• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሙስና ተመዝብሮ በአገር ውስጥና በውጭ 130 ቢሊዮን ብር ተደብቆ እንደሚገኝ ተጠቆመ

September 29, 2020 09:39 pm by Editor Leave a Comment

መንግሥት በተለያዩ ሁኔታዎች በሙስና ወንጀል የተመዘበሩ ሀብቶችን ለማስመለስ ጥረት እያደረገ ቢሆንም፣ እስካሁን በተደረገ ጥናት በአገር ውስጥና በውጭ አገሮች ተደብቆ የሚገኝ ከ130 ቢሊዮን ብር በላይ ሀብት እንዳለ ተጠቆመ።

የአመራር ለውጥ ከተደረገ ከሁለት ዓመታት ወዲህ ሙስናን ለመዋጋት መንግሥት የአገሪቱ ተቀዳሚ ተግባር አድርጎ እየተንቀሳቀሰ፣ የፖለቲካ ጣልቃ ገብነትም በተወሰነ ሁኔታ እየቀነሰና አጋር መንግሥታትና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ድጋፍና ተነሳሽነት የጨመረ ቢሆንም፣ በአገሪቱ ያለውን አለመረጋጋት እንደ ጥሩ አጋጣሚ በመውሰድ የሙስና ወንጀል በተደራጀ መልኩ እየተፈጸመ መሆኑም ተገልጿል።

ሙስና በከፍተኛ ሁኔታ በተደራጀ ሁኔታ ተጠናክሮ መቀጠሉ የተነገረው፣ የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ከባለድርሻ አካላት ጋር መስከረም 14 ቀን 2013 ዓ.ም. በኢሊሌ ሆቴል ለሁለት ቀናት ባዘጋጀው የጋራ የውይይት መክፈቻ መድረክ ላይ ነው።

በተቋሙ የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ምክትል ዳይሬክተር አቶ ዘለዓለም ፈቃዱ ባቀረቡት የውይይት መነሻ ሐሳብ ላይ እንደገለጹት፣ ሙስናን ከመዋጋት አንፃር መንግሥት ተቀዳሚ ተግባር አድርጎ እየሠራበት ነው። የፖለቲካ ጣልቃ ገብነትም በተወሰነ መልኩ የመቀነስ አዝማሚያ አለው፣ አጋር መንግሥታትና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ድጋፋቸውና ተነሳሽነታቸው ጨምሯል። ምንም እንኳን እንዲህ ዓይነት ተግባራት ያሉ ቢሆንም፣ በሌላ በኩል ደግሞ ባለፉት ሁለት ዓመታት በአገሪቱ ያለውን አለመረጋጋት በመጠቀም የሙስና ሁኔታ በተደራጀ መልኩ እየተፈጸመ መሆኑን ጠቁመዋል።

ከመሬት ወረራ፣ ከባንክ ገንዘብ ማጭበርበር፣ ሐሰተኛ ሰነዶችን ከመጠቀምና ሕገወጥ ገንዘብን ሕጋዊ አስመስሎ ከማቅረብ ጋር በተያያዘ፣ የሙስና ወንጀሎች በስፋት እየጨመሩ መምጣታቸውን ምክትል ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል።

እንደ ምክትል ዳይሬክተሩ ገለጻ፣ ባለፈው ዓመት የተከሰተው ዓለም አቀፍ የኮሮና ወረርሽኝ ለሙስና ወንጀል ምቹ ሁኔታዎችን ፈጥሯል። ሙስና በግሉ ዘርፍም (Private Sector Corruption) ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱንም ተናግረዋል።

በሙስና ወንጀል የተመዘበረ ሀብትን ከማስመለስ አንፃር ጥረቶች እየተደረጉ ቢሆንም፣ በወንጀሉ የተገኘውን በአገር ውስጥና በውጭ አገሮች ተደብቆ የሚገኝን ከ130 ቢሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ማስመለስ አለመቻሉንም ጠቁመዋል።

ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ በ2012 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግሥቱን የፀረ ሙስና ሕጎችን ከማስፈጸምና መፈጸማቸውን ከመከታተል አንፃር የሠራውን እንዳብራሩት፣ የሙስና ወንጀል ምርመራን አስጀምሯል። ይመራልም። በሙስና ወንጀል የክስ መዛግብትን በሚመለከት 582 መዛግብት ለዓቃቤ ሕግ ቀርበው በ400ዎቹ ላይ ምርመራና ድጋፍ ክትትል ማድረጉንና 466 መዛግብት ውሳኔ ማግኘታቸውን አብራርተዋል።

በ2012 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ከ700 ሚሊዮን ብር በላይ የተመዘበረ ሀብት ማስመለስ መቻሉን፣ በተለያዩ ወንጀሎች የተመዘበሩ ሀብቶችን የሚያስመልስ ዳይሬክቶሬት በማቋቋም፣ በአገር ውስጥ የተደበቁና ወደ ውጭ አገሮች የሸሹ ሀብቶችን በተመለከተ የማጥናት (Tracing) እና አገሪቱን የመለየት ሥራ እየተሠራ መሆኑን አብራርተዋል።  

በበጀት ዓመቱ ከመንግሥትና ከግል ባንኮች ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ የተወሰደባቸው ከ40 በላይ የክስ መዛግብት ወደ ፍርድ ቤት ቀርበው በክርክር ላይ መሆናቸውን፣ በርካታ ሚሊዮን ብሮች እንዲታገዱና የውርስ አቤቱታ እንዲቀርብባቸው መደረጉን፣ ከሜቴክና ከሌሎች ትልልቅ የሙስና ወንጀሎች ጋር በተያያዘም ከሦስት ቢሊዮን ብር በላይ ገንዘብ የያዙ የክስ መዝገቦች ፍርድ ቤት ቀርበው ክርክር መደረጉን ምክትል ዳይሬክተሩ አብራርተዋል። በመደበኛ መዝገቦች ላይ የአፈጻጸም ክፍተት ቢኖርም፣ በትልልቅ መዝገቦች ላይ ግን የተሻለ ውሳኔና የችሎት ክርክር አፈጻጸም መመዝገቡን አክሏል።

ምክትል ዳይሬክተሩ ስለቀጣይ አሥር ዓመታት ዕቅድ አፈጻጸምና በ2013 በጀት ዓመት የሥራ ዕቅድ እንዳብራሩት፣ በማስረጃ አለመሟላት ምክንያት በርካታ የተከማቸ መዛግብት ላይ ማስረጃዎችን በማሟላት ውሳኔ እንደሚያሰጡ፣ ‹‹ለምርመራ›› በሚል ተመላሽ የተደረጉ መዛግብትን ከመከታተል ባለፈ፣ በከባድና ውስብስብ ወንጀሎች ምርመራ ላይ በቀጥታ እንደሚሳተፉ ማቀዳቸውን አስረድተዋል።

ከፍተኛ የሕዝብና የመንግሥት ጥቅም ያላቸው ትልልቅ የሙስና ወንጀል ጉዳዮችን ከምርመራ ጀምሮ ቅድሚያና ልዩ ትኩረት ሰጥተው እንደሚሠሩ፣ በዋና ኦዲተር የኦዲት ሥራ የተሠራባቸው የመንግሥት መሥሪያ ቤቶችና ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በተያያዘ ያልተወራረደ ሒሳብ እንዲወራረድና በሕግ የመጠቀም ተግባር በስፋት እንደሚከናወን መታቀዱን ምክትል ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።

ዳይሬክቶሬቱ የተለያዩ ተግዳሮቶች እንደገጠሙት የጠቆሙ ምክትል ዳይሬክተሩ፣ ማስረጃዎችን ከሚመለከታቸው አካላት በተገቢው ፍጥነት ለማግኘት አለመቻሉ፣ በማስረጃዎች ላይ ተጨማሪ ማብራሪያ ለመስጠት ፈቃደኛ አለመሆን፣ አግባብነት የሌላቸው ማስረጃዎችን መስጠት፣ ሙስና የሚፈጸምባቸው ተቋማት ቢኖሩም የሚመለከታቸው አካላት ሪፖርት አለማድረጋቸውን ጠቁመዋል።

የኦዲት ሥራ የሚሠሩ አካላት በመደበኛነት ከሚሠሩ ኦዲት ውጪ ከወንጀል ምርመራ ጋር የተያያዙ ኦዲቶችን በአፋጣኝ ሠርቶ ለመላክ ውስንነት እንዳለባቸው ጠቁመው፣ ጥፋተኛውን በግልጽ ከማሳየት አንፃር ጉድለት እንደሚታይባቸውና በሠሩት ኦዲት ላይ ምስክርነት ሲጠየቁ ፈቃደኛ ለመሆን ተግዳሮቶች እየገጠማቸው መሆኑንም አስረድተዋል።

ሚዲዎችም ሙስናን ከማጋለጥ አንፃር ያላቸው ተሳትፎ አነስተኛ መሆኑን፣ የሙስና ወንጀል ጉዳዮችን በወቅቱ ለሕዝብ ከማሳወቅ አንፃር ችግሮች መኖራቸውንም ምክትል ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። በፋይናንስ ተቋማትና ሌሎች ተቋማትም በርካታ ተግዳሮቶች መኖራቸውንና በተለይም በግሉ ዘርፍ ከሚፈጸም ሙስና ጋር በተያያዘ ምርመራ የሚያደርግ አካል አለመኖሩን አሳውቀዋል።

የአስተዳደር አካላት፣ የልማት ድርጅቶች፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ ዕንባ ጠባቂ ተቋም፣ ፀረ ሙስና ኮሚሽን፣ የፍትሕ አካላት፣ ዋና ኦዲተር፣ ሚዲያና ኅብረተሰቡ ባለድርሻ አካላት ጋር ያለው ግንኙነት ችግር እንዳለበት ጠቁመው፣ በመንግሥትም ሆነ በግሉ ዘርፍ የሚፈጸም ሙስናን በማጋለጥ ረገድ ተባብሮ መሥራት አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል።

የኦዲት ተቋማት የተረጋገጡ ጥፋቶችን ለሚመለከተው አካል ማሳወቅ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተጠያቂነትን ከማረጋገጥ አንፃር አስፈጻሚ ተቋማት ላይ ተፅዕኖ መፍጠር፣ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ደግሞ ከበደል ጋር በተያያዘ በትብብር መሥራት፣ ፀረ ሙስና ኮሚሽን የሥነ ምግባር ትምህርቶችን አጠናቅሮ በመስጠትና ሚዲዎችም የምርመራ ጋዜጠኝነት ሥራ በማናወን ሙስናን እንዲያጋልጡ ጥሪ አቅርበዋል። (ታምሩ ጽጌ፤ ሪፖርተር)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Law, News, Right Column Tagged With: corruption, new birr notes, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule