። እጅግ በርካታ ሕዝብ በተለይ በአማራ ከተሞች ወጣ፤ አክቲቪስቶች የሚባሉቱም በሽሙጥ በለውጡ ኃይል በተለይም በጠቅላይ ሚኒስትሩ አሸሞሩ፤ እርስዎን የሚጠብቀው ሪፓብሊካን ዘብ ታጋቾችን ማስፈታት እንዴት አቃተው በማለት ዕውቀትን የጾመ ልመና አቀረቡ፤ እናቶች ይጸልዩልኛል እያሉ እንዴት ሴቶች ልጆች ሲታገቱ ዝም ማለት አስቻለዎት በማለት ጠቅላዩን “ትህትና” በተላበሰ ሽሙጥ ወረፉ፤ ንጉሡ ጥላሁንም አልቀረላቸውም፤ ጸረ አማራ ተባሉ። በየማኅበራዊ ሚዲያውም ዘመቻው ቀጠለ።

ዓይን አፍጥጦ ወጥቶ የነበረ ነገርግን ሆን ተብሎ ትኩረት እንዳይሰጥበት የተደረገው ነገር ቢቢሲ አስቀድሞ ያወጣውና ከታጋች ወላጆች መካከል አንድኛው አባት የተናገሩት ነበር፤ “… ከእንግዲህ ከሷ ጋር መገናኘት እንደማልችል ነገረችኝ” ካሉ በኋላ “እና ታዲያ ምን አሏችሁ? ብዬ ስላት “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን”” አለችኝ ብለው ነበር ምስክርነታቸውን የሰጡት። ይህ ፍንትው ያለ እውነታ ለምን ትኩረት አልባ ሆነ?    

እንደሚታወቀው አጋች ዓላማ ስላለው ያገተበትን ዓላማ በመግለጽ የሚቀድመው አይኖርም። በዘመናችን እንዲያውም ያለውን ሚዲያ በመጠቀም አጋች ፍላጎቱን ዓለም እንዲሰማው ያደርጋል። በየጊዜውም ያገተውን እያስፈራራ የቪዲዮና የፎቶ መረጃ ይለቃል፤ ይህንን ካላደረጋችሁልኝ ይህንን አደርጋለሁ እያለ ይፎክራል። በደምቢዶሎው ግን ይህንን መሰሉ ድርጊት ሲፈጸም አልታየም። እንዲያውም ባልተለመደ ሁኔታ አጋቹ ዓይናፋር ይመስል መሰወርና አለመታወቅን ነው የመረጠው።

የሚፈልጉትን ባለማግኘታቸው አገራችንን ለማፍረስ እየጣሩ ያሉና ዓላማቸውንም ለማሳካት በትጋት የሚሠሩት ሩቅ ሳይሆን እዚሁ ቅርብ ያሉ ናቸው። ጽንፈኛ ብሔረተኞችና በይፋ የሚታወቁ ድርጅቶች በተለይ በአማራና በኦሮሞ ክልል የሚገኙ ከህወሓት ጋር የሚለያቸው እታገልለታለሁ የሚሉት ብሔር ስም መለየት ብቻ ስለሆነ ከህወሓት ጋር አይወግኑም፤ በአጀንዳ አይስማሙም ብሎ ማሰብ የፖለቲካ ጨቅላነት ነው።   

የታጋች አባት ያሉትን በድጋሚ እናጢን፤ “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን”!!

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ™” አቋም ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Editorial, Right Column Tagged With: jawar massacre, Right Column - Primary Sidebar, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule