• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለተከሳሽ ጃዋርና ግብረአበሮቹ “ማንኛውም ሰው በሕግ ፊት እኩል ነው” የሚል ምላሽ ተሰጠ

September 29, 2020 01:57 am by Editor Leave a Comment

ባለፈው ሳምንት ሰኞ መስከረም 11 ቀን 2013 ዓ.ም. አሥር የተለያዩ ክሶች የተመሠረተባቸው አቶ ጃዋር መሐመድን ጨምሮ 24 ተከሳሾች ክሱ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 20 ድንጋጌ መሠረት የተሰጣቸው ቢሆንም፣ በሥነ ሥርዓት ሕጉ አንቀጽ 129 ድንጋጌ መሠረት ክሱ ለተከሳሾቹ በችሎት መነበብ ስላለበት፣ በችሎት ለማንበብ ለመስከረም 20 ቀን 2013 ዓ.ም. ቀጠሮ ተሰጣቸው።

ፍርድ ቤቱ ተከሳሾን ለመስከረም 14 ቀን 2013 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው፣ መስከረም 11 ቀን 2013 ዓ.ም. ያልቀረቡ ተከሳሾችን የፌዴራል ፖሊስ እንዲያቀርብና ክስ እንዲነበብላቸው የነበረ ቢሆንም ሳያቀርብ ቀርቷል።

በእነ አቶ ጃዋር የክስ መዝገብ አምስተኛ ተከሳሽ የሆኑት አቶ ደጀኔ ጣፋ፣ 14ኛ ተከሳሽና በአሜሪካ አገር ነዋሪ የሆኑት አቶ ብርሃነ መስቀል አበበና አውስትራሊያ እንደሚኖሩ የሚነገረው አቶ ፀጋዬ ረጋሳ አራርሳን ጨምሮ ስድስት ተከሳሾች በድጋሚ ሳይቀርቡ በመቀረታቸው፣ ፍርድ ቤቱ ለሁለተኛ ጊዜ ክስ ለማንበብ ቀጠሮ ሰጥቷል።

በችሎት የተገኙትንና ሳይቀርቡ የቀሩትን ተከሳሾች አቶ ደጀኔንና ሌላ ተከሳሽን የሚወክሉ 12 ጠበቆች በችሎት ተሰይመዋል።

የፌዴራል ፖሊስ ተከሳሾቹን ለምን እንዳላቀረበ ተጠይቆ በሰጠው ምላሽ፣ እንዲያቀርብ ትዕዛዝ የተሰጠበት ቀን አጭር በመሆኑ ጊዜ እንዳነሰው ተናግሮ፣ የኦኤምኤን ተወካይ የተባለው ተከሳሽ ግን 16ኛ ተከሳሽ አቶ ቦና ቲቢሌ በእስር ላይ የሚገኝና እየቀረበ መሆኑን አስረድቷል። አጭር ቀን ቢሰጠውም እንደሚያቀርብ ገልጾ፣ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል።

አቶ ደጀኔ ጣፋን በሚመለከት ጠበቃቸው ለፍርድ ቤቱ እንዳስረዱት፣ ደንበኛቸው አቶ ደጀኔ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ብለው በማሰብ መገኘታቸውን ተናግረው፣ ታስረው ስለሚገኙበት ሁኔታ አስረድተዋል። አቶ ደጀኔ ከታሰሩበት ጊዜ አንስተው ቤተሰቦቻቸው እየጎበኟቸው ባለመሆኑ ጥብቅ ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው ጠይቀዋል።

ፌዴራል ፖሊስ አጭር ቀን ቢሰጠው እንደሚያቀርብ ለፍርድ ቤቱ ያስረዳውን በሚመለከት ጠበቆች በመቃወም፣ የተወሰኑት ተከሳሾች በአገር ውስጥ ስለሌሉ ፕሮሲጀሩ ታልፎ በችሎት ለተገኙት ተከሳሾች ክሱ ተነቦላቸው ወደ ዋናው ክርከር እንዲገቡ ጠይቀዋል።

በተከሳሾቹ ላይ በሥር ፍርድ ቤት የተሰማው የቀዳሚ ምርመራ ቃል ግልባጭና ኦዲዮ ግልባጭ ስላልደረሳቸው፣ እንዲደርሳቸው ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸውም ጠይቀዋል።

አቶ ሻምሰዲን ጠሃ የተባሉት ተከሳሽ ደግሞ ለፍርድ ቤቱ ባቀረቡት አቤቱታ እንዳስረዱት፣ በተፈጸመባቸው ድብደባ ጆሯቸው ተጎድቶ ሲታከሙ ቢቆዩም አልዳኑም። ጆሯቸው እየመገለ በመሆኑ ስፔሻሊስት ዘንድ እንዲታከሙ በሥር ፍርድ ቤት ስለተፈቀደላቸው፣ ሳይከለከሉ እንዲታከሙ እንዲፈቀድላቸውና ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው ጠይቀዋል።

ተከሳሹ ፍርድ ቤቱን ሌላው የጠየቁት ከኢሬቻ በዓል አከባበር ጋር የተገናኘ ሲሆን፣ ‹‹እስካሁን በኢሬቻ በዓል አከባበር ላይ ቀርቼ ስለማላውቅ ይፈቀድልኝ ወይም በአጃቢ እንዳከብር ይደረግልኝ›› ሲሉ አመልክተዋል።

ፍርድ ቤቱ ክሱን በሚመለከት ያልቀረቡት ተከሳሾች ሲቀርቡ እንደሚነበብ ገልጾ፣ አቆያያቸውን በሚመለከት የሚሉት ካላቸው ተከሳሾቹን ጠይቋል።

የተከሳሾቹ ጠበቆች በሰጡት ምላሽ አቶ በቀለ፣ አቶ ጃዋርና አቶ ሀምዛ አዳነ ከፍተኛ የፖለቲካ አመራሮች በመሆናቸውና ከፍተኛ የሆነ ጥበቃም ስለሚያስፈልጋቸው፣ ከታሰሩበት ጊዜ እንስቶ ባሉበት እስር ቤት ሆነው ክሳቸውን እንዲከታተሉ ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው ጠይቀዋል። ሌሎቹም ተከሳሾች ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እየቀረቡ ክሳቸውን እንዲከታተሉ ጠይቀዋል።

በዕለቱ ሦስት ዓቃቤያነ ሕግ የተሰየሙ ሲሆን፣ ባቀረቡት ተቃውሞ ጥበቃንም ሆነ አያያዝን በሚመለከት ኃላፊነቱ የመንግሥት መሆኑን ጠቁመው ከሕክምና፣ ከቀለብና ከአያያዝ ጋር በተገናኘ ተከሳሾቹ መቆየት ያለባቸው በማረሚያ ቤት መሆኑን፣ ከሕግ አንፃርም ቢሆን ማንኛውም ሰው በሕግ ፊት እኩል ነው በሚለው መርህ መሠረት እንደ ማንኛውም ተከሳሽ መቆየት ያለባቸው ማረሚያ ቤት ስለሆነ፣ ወደዚያው እንዲላኩ እንዲታዘዝለት ጠይቋል።

አቶ ጃዋር በመሀል ተነስቶ ለፍርድ ቤቱ የሚያመለክተው እንዳለው ጠይቆ ሲከለከል፣ “የትም ብንታሰር ግድ የለንም” በማለት ተቀምጧል።

ፍርድ ቤቱ በሰጠው ትዕዛዝ፣ ሁሉም ተከሳሾች በማረሚያ ቤት ይቆዩ ብሏል። የሕክምናና ሌሎች ከመብት ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን በሚመለከት የፌዴራል ማረሚያ ቤት አስተዳደር ፈጽሞ እንዲያቀርብ፣ ፖሊስ በውጭ አገርም ሆነ በአገር ውስጥ ያሉ ተከሳሾችን ይዞ እንዲያቀርብ ወይም ያልቻለበትን ምክንያት እንዲያስረዳ ትዕዛዝ በመስጠት ክስ ለማንበብ ለመስከረም 20 ቀን 2013 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል።    

(ታምሩ ጽጌ፤ ሪፖርተር)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Law, Left Column Tagged With: bekele gerba, birhanemeskel, chilot, eskinder, hamza, jawar massacre, omn, tsgaye ararssa, ችሎት

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule