• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሙስና ተመዝብሮ በአገር ውስጥና በውጭ 130 ቢሊዮን ብር ተደብቆ እንደሚገኝ ተጠቆመ

September 29, 2020 09:39 pm by Editor Leave a Comment

መንግሥት በተለያዩ ሁኔታዎች በሙስና ወንጀል የተመዘበሩ ሀብቶችን ለማስመለስ ጥረት እያደረገ ቢሆንም፣ እስካሁን በተደረገ ጥናት በአገር ውስጥና በውጭ አገሮች ተደብቆ የሚገኝ ከ130 ቢሊዮን ብር በላይ ሀብት እንዳለ ተጠቆመ።

የአመራር ለውጥ ከተደረገ ከሁለት ዓመታት ወዲህ ሙስናን ለመዋጋት መንግሥት የአገሪቱ ተቀዳሚ ተግባር አድርጎ እየተንቀሳቀሰ፣ የፖለቲካ ጣልቃ ገብነትም በተወሰነ ሁኔታ እየቀነሰና አጋር መንግሥታትና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ድጋፍና ተነሳሽነት የጨመረ ቢሆንም፣ በአገሪቱ ያለውን አለመረጋጋት እንደ ጥሩ አጋጣሚ በመውሰድ የሙስና ወንጀል በተደራጀ መልኩ እየተፈጸመ መሆኑም ተገልጿል።

ሙስና በከፍተኛ ሁኔታ በተደራጀ ሁኔታ ተጠናክሮ መቀጠሉ የተነገረው፣ የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ከባለድርሻ አካላት ጋር መስከረም 14 ቀን 2013 ዓ.ም. በኢሊሌ ሆቴል ለሁለት ቀናት ባዘጋጀው የጋራ የውይይት መክፈቻ መድረክ ላይ ነው።

በተቋሙ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ምክትል ዳይሬክተር አቶ ዘለዓለም ፈቃዱ ባቀረቡት የውይይት መነሻ ሐሳብ ላይ እንደገለጹት፣ ሙስናን ከመዋጋት አንፃር መንግሥት ተቀዳሚ ተግባር አድርጎ እየሠራበት ነው። የፖለቲካ ጣልቃ ገብነትም በተወሰነ መልኩ የመቀነስ አዝማሚያ አለው፣ አጋር መንግሥታትና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ድጋፋቸውና ተነሳሽነታቸው ጨምሯል። ምንም እንኳን እንዲህ ዓይነት ተግባራት ያሉ ቢሆንም፣ በሌላ በኩል ደግሞ ባለፉት ሁለት ዓመታት በአገሪቱ ያለውን አለመረጋጋት በመጠቀም የሙስና ሁኔታ በተደራጀ መልኩ እየተፈጸመ መሆኑን ጠቁመዋል።

ከመሬት ወረራ፣ ከባንክ ገንዘብ ማጭበርበር፣ ሐሰተኛ ሰነዶችን ከመጠቀምና ሕገወጥ ገንዘብን ሕጋዊ አስመስሎ ከማቅረብ ጋር በተያያዘ፣ የሙስና ወንጀሎች በስፋት እየጨመሩ መምጣታቸውን ምክትል ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል።

እንደ ምክትል ዳይሬክተሩ ገለጻ፣ ባለፈው ዓመት የተከሰተው ዓለም አቀፍ የኮሮና ወረርሽኝ ለሙስና ወንጀል ምቹ ሁኔታዎችን ፈጥሯል። ሙስና በግሉ ዘርፍም (Private Sector Corruption) ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱንም ተናግረዋል።

በሙስና ወንጀል የተመዘበረ ሀብትን ከማስመለስ አንፃር ጥረቶች እየተደረጉ ቢሆንም፣ በወንጀሉ የተገኘውን በአገር ውስጥና በውጭ አገሮች ተደብቆ የሚገኝን ከ130 ቢሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ማስመለስ አለመቻሉንም ጠቁመዋል።

ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ በ2012 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግሥቱን የፀረ ሙስና ሕጎችን ከማስፈጸምና መፈጸማቸውን ከመከታተል አንፃር የሠራውን እንዳብራሩት፣ የሙስና ወንጀል ምርመራን አስጀምሯል። ይመራልም። በሙስና ወንጀል የክስ መዛግብትን በሚመለከት 582 መዛግብት ለዓቃቤ ሕግ ቀርበው በ400ዎቹ ላይ ምርመራና ድጋፍ ክትትል ማድረጉንና 466 መዛግብት ውሳኔ ማግኘታቸውን አብራርተዋል።

በ2012 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ከ700 ሚሊዮን ብር በላይ የተመዘበረ ሀብት ማስመለስ መቻሉን፣ በተለያዩ ወንጀሎች የተመዘበሩ ሀብቶችን የሚያስመልስ ዳይሬክቶሬት በማቋቋም፣ በአገር ውስጥ የተደበቁና ወደ ውጭ አገሮች የሸሹ ሀብቶችን በተመለከተ የማጥናት (Tracing) እና አገሪቱን የመለየት ሥራ እየተሠራ መሆኑን አብራርተዋል።  

በበጀት ዓመቱ ከመንግሥትና ከግል ባንኮች ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ የተወሰደባቸው ከ40 በላይ የክስ መዛግብት ወደ ፍርድ ቤት ቀርበው በክርክር ላይ መሆናቸውን፣ በርካታ ሚሊዮን ብሮች እንዲታገዱና የውርስ አቤቱታ እንዲቀርብባቸው መደረጉን፣ ከሜቴክና ከሌሎች ትልልቅ የሙስና ወንጀሎች ጋር በተያያዘም ከሦስት ቢሊዮን ብር በላይ ገንዘብ የያዙ የክስ መዝገቦች ፍርድ ቤት ቀርበው ክርክር መደረጉን ምክትል ዳይሬክተሩ አብራርተዋል። በመደበኛ መዝገቦች ላይ የአፈጻጸም ክፍተት ቢኖርም፣ በትልልቅ መዝገቦች ላይ ግን የተሻለ ውሳኔና የችሎት ክርክር አፈጻጸም መመዝገቡን አክሏል።

ምክትል ዳይሬክተሩ ስለቀጣይ አሥር ዓመታት ዕቅድ አፈጻጸምና በ2013 በጀት ዓመት የሥራ ዕቅድ እንዳብራሩት፣ በማስረጃ አለመሟላት ምክንያት በርካታ የተከማቸ መዛግብት ላይ ማስረጃዎችን በማሟላት ውሳኔ እንደሚያሰጡ፣ ‹‹ለምርመራ›› በሚል ተመላሽ የተደረጉ መዛግብትን ከመከታተል ባለፈ፣ በከባድና ውስብስብ ወንጀሎች ምርመራ ላይ በቀጥታ እንደሚሳተፉ ማቀዳቸውን አስረድተዋል።

ከፍተኛ የሕዝብና የመንግሥት ጥቅም ያላቸው ትልልቅ የሙስና ወንጀል ጉዳዮችን ከምርመራ ጀምሮ ቅድሚያና ልዩ ትኩረት ሰጥተው እንደሚሠሩ፣ በዋና ኦዲተር የኦዲት ሥራ የተሠራባቸው የመንግሥት መሥሪያ ቤቶችና ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በተያያዘ ያልተወራረደ ሒሳብ እንዲወራረድና በሕግ የመጠቀም ተግባር በስፋት እንደሚከናወን መታቀዱን ምክትል ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።

ዳይሬክቶሬቱ የተለያዩ ተግዳሮቶች እንደገጠሙት የጠቆሙ ምክትል ዳይሬክተሩ፣ ማስረጃዎችን ከሚመለከታቸው አካላት በተገቢው ፍጥነት ለማግኘት አለመቻሉ፣ በማስረጃዎች ላይ ተጨማሪ ማብራሪያ ለመስጠት ፈቃደኛ አለመሆን፣ አግባብነት የሌላቸው ማስረጃዎችን መስጠት፣ ሙስና የሚፈጸምባቸው ተቋማት ቢኖሩም የሚመለከታቸው አካላት ሪፖርት አለማድረጋቸውን ጠቁመዋል።

የኦዲት ሥራ የሚሠሩ አካላት በመደበኛነት ከሚሠሩ ኦዲት ውጪ ከወንጀል ምርመራ ጋር የተያያዙ ኦዲቶችን በአፋጣኝ ሠርቶ ለመላክ ውስንነት እንዳለባቸው ጠቁመው፣ ጥፋተኛውን በግልጽ ከማሳየት አንፃር ጉድለት እንደሚታይባቸውና በሠሩት ኦዲት ላይ ምስክርነት ሲጠየቁ ፈቃደኛ ለመሆን ተግዳሮቶች እየገጠማቸው መሆኑንም አስረድተዋል።

ሚዲዎችም ሙስናን ከማጋለጥ አንፃር ያላቸው ተሳትፎ አነስተኛ መሆኑን፣ የሙስና ወንጀል ጉዳዮችን በወቅቱ ለሕዝብ ከማሳወቅ አንፃር ችግሮች መኖራቸውንም ምክትል ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። በፋይናንስ ተቋማትና ሌሎች ተቋማትም በርካታ ተግዳሮቶች መኖራቸውንና በተለይም በግሉ ዘርፍ ከሚፈጸም ሙስና ጋር በተያያዘ ምርመራ የሚያደርግ አካል አለመኖሩን አሳውቀዋል።

የአስተዳደር አካላት፣ የልማት ድርጅቶች፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ ዕንባ ጠባቂ ተቋም፣ ፀረ ሙስና ኮሚሽን፣ የፍትሕ አካላት፣ ዋና ኦዲተር፣ ሚዲያና ኅብረተሰቡ ባለድርሻ አካላት ጋር ያለው ግንኙነት ችግር እንዳለበት ጠቁመው፣ በመንግሥትም ሆነ በግሉ ዘርፍ የሚፈጸም ሙስናን በማጋለጥ ረገድ ተባብሮ መሥራት አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል።

የኦዲት ተቋማት የተረጋገጡ ጥፋቶችን ለሚመለከተው አካል ማሳወቅ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተጠያቂነትን ከማረጋገጥ አንፃር አስፈጻሚ ተቋማት ላይ ተፅዕኖ መፍጠር፣ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ደግሞ ከበደል ጋር በተያያዘ በትብብር መሥራት፣ ፀረ ሙስና ኮሚሽን የሥነ ምግባር ትምህርቶችን አጠናቅሮ በመስጠትና ሚዲዎችም የምርመራ ጋዜጠኝነት ሥራ በማናወን ሙስናን እንዲያጋልጡ ጥሪ አቅርበዋል። (ታምሩ ጽጌ፤ ሪፖርተር)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Law, News, Right Column Tagged With: corruption, new birr notes, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule