• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለተከሳሽ ጃዋርና ግብረአበሮቹ “ማንኛውም ሰው በሕግ ፊት እኩል ነው” የሚል ምላሽ ተሰጠ

September 29, 2020 01:57 am by Editor Leave a Comment

ባለፈው ሳምንት ሰኞ መስከረም 11 ቀን 2013 ዓ.ም. አሥር የተለያዩ ክሶች የተመሠረተባቸው አቶ ጃዋር መሐመድን ጨምሮ 24 ተከሳሾች ክሱ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 20 ድንጋጌ መሠረት የተሰጣቸው ቢሆንም፣ በሥነ ሥርዓት ሕጉ አንቀጽ 129 ድንጋጌ መሠረት ክሱ ለተከሳሾቹ በችሎት መነበብ ስላለበት፣ በችሎት ለማንበብ ለመስከረም 20 ቀን 2013 ዓ.ም. ቀጠሮ ተሰጣቸው።

ፍርድ ቤቱ ተከሳሾን ለመስከረም 14 ቀን 2013 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረው፣ መስከረም 11 ቀን 2013 ዓ.ም. ያልቀረቡ ተከሳሾችን የፌዴራል ፖሊስ እንዲያቀርብና ክስ እንዲነበብላቸው የነበረ ቢሆንም ሳያቀርብ ቀርቷል።

በእነ አቶ ጃዋር የክስ መዝገብ አምስተኛ ተከሳሽ የሆኑት አቶ ደጀኔ ጣፋ፣ 14ኛ ተከሳሽና በአሜሪካ አገር ነዋሪ የሆኑት አቶ ብርሃነ መስቀል አበበና አውስትራሊያ እንደሚኖሩ የሚነገረው አቶ ፀጋዬ ረጋሳ አራርሳን ጨምሮ ስድስት ተከሳሾች በድጋሚ ሳይቀርቡ በመቀረታቸው፣ ፍርድ ቤቱ ለሁለተኛ ጊዜ ክስ ለማንበብ ቀጠሮ ሰጥቷል።

በችሎት የተገኙትንና ሳይቀርቡ የቀሩትን ተከሳሾች አቶ ደጀኔንና ሌላ ተከሳሽን የሚወክሉ 12 ጠበቆች በችሎት ተሰይመዋል።

የፌዴራል ፖሊስ ተከሳሾቹን ለምን እንዳላቀረበ ተጠይቆ በሰጠው ምላሽ፣ እንዲያቀርብ ትዕዛዝ የተሰጠበት ቀን አጭር በመሆኑ ጊዜ እንዳነሰው ተናግሮ፣ የኦኤምኤን ተወካይ የተባለው ተከሳሽ ግን 16ኛ ተከሳሽ አቶ ቦና ቲቢሌ በእስር ላይ የሚገኝና እየቀረበ መሆኑን አስረድቷል። አጭር ቀን ቢሰጠውም እንደሚያቀርብ ገልጾ፣ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል።

አቶ ደጀኔ ጣፋን በሚመለከት ጠበቃቸው ለፍርድ ቤቱ እንዳስረዱት፣ ደንበኛቸው አቶ ደጀኔ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ብለው በማሰብ መገኘታቸውን ተናግረው፣ ታስረው ስለሚገኙበት ሁኔታ አስረድተዋል። አቶ ደጀኔ ከታሰሩበት ጊዜ አንስተው ቤተሰቦቻቸው እየጎበኟቸው ባለመሆኑ ጥብቅ ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው ጠይቀዋል።

ፌዴራል ፖሊስ አጭር ቀን ቢሰጠው እንደሚያቀርብ ለፍርድ ቤቱ ያስረዳውን በሚመለከት ጠበቆች በመቃወም፣ የተወሰኑት ተከሳሾች በአገር ውስጥ ስለሌሉ ፕሮሲጀሩ ታልፎ በችሎት ለተገኙት ተከሳሾች ክሱ ተነቦላቸው ወደ ዋናው ክርከር እንዲገቡ ጠይቀዋል።

በተከሳሾቹ ላይ በሥር ፍርድ ቤት የተሰማው የቀዳሚ ምርመራ ቃል ግልባጭና ኦዲዮ ግልባጭ ስላልደረሳቸው፣ እንዲደርሳቸው ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸውም ጠይቀዋል።

አቶ ሻምሰዲን ጠሃ የተባሉት ተከሳሽ ደግሞ ለፍርድ ቤቱ ባቀረቡት አቤቱታ እንዳስረዱት፣ በተፈጸመባቸው ድብደባ ጆሯቸው ተጎድቶ ሲታከሙ ቢቆዩም አልዳኑም። ጆሯቸው እየመገለ በመሆኑ ስፔሻሊስት ዘንድ እንዲታከሙ በሥር ፍርድ ቤት ስለተፈቀደላቸው፣ ሳይከለከሉ እንዲታከሙ እንዲፈቀድላቸውና ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው ጠይቀዋል።

ተከሳሹ ፍርድ ቤቱን ሌላው የጠየቁት ከኢሬቻ በዓል አከባበር ጋር የተገናኘ ሲሆን፣ ‹‹እስካሁን በኢሬቻ በዓል አከባበር ላይ ቀርቼ ስለማላውቅ ይፈቀድልኝ ወይም በአጃቢ እንዳከብር ይደረግልኝ›› ሲሉ አመልክተዋል።

ፍርድ ቤቱ ክሱን በሚመለከት ያልቀረቡት ተከሳሾች ሲቀርቡ እንደሚነበብ ገልጾ፣ አቆያያቸውን በሚመለከት የሚሉት ካላቸው ተከሳሾቹን ጠይቋል።

የተከሳሾቹ ጠበቆች በሰጡት ምላሽ አቶ በቀለ፣ አቶ ጃዋርና አቶ ሀምዛ አዳነ ከፍተኛ የፖለቲካ አመራሮች በመሆናቸውና ከፍተኛ የሆነ ጥበቃም ስለሚያስፈልጋቸው፣ ከታሰሩበት ጊዜ እንስቶ ባሉበት እስር ቤት ሆነው ክሳቸውን እንዲከታተሉ ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው ጠይቀዋል። ሌሎቹም ተከሳሾች ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እየቀረቡ ክሳቸውን እንዲከታተሉ ጠይቀዋል።

በዕለቱ ሦስት ዓቃቤያነ ሕግ የተሰየሙ ሲሆን፣ ባቀረቡት ተቃውሞ ጥበቃንም ሆነ አያያዝን በሚመለከት ኃላፊነቱ የመንግሥት መሆኑን ጠቁመው ከሕክምና፣ ከቀለብና ከአያያዝ ጋር በተገናኘ ተከሳሾቹ መቆየት ያለባቸው በማረሚያ ቤት መሆኑን፣ ከሕግ አንፃርም ቢሆን ማንኛውም ሰው በሕግ ፊት እኩል ነው በሚለው መርህ መሠረት እንደ ማንኛውም ተከሳሽ መቆየት ያለባቸው ማረሚያ ቤት ስለሆነ፣ ወደዚያው እንዲላኩ እንዲታዘዝለት ጠይቋል።

አቶ ጃዋር በመሀል ተነስቶ ለፍርድ ቤቱ የሚያመለክተው እንዳለው ጠይቆ ሲከለከል፣ “የትም ብንታሰር ግድ የለንም” በማለት ተቀምጧል።

ፍርድ ቤቱ በሰጠው ትዕዛዝ፣ ሁሉም ተከሳሾች በማረሚያ ቤት ይቆዩ ብሏል። የሕክምናና ሌሎች ከመብት ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን በሚመለከት የፌዴራል ማረሚያ ቤት አስተዳደር ፈጽሞ እንዲያቀርብ፣ ፖሊስ በውጭ አገርም ሆነ በአገር ውስጥ ያሉ ተከሳሾችን ይዞ እንዲያቀርብ ወይም ያልቻለበትን ምክንያት እንዲያስረዳ ትዕዛዝ በመስጠት ክስ ለማንበብ ለመስከረም 20 ቀን 2013 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል።    

(ታምሩ ጽጌ፤ ሪፖርተር)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Law, Left Column Tagged With: bekele gerba, birhanemeskel, chilot, eskinder, hamza, jawar massacre, omn, tsgaye ararssa, ችሎት

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule