• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ወደ ንግድ ባንክ በየቀኑ በአማካኝ ከ351 ሚሊዮን ብር በላይ ይገባል

September 29, 2020 01:43 am by Editor Leave a Comment

ከብር ኖት ለውጡ ጋር በተያያዘ በአማካኝ በቀን ከ16 ሺ 700 በላይ ሰዎች አዲስ የሒሳብ ደብተር እንደሚከፍቱ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ። በየእለቱ በአማካኝ ከ351 ሚሊዮን ብር በላይ ወደ ንግድ ባንኩ ገቢ እንደሚሆን ገለጸ።

የባንኩ የኮርፖሬት ኮሚኒኬሽን ተጠባባቂ ዳይሬክተር አቶ የአብስራ ከበደ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቁት፤ የብር ኖቱ መቀየሩ በባንኮች የሚቆጠበውንም ሆነ የሚቀመጠውን ብር ሆነ የደንበኞችን ቁጥር ያሳድጋል።

ባንኩ ከ5ሺ ብር በላይ ለቅያሬ ይዘው የሚመጡ ሰዎች የቁጠባ ደብተር እንዲከፍቱ እያደረገ መሆኑን አመልክተው ፣ የቁጠባ ሒሳብ ደብተር የሚከፍቱ ሰዎች ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩን አስታውቀዋል።

በቀን በአማካኝ ከ16ሺህ 700 በላይ ሰዎች የቁጠባ ሒሳብ እንዲከፈቱ ጠቁመው ፣ የቁጠባ ሂሳቡ በየእለቱ ከ351 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ እንደሚሆን አስታውቀዋል። በቀጣይም የተገልጋዩ ቁጥር እንደሚጨምር ጠቁመዋል። ገንዘብን ቤት ማስቀመጥ በርካታ ችግሮችን ሊያስከትል እንደሚችል አመልክተው ፣ በባንኮች ማስቀመጥ ራስን ከመታደግ አይተናነስም ብለዋል።

ብሔራዊ ባንክ ውክልና የሰጣቸው 36 ገንዘብ አከፋፋይ ቅርንጫፎች እንዳሉም አስታውቀው፣ በነሱ በኩል ከ1600 በላይ ቅርንጫፎቹን ሊያዳርስ በሚችል መልኩ እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ገንዘብ የማዳረሱ ሥራ ከፍተኛ ጥንቃቄን እንደሚጠይቅ ተናግረው፣ ቅርንጫፎቹ ባሉበት ሁሉ በመድረስ ለመስራት ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

የብር ኖት ለውጡ በየቀኑ የሚከናወን በመሆኑ ምን ያህል ቅያሬ እንደተደረገ ለመግለጽ ልዩነቶች ይኖሩታል ያሉት አቶ የአብስራ፣ በዚህም ከሦስት ቀን በፊት በነበረ መረጃ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ16 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በላይ ከብሔራዊ ባንክ ተቀብሎ ለለገንዘብ አከፋፋይ ቅርንጫፎቹ እንዳስረከበ አስታውቀዋል። ቅርንጫፎቹም ትናንትን ጨምሮ የማከፋፈሉን ሥራ እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።

እንደ አቶ የአብስራ ገለጻ፤ ህብረተሰቡ አዲሱን የብር ኖት መቀየሩ ብቻ በቂ አይደለም። ለውጡን ፈጽሞ ወደነበረበት አሰራርም መመለስ የለበትም። ደንበኞች የተለያዩ የቁጠባ ሒሳቦች በመኖራቸው ገንዘባቸውን በባንኮች በማስቀመጥ አገራቸውንም ሆነ ራሳቸውን ከአደጋ ሊጠብቁ ይገባል ብለዋል ።

 በተለይም ገንዘብ በቤታቸው የሚያስቀምጡ ሰዎች ትልቅ ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው። በተለያዩ የተፈጥሮ አደጋዎች ብዙ ንብረቶች እየጠፉና እየወደሙ ናቸው። ከዚያ በተጨማሪም ለዘረፋ የሚዳረጉበት ሁኔታም ሰፊ ነው። ለመጭበርበርም በር ይከፍታል። እነዚህንና መሰል ችግሮች እንዳይደርስባቸው ገንዘባቸውን በባንክ ማስቀመጡን ልምድ ሊያደርጉ እንደሚገባ አመልክተዋል::

 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ1 ሺ 600 በላይ ቅርንጫፎች፤ ከ100 በላይ ንዑስ ቅርንጫፎችና ከ25 ሚሊዮን በላይ ደንበኞች አሉት። ከ5 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ ኤትኤም ካርድ፤ ከ 4 ነጥብ 25 በላይ ደግሞ የሞባይል ባንክና ከ3ነጥብ 8 ሚሊዮን በላይ የሲቢኢ ብር ተጠቃሚዎች እንዳሉት ከባንኩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። (አዲስ ዘመን መስከረም 18/2013)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column Tagged With: new birr notes, new currency

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ October 30, 2023 10:27 am
  • የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ October 26, 2023 01:30 pm
  • ጥቅምት 15 ለምን? October 26, 2023 01:29 am
  • “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት” October 26, 2023 12:57 am
  • “ውትድርና ሕይወቴ ነው” October 26, 2023 12:13 am
  • መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው October 20, 2023 05:07 pm
  • “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ October 20, 2023 04:47 pm
  • 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ታሰሩ October 18, 2023 04:29 pm
  • በተማሪዎች ፈተና ውጤት ለታየው ውድቀት ትምህርት ሚ/ር ኃላፊ መሆን አለበት ተባለ October 18, 2023 04:00 pm
  • ቀይ ባሕር እና ዓባይ “የኅልውና ጉዳይ ናቸው”፤ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል” October 13, 2023 10:04 pm
  • ከ3,106 ትምህርት ቤቶች 1,328ቱ (44%) አንድም ተማሪ አላሳለፉም October 10, 2023 01:51 pm
  • “አቋጥሬ” በአማራ ክልል እያጫረሰ ነው፤ ” ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ” ነዋሪዎች October 10, 2023 09:07 am
  • እሸቴ አሸባሪ፤ ቲዲኤፍ/ትሕነግ “ሰማዕት” – የዘመናችን ጉድ! October 7, 2023 06:47 am
  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule