• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኔታ መስፍን ወልደ ማርያም የዘመን ዕንቁ! የትውልድ ዋርካ!

September 30, 2020 02:13 am by Editor Leave a Comment

መስከረም 20፤ 2013 ዓም የትውልድ ዋርካ፤ የዘመናት ዕንቁ የሆኑትን የኔታ መስፍን ወልደ ማርያም ማረፋቸው ተሰምቷል። ስለ እርሳቸው ብዙ ማለት ይቻላል። ሞት ለማንም የማይቀር ቢሆንም ስለ እርሳቸው ዕረፍት እኛ ከምንናገረው በላይ ራሳቸው ስለ ሞት የተናገሩትን አትመነዋል። ከሁሉ በላይ “ዛሬም እንደ ትናንት” የተሰኘውን የመጨረሻ መጽሐፋቸውን ከሁለት ሳምንታት በፊት አሳትመው ማረፋቸው ለአገራቸው እስከመጨረሻው የተጉ የዘመናችን ዕንቁ! የኔታ መስፍን! የቅኔ ጌታ! የዕውቀት ገበታ! ቢባልላቸው በፍጹም የሚያንስባቸው አይደለም።  

የዛሬ ሦስት ዓመት ተኩል አካባቢ ጥር/2009 ስለራሳቸው ህይወትና ጻዕረሞት የጻፉትን በድጋሚ በማተም የስንብት ሐዘናችንን እንገልጻለን።

ለቤተሰብ፣ ለዘመድ፣ ለወዳጅ፣ ለመላው የአገራችን ሕዝብ መጽናናትን እንመኛለን።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

ጻዕረ ሞትና መስፍን ወልደ ማርያም

አንደኛ፣ ገና በልጅነቴ አሥር ዓመት ግድም ሲሆነኝ አንድ በድቀድቂት ከእንጦጦ ወደታች የሚወርድ ኢጣልያዊና እኔ ተጋጠምን፤ እሱ በዚያ በጥቁር ድንጋይ ኮረት በረበረበበት መንገድ ላይ ሲጓዝ ወደ እንጦጦ የሚወጣ ወታደሮችን የጫነ ከባድ መኪና ቆሞ ነበር፤ በዚያ መኪና ላይ አንድ ዝንጀሮ ነበር፤ የኔ አትኩሮት በዚህ ዝንጀሮ ላይ ነበር! እንደሚመስለኝ ዝንጀሮውን እያየሁ ስሮጥ ከድቅድቂቱ ጋር ተገናኘን፤ እኔ ከስር በተረበረበው የጥቁር ድንጋይ ኮረት ላይ፣ ድቅድቂቱ ደግሞ የእኔን ራስ ጨፍልቆ! ምኒልክ ሀኪም ቤት ከስንት ቀኖች በኋላ የካቶሊክ መነኮሳት አስታማሚዎች ከነመለዮአቸው አልጋዬ አጠገብ ቆመው በትልቅ የበሽተኞች ድንኳን ውስጥ በአንዱ መደዳ ውስጥ ተኝቼ ነቃሁ፤ መድኃኔ ዓለም ማንን ልኮ የእኔን ጭንቅላት ከድንጋዩና ከድቅድቂቱ መክቶ እንዳዳነኝ አላውቅም።

ሁለተኛ፣ ከሶደሬ መውጫ ላይ በመቶ ሰባ ኪሜ የሚሽከረከር መኪና ተገልብጦ ከመኪናው በጣራው በርሬ ወጥቼ የጥቁር ድንጋይ ሰፈር በሆነበት አሸዋ ተነጥፎልኝ ሳልፈነከት በጭንቅላቴ አረፍሁና በጸጉሬ አሸዋ አፍሼ ተነሣሁ።

ሦስተኛ፣ በፓሪስ በአንድ ዓለም-አቀፍ ስብስባ ላይ የተጠናወተኝ ሕመም እስከሎንዶን ተከትሎኝ፣ ወደ አዲስ አበባ ለመመለስ አንድ ወዳጄ አውሮጵላን ጣቢያ ወሰደኝ፤ እኔ ከሆቴል ከወጣሁ በኋላ ምንም የማስታውሰው ነገር የለኝም፤ ጻዕረ ሞት እያለሳለሰ ይዞኝ በመሄድ ላይ ነበረ፤ በሦሰተኛው ቀን በሆስፒታል ውስጥ ነቃሁ፤ አሥራ ሦስት ቀን በሀኪም ቤት ስታከም ቀይቼ ወጣሁ።

አራተኛ፣ በቃሊቲ የወያኔ እስረኛ ሆኜ ጻዕረ ሞት ጎበኘኝ፤ ደበበ እሸቱ ደረሰበትና በወያኔ መልካም ፈቃድ በላንድሮቨር ወደ ፖሊስ ሆስፒታል ዶ/ር ሰይፉ ተረከበኝ፤ ለሦስት ቀናት ያህል ራሴን አላውቅም ነበር።

አምስተኛ፣ ተወልጄ ያደግሁበት አዲስ አበባ በድንገት ላንተ አይሆንም የተባለ ይመስል ኦክሲጄን እያነሰብኝ ትንፋሽ ያጥረኝ ጀመረ፤ አዋሳ ሄጄ አንድ ወር ያህል በሰላም ቆየሁ፤ ከዚያ በኋላ አገሩ ሁሉ በፉከራ፣ በጭስና በእሳት ታፈነና በአገሬ መሄጃ አጣሁና ወደህንድ መጣሁ፤ ለአሥር ቀናት ያህል ሰላም አገኘሁ፤ ከዚያ ጻዕረ ሞት ተቆጥቶ መጣ! እጄንና እግሬን ይዞኝ ታገልን! የእውነት ትግል ነበር፤ የሆቴሉን ስልክ አንሥቼ እያቃሳትሁ ወደ ሀኪም ቤት የሚወስደኝን መኪና (አምቡላንስ) እንዲያስመጡልኝ ጮህኩኝ! ኦክሲጅንና ሌላም ነገር እያማጉኝ በዚያ ሰውና መኪና፣ ድቅድቂት እየተጋፋ እየተዳፋ በሚሄድበት መንገድ ለረጅም ጊዜ እየተንገጫገጭሁ ተጓዝሁ፤ ነፍስ ውጪ-ነፍስ-ግቢ ክፍል አስገቡኝ፤ ጻዕረ-ሞት ተናድዶ እየዛተ ጥሎኝ ሄደ።

እሱም አይቀር! እኔም ማምለጫ የለኝ!

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
ጥር/ 2009

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial, Right Column Tagged With: mesfin, prof mesfin

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule