• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ወደ ንግድ ባንክ በየቀኑ በአማካኝ ከ351 ሚሊዮን ብር በላይ ይገባል

September 29, 2020 01:43 am by Editor Leave a Comment

ከብር ኖት ለውጡ ጋር በተያያዘ በአማካኝ በቀን ከ16 ሺ 700 በላይ ሰዎች አዲስ የሒሳብ ደብተር እንደሚከፍቱ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ። በየእለቱ በአማካኝ ከ351 ሚሊዮን ብር በላይ ወደ ንግድ ባንኩ ገቢ እንደሚሆን ገለጸ።

የባንኩ የኮርፖሬት ኮሚኒኬሽን ተጠባባቂ ዳይሬክተር አቶ የአብስራ ከበደ በተለይ ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንዳስታወቁት፤ የብር ኖቱ መቀየሩ በባንኮች የሚቆጠበውንም ሆነ የሚቀመጠውን ብር ሆነ የደንበኞችን ቁጥር ያሳድጋል።

ባንኩ ከ5ሺ ብር በላይ ለቅያሬ ይዘው የሚመጡ ሰዎች የቁጠባ ደብተር እንዲከፍቱ እያደረገ መሆኑን አመልክተው ፣ የቁጠባ ሒሳብ ደብተር የሚከፍቱ ሰዎች ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩን አስታውቀዋል።

በቀን በአማካኝ ከ16ሺህ 700 በላይ ሰዎች የቁጠባ ሒሳብ እንዲከፈቱ ጠቁመው ፣ የቁጠባ ሂሳቡ በየእለቱ ከ351 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ እንደሚሆን አስታውቀዋል። በቀጣይም የተገልጋዩ ቁጥር እንደሚጨምር ጠቁመዋል። ገንዘብን ቤት ማስቀመጥ በርካታ ችግሮችን ሊያስከትል እንደሚችል አመልክተው ፣ በባንኮች ማስቀመጥ ራስን ከመታደግ አይተናነስም ብለዋል።

ብሔራዊ ባንክ ውክልና የሰጣቸው 36 ገንዘብ አከፋፋይ ቅርንጫፎች እንዳሉም አስታውቀው፣ በነሱ በኩል ከ1600 በላይ ቅርንጫፎቹን ሊያዳርስ በሚችል መልኩ እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል። ገንዘብ የማዳረሱ ሥራ ከፍተኛ ጥንቃቄን እንደሚጠይቅ ተናግረው፣ ቅርንጫፎቹ ባሉበት ሁሉ በመድረስ ለመስራት ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

የብር ኖት ለውጡ በየቀኑ የሚከናወን በመሆኑ ምን ያህል ቅያሬ እንደተደረገ ለመግለጽ ልዩነቶች ይኖሩታል ያሉት አቶ የአብስራ፣ በዚህም ከሦስት ቀን በፊት በነበረ መረጃ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ16 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በላይ ከብሔራዊ ባንክ ተቀብሎ ለለገንዘብ አከፋፋይ ቅርንጫፎቹ እንዳስረከበ አስታውቀዋል። ቅርንጫፎቹም ትናንትን ጨምሮ የማከፋፈሉን ሥራ እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።

እንደ አቶ የአብስራ ገለጻ፤ ህብረተሰቡ አዲሱን የብር ኖት መቀየሩ ብቻ በቂ አይደለም። ለውጡን ፈጽሞ ወደነበረበት አሰራርም መመለስ የለበትም። ደንበኞች የተለያዩ የቁጠባ ሒሳቦች በመኖራቸው ገንዘባቸውን በባንኮች በማስቀመጥ አገራቸውንም ሆነ ራሳቸውን ከአደጋ ሊጠብቁ ይገባል ብለዋል ።

 በተለይም ገንዘብ በቤታቸው የሚያስቀምጡ ሰዎች ትልቅ ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው። በተለያዩ የተፈጥሮ አደጋዎች ብዙ ንብረቶች እየጠፉና እየወደሙ ናቸው። ከዚያ በተጨማሪም ለዘረፋ የሚዳረጉበት ሁኔታም ሰፊ ነው። ለመጭበርበርም በር ይከፍታል። እነዚህንና መሰል ችግሮች እንዳይደርስባቸው ገንዘባቸውን በባንክ ማስቀመጡን ልምድ ሊያደርጉ እንደሚገባ አመልክተዋል::

 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ1 ሺ 600 በላይ ቅርንጫፎች፤ ከ100 በላይ ንዑስ ቅርንጫፎችና ከ25 ሚሊዮን በላይ ደንበኞች አሉት። ከ5 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ ኤትኤም ካርድ፤ ከ 4 ነጥብ 25 በላይ ደግሞ የሞባይል ባንክና ከ3ነጥብ 8 ሚሊዮን በላይ የሲቢኢ ብር ተጠቃሚዎች እንዳሉት ከባንኩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል። (አዲስ ዘመን መስከረም 18/2013)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Middle Column Tagged With: new birr notes, new currency

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule