• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለተከሳሽ ጃዋርና ግብረአበሮቹ “ማንኛውም ሰው በሕግ ፊት እኩል ነው” የሚል ምላሽ ተሰጠ

September 29, 2020 01:57 am by Editor Leave a Comment

ባለፈው ሳምንት ሰኞ መስከረም 11 ቀን 2013 ዓ.ም. አሥር የተለያዩ ክሶች የተመሠረተባቸው አቶ ጃዋር መሐመድን ጨምሮ 24 ተከሳሾች ክሱ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 20 ድንጋጌ መሠረት የተሰጣቸው ቢሆንም፣ በሥነ ሥርዓት ሕጉ አንቀጽ 129 ድንጋጌ መሠረት ክሱ ለተከሳሾቹ በችሎት መነበብ ስላለበት፣ በችሎት ለማንበብ ለመስከረም 20 ቀን 2013 ዓ.ም. ቀጠሮ ተሰጣቸው።

ፍርድ ቤቱ ተከሳሾን ለመስከረም 14 ቀን 2013 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው፣ መስከረም 11 ቀን 2013 ዓ.ም. ያልቀረቡ ተከሳሾችን የፌዴራል ፖሊስ እንዲያቀርብና ክስ እንዲነበብላቸው የነበረ ቢሆንም ሳያቀርብ ቀርቷል።

በእነ አቶ ጃዋር የክስ መዝገብ አምስተኛ ተከሳሽ የሆኑት አቶ ደጀኔ ጣፋ፣ 14ኛ ተከሳሽና በአሜሪካ አገር ነዋሪ የሆኑት አቶ ብርሃነ መስቀል አበበና አውስትራሊያ እንደሚኖሩ የሚነገረው አቶ ፀጋዬ ረጋሳ አራርሳን ጨምሮ ስድስት ተከሳሾች በድጋሚ ሳይቀርቡ በመቀረታቸው፣ ፍርድ ቤቱ ለሁለተኛ ጊዜ ክስ ለማንበብ ቀጠሮ ሰጥቷል።

በችሎት የተገኙትንና ሳይቀርቡ የቀሩትን ተከሳሾች አቶ ደጀኔንና ሌላ ተከሳሽን የሚወክሉ 12 ጠበቆች በችሎት ተሰይመዋል።

የፌዴራል ፖሊስ ተከሳሾቹን ለምን እንዳላቀረበ ተጠይቆ በሰጠው ምላሽ፣ እንዲያቀርብ ትዕዛዝ የተሰጠበት ቀን አጭር በመሆኑ ጊዜ እንዳነሰው ተናግሮ፣ የኦኤምኤን ተወካይ የተባለው ተከሳሽ ግን 16ኛ ተከሳሽ አቶ ቦና ቲቢሌ በእስር ላይ የሚገኝና እየቀረበ መሆኑን አስረድቷል። አጭር ቀን ቢሰጠውም እንደሚያቀርብ ገልጾ፣ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል።

አቶ ደጀኔ ጣፋን በሚመለከት ጠበቃቸው ለፍርድ ቤቱ እንዳስረዱት፣ ደንበኛቸው አቶ ደጀኔ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ብለው በማሰብ መገኘታቸውን ተናግረው፣ ታስረው ስለሚገኙበት ሁኔታ አስረድተዋል። አቶ ደጀኔ ከታሰሩበት ጊዜ አንስተው ቤተሰቦቻቸው እየጎበኟቸው ባለመሆኑ ጥብቅ ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው ጠይቀዋል።

ፌዴራል ፖሊስ አጭር ቀን ቢሰጠው እንደሚያቀርብ ለፍርድ ቤቱ ያስረዳውን በሚመለከት ጠበቆች በመቃወም፣ የተወሰኑት ተከሳሾች በአገር ውስጥ ስለሌሉ ፕሮሲጀሩ ታልፎ በችሎት ለተገኙት ተከሳሾች ክሱ ተነቦላቸው ወደ ዋናው ክርከር እንዲገቡ ጠይቀዋል።

በተከሳሾቹ ላይ በሥር ፍርድ ቤት የተሰማው የቀዳሚ ምርመራ ቃል ግልባጭና ኦዲዮ ግልባጭ ስላልደረሳቸው፣ እንዲደርሳቸው ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸውም ጠይቀዋል።

አቶ ሻምሰዲን ጠሃ የተባሉት ተከሳሽ ደግሞ ለፍርድ ቤቱ ባቀረቡት አቤቱታ እንዳስረዱት፣ በተፈጸመባቸው ድብደባ ጆሯቸው ተጎድቶ ሲታከሙ ቢቆዩም አልዳኑም። ጆሯቸው እየመገለ በመሆኑ ስፔሻሊስት ዘንድ እንዲታከሙ በሥር ፍርድ ቤት ስለተፈቀደላቸው፣ ሳይከለከሉ እንዲታከሙ እንዲፈቀድላቸውና ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው ጠይቀዋል።

ተከሳሹ ፍርድ ቤቱን ሌላው የጠየቁት ከኢሬቻ በዓል አከባበር ጋር የተገናኘ ሲሆን፣ ‹‹እስካሁን በኢሬቻ በዓል አከባበር ላይ ቀርቼ ስለማላውቅ ይፈቀድልኝ ወይም በአጃቢ እንዳከብር ይደረግልኝ›› ሲሉ አመልክተዋል።

ፍርድ ቤቱ ክሱን በሚመለከት ያልቀረቡት ተከሳሾች ሲቀርቡ እንደሚነበብ ገልጾ፣ አቆያያቸውን በሚመለከት የሚሉት ካላቸው ተከሳሾቹን ጠይቋል።

የተከሳሾቹ ጠበቆች በሰጡት ምላሽ አቶ በቀለ፣ አቶ ጃዋርና አቶ ሀምዛ አዳነ ከፍተኛ የፖለቲካ አመራሮች በመሆናቸውና ከፍተኛ የሆነ ጥበቃም ስለሚያስፈልጋቸው፣ ከታሰሩበት ጊዜ እንስቶ ባሉበት እስር ቤት ሆነው ክሳቸውን እንዲከታተሉ ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው ጠይቀዋል። ሌሎቹም ተከሳሾች ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እየቀረቡ ክሳቸውን እንዲከታተሉ ጠይቀዋል።

በዕለቱ ሦስት ዓቃቤያነ ሕግ የተሰየሙ ሲሆን፣ ባቀረቡት ተቃውሞ ጥበቃንም ሆነ አያያዝን በሚመለከት ኃላፊነቱ የመንግሥት መሆኑን ጠቁመው ከሕክምና፣ ከቀለብና ከአያያዝ ጋር በተገናኘ ተከሳሾቹ መቆየት ያለባቸው በማረሚያ ቤት መሆኑን፣ ከሕግ አንፃርም ቢሆን ማንኛውም ሰው በሕግ ፊት እኩል ነው በሚለው መርህ መሠረት እንደ ማንኛውም ተከሳሽ መቆየት ያለባቸው ማረሚያ ቤት ስለሆነ፣ ወደዚያው እንዲላኩ እንዲታዘዝለት ጠይቋል።

አቶ ጃዋር በመሀል ተነስቶ ለፍርድ ቤቱ የሚያመለክተው እንዳለው ጠይቆ ሲከለከል፣ “የትም ብንታሰር ግድ የለንም” በማለት ተቀምጧል።

ፍርድ ቤቱ በሰጠው ትዕዛዝ፣ ሁሉም ተከሳሾች በማረሚያ ቤት ይቆዩ ብሏል። የሕክምናና ሌሎች ከመብት ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን በሚመለከት የፌዴራል ማረሚያ ቤት አስተዳደር ፈጽሞ እንዲያቀርብ፣ ፖሊስ በውጭ አገርም ሆነ በአገር ውስጥ ያሉ ተከሳሾችን ይዞ እንዲያቀርብ ወይም ያልቻለበትን ምክንያት እንዲያስረዳ ትዕዛዝ በመስጠት ክስ ለማንበብ ለመስከረም 20 ቀን 2013 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል።    

(ታምሩ ጽጌ፤ ሪፖርተር)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Law, Left Column Tagged With: bekele gerba, birhanemeskel, chilot, eskinder, hamza, jawar massacre, omn, tsgaye ararssa, ችሎት

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule