• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሕዝብ ከስሜትና ከተራ ብሽሽቅ በመራቅ በያለበት የአገሩ ዘበኛ ይሁን!

June 28, 2018 11:30 pm by Editor 2 Comments

ቀደም ሲል በሃዋሳ፣ ባለፈው ቅዳሜ በመስቀል አደባባይ በተቀነባበረ ሁኔታ የደረሰውን የቦንብ ፍንዳታ፣ በቤኒሻንጉል በተለያዩ ቦታዎችና በተለይም በአሶሳ የደረሰንና እየደረሰ ያለውን የዘር ማጥራት ጭፍጨፋ፣ ሕዝብ ወደ ምሬት እንዲሄድ ሆን ተብሎ የሚደረግ የኢኮኖሚ አሻጥር፣ በጥሞና ለምትከታተሉ ሁሉ፤

በባህር ዳር ለጠቅከላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ ቀና ተግባርና የለውጥ ሩጫ እውቅና ለመስጠት የተጠራውን ሰልፍ ለማወክ ከወዲሁ ቦንብ ሲያዘዋውሩ መያዛቸውን ለሰማችሁ፣ የደኅንነት ኃይሉን ትብትብ በወጉ ለምትረዱና ለምትገነዘቡ፤ በተለያዩ የአገሪቱ የልማት ተቋማት ላይ የሚፈጸመውን የኢኮኖሚ አሻጥር በውል ለምትከታተሉ፤ ህዝብን ከህዝብ ጋር ለማጋጨት የሚሸረቡ ተንኮሎችን ለምታጤኑ፤ ለውጡ እንዲኮላሽና አገሪቱ ወደ ትርምስ ውስጥ እንድትገባ በተሸናፊነት ውስጥ ሆነው ለጥፋት የሚመደበውን በጀት ለምትሰሙ …. በጥቅሉ አሁን እየሆነ ያለውን ለምታስተውሉ አገር ወዳድ ዜጎች የጎልጉል ዝግጅት ክፍል አጭር መልዕክት አለው።

እየሆነ ባለው የለውጥ ሂደት ቀልብን ሰብስቦ በማሰብ፣ ልብን በመጠበቅ፣ በየመኖሪያና በየሥራው ቦታ፣ በአለፍንበትና ባገደምነበት ሁሉ የአገራችን ዘበኛ ልንሆን ይገባል። በተራ ብሽⶥቅና እንካ ሰላንቲያ የሚገኝ ትርፍ የለምና እንዲህ ያለውን የሰንፎች መንገድ ካልተውን ተሸናፊዎች አጀንዳና እጅ ተመልሰን እንወድቃለን።

አሁን ጊዜው ዋጋ የሚከፈልበት ነው። አሁን ጊዜው ከቀድሞው መስዋዕትነት በላይ ዋጋ ለመክፈል የምንምልበት ነው። ፍቅር ያሸንፋል ሲባል፣ ከክፉ መንገዳቸው የተመለሱትን ከነጸጸታቸው መቀብል እንጂ መግፋት አይደለምና በአገር ደረጃ ለታወጀው የሰላም መንገድ፣ የድል መንገድ፣ የዕርቅ መንገድ ክፉዎች የሚወድቁበት ወጥመድ ይህ የፍቅር መንገድ ብቻ በመሆኑ በማስተዋል እንራመድ።

በየድረገጹና በየማኅበራዊ ሚዲያ የሚታየው፣ የሚነበበው ተራ የብሽሽቅ ፖለቲካ ብስጭት ውስጥ ያሉትን የበለጠ እንዲያመርሩ፤ ያልገቡትን ደግሞ ወደዚያው እንዲገቡ የሚገፋፋ ነው ሰከን እንበል። ያለንበት ሁኔታ “ተራው የኔ ነው” የሚያስብል ሳይሆን አገር ለማዳን የምንጨነቅበት፤ የምንችለውን ሁሉ ቀንና ሌሊት የምሠራበት ነው። በርግጥ ላለፉት በርካታ ዓመታት ለአገራችን ስንለፋ ከነበርን ይህ የታየው ለውጥ ፍሬ እንዲያፈራ ይበልጡኑ የምንተጋበት ጊዜ አሁን ነው።

በስሜት እየተንቦጫረቅን ከተቀመጠው ዋንኛ የድል መንገድ የምንወጣ ከሆነ መፈረካከስ ይሆናልና በጥሞና ወደ ድልና መደመር የሚወስደንን ጎዳና አንልቀቅ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት ለለውጡ መቀጠል ሁላችንም በተግባር የሚጠበቅብንን እንወጣ። አሁን የጥፋት ኃይሎች ሆነው ብቅ ያሉት ያለ ከልካይ እንደመዥገር ተጣበቀው ሲጠቧት የነበረችውን አገር እንዲለቅቁ እየተደረጉ ነውና በቀላሉ ለመልቀቅ ፈቃደኞች ይሆናሉ ብሎ መገመት የዋህነት ነው። ይህ ለውጥ ለአብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ የመኖርን ትርጉም ፍንትው አድርጎ ያሳየ የመሆኑን ያህል ለነዚህ ኃይሎች ደግሞ የዚህ ተቃራኒ ነው የሆነባቸው። ስለዚህ በለውጡ ሒደት በፍጥነት ወደፊት ከምንገሰግስ ይልቅ እሣት ወደ ማጥፋት እንድንሄድና በሒደትም መንገዳችንን እንድንስት እንደሚያደርጉን ጠንቅን ልንገነዘብ ያስፈልጋል።

እነዚህ የተቀናጁ፣ የተደራጁ፣ ለዘመናት ሲዘርፉት በነበረው በርካታ የገንዘብ ኃይል የሚደገፉ፣ ለአገር ደኅንነት ቅንጣት ያህል የማይጨንቃቸው ኃይሎችን በስሜት፣ በግብታዊነት፣ በበቀል፣ በእልህና በንዴት ሳይሆን አካሄዳቸውን በማጥናት፣ በብልሃትና በትጋት ነቅተን የምንታገልበት ወሳኝ ሰዓት ላይ ነን። የተጀመረው የለውጥና የተሃድሶ ጉዞ መስቀለኛ መንገድ ላይ መሆኑን በመገንዘብ ለድል እናምርር።

ስለዚህ ባለሙያዎችም አገራችሁን የምትረዱበት ወቅት አሁን ነውና ኢትዮጵያን በማዳኑ የቀና መንገድ ያለ አንዳች ይጥቅም የበኩላችሁን ተወጡ። አገራችሁ ትፈልጋችኋለች፤ የትኛውም ዓይነት የሙያ ልምድ ይሆን ትምህርት በአሁኔ ጊዜ ያስፈልጋልና በሁሉም መስክ ተደመሩ። በሚዲያ ላይ ያላችሁ በማኅበራዊ ድረገጾችም ይሁን በድረገጾችና በመካነ ጦማሮች ላይ የምትሳተፉ፣ አስተያየት የምትሰጡ የብሽሽቅ ፖለቲካውን ባካችሁን አርግቡት፤ ከጥቅሙ ጉዳቱ ነው የሚበልጠውና ይቅርባችሁ። የዓመታት ግፍ በርግጥ ብዙ እንዲባል ያስገድዳል ግን ደግሞ ውጤቱ መልሶ እኛኑ የሚጎዳ ከሆነ መተዉ የተሻለ ይሆናል። አሁን እየጎላ የመጣውን የለውጥና የመኖር ተስፋ፣ ተመልሶ ኢትዮጵያዊ የመሆን ታላቅ ዕድል ለማፈራረስ የማይማስ ጉድጓድ የለምና ሁሉም ዘብ ይቁም!!


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ™” አቋም ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: abiy ahmed, eprdf, Left Column, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Lemma says

    July 1, 2018 10:26 pm at 10:26 pm

    Yibarkachihu. BeTam Teqami melikt new. TPLF is now like a grotesque rabid dog. It barks and bites at any thing, including, at last, its own tail to finish itsel off.
    Degagmachehu hizbun mikeru. Bertu Golguloch.

    Reply
  2. Ezira says

    July 2, 2018 07:27 pm at 7:27 pm

    ትክክል ነው። አንዲት የተቆጣች ድመት የመዉጫውን በር ከዘጋህባት ያላት አማራጭ ከአንት ላይ መጎመር ነው። ስለዚህ ከምንም በላይ አገራችን ኢትዮጵያን መጠበቅና ለ27 ዓመት ከተቀበረችበት መቃብር ፈንቅላ እየወጣች ነችና …ይሄንን የመቃበሯን ድንጋይ ላይዋ ላይ ልናነሳላት የምንችለው በጋራ ሆነን ጠ/ር ዶ/ር አብይ እንዳሉት በመደመርና በመደመር ብቻ ነው። እግዚአብሔር ኢትዮጵያን እና ህዝቧን ይጠብቅ! ይባርክ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule