• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ወደ ንግድ ባንክ በየቀኑ በአማካኝ ከ351 ሚሊዮን ብር በላይ ይገባል

September 29, 2020 01:43 am by Editor Leave a Comment

ከብር ኖት ለውጡ ጋር በተያያዘ በአማካኝ በቀን ከ16 ሺ 700 በላይ ሰዎች አዲስ የሒሳብ ደብተር እንደሚከፍቱ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ። በየእለቱ በአማካኝ ከ351 ሚሊዮን ብር በላይ ወደ ንግድ ባንኩ ገቢ እንደሚሆን ገለጸ።

የባንኩ የኮርፖሬት ኮሚኒኬሽን ተጠባባቂ ዳይሬክተር አቶ የአብስራ ከበደ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቁት፤ የብር ኖቱ መቀየሩ በባንኮች የሚቆጠበውንም ሆነ የሚቀመጠውን ብር ሆነ የደንበኞችን ቁጥር ያሳድጋል።

ባንኩ ከ5ሺ ብር በላይ ለቅያሬ ይዘው የሚመጡ ሰዎች የቁጠባ ደብተር እንዲከፍቱ እያደረገ መሆኑን አመልክተው ፣ የቁጠባ ሒሳብ ደብተር የሚከፍቱ ሰዎች ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩን አስታውቀዋል።

በቀን በአማካኝ ከ16ሺህ 700 በላይ ሰዎች የቁጠባ ሒሳብ እንዲከፈቱ ጠቁመው ፣ የቁጠባ ሂሳቡ በየእለቱ ከ351 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ እንደሚሆን አስታውቀዋል። በቀጣይም የተገልጋዩ ቁጥር እንደሚጨምር ጠቁመዋል። ገንዘብን ቤት ማስቀመጥ በርካታ ችግሮችን ሊያስከትል እንደሚችል አመልክተው ፣ በባንኮች ማስቀመጥ ራስን ከመታደግ አይተናነስም ብለዋል።

ብሔራዊ ባንክ ውክልና የሰጣቸው 36 ገንዘብ አከፋፋይ ቅርንጫፎች እንዳሉም አስታውቀው፣ በነሱ በኩል ከ1600 በላይ ቅርንጫፎቹን ሊያዳርስ በሚችል መልኩ እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ገንዘብ የማዳረሱ ሥራ ከፍተኛ ጥንቃቄን እንደሚጠይቅ ተናግረው፣ ቅርንጫፎቹ ባሉበት ሁሉ በመድረስ ለመስራት ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

የብር ኖት ለውጡ በየቀኑ የሚከናወን በመሆኑ ምን ያህል ቅያሬ እንደተደረገ ለመግለጽ ልዩነቶች ይኖሩታል ያሉት አቶ የአብስራ፣ በዚህም ከሦስት ቀን በፊት በነበረ መረጃ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ16 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በላይ ከብሔራዊ ባንክ ተቀብሎ ለለገንዘብ አከፋፋይ ቅርንጫፎቹ እንዳስረከበ አስታውቀዋል። ቅርንጫፎቹም ትናንትን ጨምሮ የማከፋፈሉን ሥራ እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።

እንደ አቶ የአብስራ ገለጻ፤ ህብረተሰቡ አዲሱን የብር ኖት መቀየሩ ብቻ በቂ አይደለም። ለውጡን ፈጽሞ ወደነበረበት አሰራርም መመለስ የለበትም። ደንበኞች የተለያዩ የቁጠባ ሒሳቦች በመኖራቸው ገንዘባቸውን በባንኮች በማስቀመጥ አገራቸውንም ሆነ ራሳቸውን ከአደጋ ሊጠብቁ ይገባል ብለዋል ።

 በተለይም ገንዘብ በቤታቸው የሚያስቀምጡ ሰዎች ትልቅ ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው። በተለያዩ የተፈጥሮ አደጋዎች ብዙ ንብረቶች እየጠፉና እየወደሙ ናቸው። ከዚያ በተጨማሪም ለዘረፋ የሚዳረጉበት ሁኔታም ሰፊ ነው። ለመጭበርበርም በር ይከፍታል። እነዚህንና መሰል ችግሮች እንዳይደርስባቸው ገንዘባቸውን በባንክ ማስቀመጡን ልምድ ሊያደርጉ እንደሚገባ አመልክተዋል::

 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ1 ሺ 600 በላይ ቅርንጫፎች፤ ከ100 በላይ ንዑስ ቅርንጫፎችና ከ25 ሚሊዮን በላይ ደንበኞች አሉት። ከ5 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ ኤትኤም ካርድ፤ ከ 4 ነጥብ 25 በላይ ደግሞ የሞባይል ባንክና ከ3ነጥብ 8 ሚሊዮን በላይ የሲቢኢ ብር ተጠቃሚዎች እንዳሉት ከባንኩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። (አዲስ ዘመን መስከረም 18/2013)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column Tagged With: new birr notes, new currency

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule