• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሕዝብ ከስሜትና ከተራ ብሽሽቅ በመራቅ በያለበት የአገሩ ዘበኛ ይሁን!

June 28, 2018 11:30 pm by Editor 2 Comments

ቀደም ሲል በሃዋሳ፣ ባለፈው ቅዳሜ በመስቀል አደባባይ በተቀነባበረ ሁኔታ የደረሰውን የቦንብ ፍንዳታ፣ በቤኒሻንጉል በተለያዩ ቦታዎችና በተለይም በአሶሳ የደረሰንና እየደረሰ ያለውን የዘር ማጥራት ጭፍጨፋ፣ ሕዝብ ወደ ምሬት እንዲሄድ ሆን ተብሎ የሚደረግ የኢኮኖሚ አሻጥር፣ በጥሞና ለምትከታተሉ ሁሉ፤

በባህር ዳር ለጠቅከላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ ቀና ተግባርና የለውጥ ሩጫ እውቅና ለመስጠት የተጠራውን ሰልፍ ለማወክ ከወዲሁ ቦንብ ሲያዘዋውሩ መያዛቸውን ለሰማችሁ፣ የደኅንነት ኃይሉን ትብትብ በወጉ ለምትረዱና ለምትገነዘቡ፤ በተለያዩ የአገሪቱ የልማት ተቋማት ላይ የሚፈጸመውን የኢኮኖሚ አሻጥር በውል ለምትከታተሉ፤ ህዝብን ከህዝብ ጋር ለማጋጨት የሚሸረቡ ተንኮሎችን ለምታጤኑ፤ ለውጡ እንዲኮላሽና አገሪቱ ወደ ትርምስ ውስጥ እንድትገባ በተሸናፊነት ውስጥ ሆነው ለጥፋት የሚመደበውን በጀት ለምትሰሙ …. በጥቅሉ አሁን እየሆነ ያለውን ለምታስተውሉ አገር ወዳድ ዜጎች የጎልጉል ዝግጅት ክፍል አጭር መልዕክት አለው።

እየሆነ ባለው የለውጥ ሂደት ቀልብን ሰብስቦ በማሰብ፣ ልብን በመጠበቅ፣ በየመኖሪያና በየሥራው ቦታ፣ በአለፍንበትና ባገደምነበት ሁሉ የአገራችን ዘበኛ ልንሆን ይገባል። በተራ ብሽⶥቅና እንካ ሰላንቲያ የሚገኝ ትርፍ የለምና እንዲህ ያለውን የሰንፎች መንገድ ካልተውን ተሸናፊዎች አጀንዳና እጅ ተመልሰን እንወድቃለን።

አሁን ጊዜው ዋጋ የሚከፈልበት ነው። አሁን ጊዜው ከቀድሞው መስዋዕትነት በላይ ዋጋ ለመክፈል የምንምልበት ነው። ፍቅር ያሸንፋል ሲባል፣ ከክፉ መንገዳቸው የተመለሱትን ከነጸጸታቸው መቀብል እንጂ መግፋት አይደለምና በአገር ደረጃ ለታወጀው የሰላም መንገድ፣ የድል መንገድ፣ የዕርቅ መንገድ ክፉዎች የሚወድቁበት ወጥመድ ይህ የፍቅር መንገድ ብቻ በመሆኑ በማስተዋል እንራመድ።

በየድረገጹና በየማኅበራዊ ሚዲያ የሚታየው፣ የሚነበበው ተራ የብሽሽቅ ፖለቲካ ብስጭት ውስጥ ያሉትን የበለጠ እንዲያመርሩ፤ ያልገቡትን ደግሞ ወደዚያው እንዲገቡ የሚገፋፋ ነው ሰከን እንበል። ያለንበት ሁኔታ “ተራው የኔ ነው” የሚያስብል ሳይሆን አገር ለማዳን የምንጨነቅበት፤ የምንችለውን ሁሉ ቀንና ሌሊት የምሠራበት ነው። በርግጥ ላለፉት በርካታ ዓመታት ለአገራችን ስንለፋ ከነበርን ይህ የታየው ለውጥ ፍሬ እንዲያፈራ ይበልጡኑ የምንተጋበት ጊዜ አሁን ነው።

በስሜት እየተንቦጫረቅን ከተቀመጠው ዋንኛ የድል መንገድ የምንወጣ ከሆነ መፈረካከስ ይሆናልና በጥሞና ወደ ድልና መደመር የሚወስደንን ጎዳና አንልቀቅ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት ለለውጡ መቀጠል ሁላችንም በተግባር የሚጠበቅብንን እንወጣ። አሁን የጥፋት ኃይሎች ሆነው ብቅ ያሉት ያለ ከልካይ እንደመዥገር ተጣበቀው ሲጠቧት የነበረችውን አገር እንዲለቅቁ እየተደረጉ ነውና በቀላሉ ለመልቀቅ ፈቃደኞች ይሆናሉ ብሎ መገመት የዋህነት ነው። ይህ ለውጥ ለአብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ የመኖርን ትርጉም ፍንትው አድርጎ ያሳየ የመሆኑን ያህል ለነዚህ ኃይሎች ደግሞ የዚህ ተቃራኒ ነው የሆነባቸው። ስለዚህ በለውጡ ሒደት በፍጥነት ወደፊት ከምንገሰግስ ይልቅ እሣት ወደ ማጥፋት እንድንሄድና በሒደትም መንገዳችንን እንድንስት እንደሚያደርጉን ጠንቅን ልንገነዘብ ያስፈልጋል።

እነዚህ የተቀናጁ፣ የተደራጁ፣ ለዘመናት ሲዘርፉት በነበረው በርካታ የገንዘብ ኃይል የሚደገፉ፣ ለአገር ደኅንነት ቅንጣት ያህል የማይጨንቃቸው ኃይሎችን በስሜት፣ በግብታዊነት፣ በበቀል፣ በእልህና በንዴት ሳይሆን አካሄዳቸውን በማጥናት፣ በብልሃትና በትጋት ነቅተን የምንታገልበት ወሳኝ ሰዓት ላይ ነን። የተጀመረው የለውጥና የተሃድሶ ጉዞ መስቀለኛ መንገድ ላይ መሆኑን በመገንዘብ ለድል እናምርር።

ስለዚህ ባለሙያዎችም አገራችሁን የምትረዱበት ወቅት አሁን ነውና ኢትዮጵያን በማዳኑ የቀና መንገድ ያለ አንዳች ይጥቅም የበኩላችሁን ተወጡ። አገራችሁ ትፈልጋችኋለች፤ የትኛውም ዓይነት የሙያ ልምድ ይሆን ትምህርት በአሁኔ ጊዜ ያስፈልጋልና በሁሉም መስክ ተደመሩ። በሚዲያ ላይ ያላችሁ በማኅበራዊ ድረገጾችም ይሁን በድረገጾችና በመካነ ጦማሮች ላይ የምትሳተፉ፣ አስተያየት የምትሰጡ የብሽሽቅ ፖለቲካውን ባካችሁን አርግቡት፤ ከጥቅሙ ጉዳቱ ነው የሚበልጠውና ይቅርባችሁ። የዓመታት ግፍ በርግጥ ብዙ እንዲባል ያስገድዳል ግን ደግሞ ውጤቱ መልሶ እኛኑ የሚጎዳ ከሆነ መተዉ የተሻለ ይሆናል። አሁን እየጎላ የመጣውን የለውጥና የመኖር ተስፋ፣ ተመልሶ ኢትዮጵያዊ የመሆን ታላቅ ዕድል ለማፈራረስ የማይማስ ጉድጓድ የለምና ሁሉም ዘብ ይቁም!!


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ™” አቋም ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: abiy ahmed, eprdf, Left Column, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Lemma says

    July 1, 2018 10:26 pm at 10:26 pm

    Yibarkachihu. BeTam Teqami melikt new. TPLF is now like a grotesque rabid dog. It barks and bites at any thing, including, at last, its own tail to finish itsel off.
    Degagmachehu hizbun mikeru. Bertu Golguloch.

    Reply
  2. Ezira says

    July 2, 2018 07:27 pm at 7:27 pm

    ትክክል ነው። አንዲት የተቆጣች ድመት የመዉጫውን በር ከዘጋህባት ያላት አማራጭ ከአንት ላይ መጎመር ነው። ስለዚህ ከምንም በላይ አገራችን ኢትዮጵያን መጠበቅና ለ27 ዓመት ከተቀበረችበት መቃብር ፈንቅላ እየወጣች ነችና …ይሄንን የመቃበሯን ድንጋይ ላይዋ ላይ ልናነሳላት የምንችለው በጋራ ሆነን ጠ/ር ዶ/ር አብይ እንዳሉት በመደመርና በመደመር ብቻ ነው። እግዚአብሔር ኢትዮጵያን እና ህዝቧን ይጠብቅ! ይባርክ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule