[ጁን 8፤ 2010] ዋኤል ጎኒም (ዕድሜ 28) እንደወትሮው ዜናዎችን ለመቃረም፣ ከዘመድና ወዳጅ ጋር ለመወያየት ዱባይ ከሚገኘው መኖሪያ ቤቱ ተቀምጦ በፌስቡክ መስኮት ወደ ትውልድ ሀገሩ ግብጽ ዘለቀ፤ በዚያን ዕለት ያነበበው ዜና እና የተመለከተው ፎቶ ስሜቱን አወከው፣ እረፍት ነሳው፣ ዜናው አሌክሳንድሪያ ውስጥ በሙባረክ የጸጥታ ሀይሎች በግፍ ስለተገደለው ካሊድ ሰይድ (ዕድሜ 28) ነበር፡፡ ሶሻል ሚዲያ ላይ ሲዘዋወር የነበረው የካሊድ አስከሬን በዐይን ለማየት ይከብዳል፡፡ “በዛ አሰቃቂ የካሊድ ፎቶ ውስጥ ራሴን አየሁት፣ በካሊድ ቦታ እኔም ልሆን እችል ነበር ብዬ አሰብኩ” ይላል ዋኤል በዚያች ቅጽፈት የተሰማውን ስሜት ሲገልጽ፣ ከቁጭትና ንዴት ባለፈ አንድ ነገር ማድረግ እንዳለበት አሰበ፤ ጊዜ ሳያጠፋ ማንነቱን ደብቆ "We are all Khaled Said/ሁላችንም ካሊድ ሰይድ ነን" … [Read more...] about ሕልመኛና የቆሰለው አውሬ ጃዋር [እና] ዋኤል ጎኒም
Opinions
የኔ ሃሳብ
ዘረኛ ፋሺስቶችን ለፍርድ እናቅርብ
የፋሽስታዊው አመለካከት ያላቸው (ethno-fascists) የጸጋዬ አራርሳ፣ የህዝቄል ገቢሳ፣ መሰሎቻቸው፣ እንዲሁም የትግራይ ሚዲያ ሀውስ መርዘኛ፡ ሃሰተኛ ቅስቀሳዎችና ትርክቶች የብሄር ለብሄር፣ የዘር ፍጅት (ጄኖሳይድ) ከማድረሳቸው በፊት በአለም ዙሪያ የሚገኙ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ሁሉ በጋራ ሆነው የተደራጀ፣ የተቀናጀ፣ የተናበበ ስራ መስራት ይገባል። ባልተናበበና በተበታተነ ሁኔታና እንቅስቃሴ ውጤት ለማምጣት እጅግ አዳጋች ይሆናል፣ ሁሉም ባለው መሰለፍ ይገባል፣ የመጣውን ኣደጋ ለመከላከል እንደ ኢትዮጵያውያን ዜጎች በጋራ መቆም የግድ ነው። የፖለቲካ አመለካከት ወደ ጎን አድርጎ በአንድ ላይ፣ በጋራ መቆም ወሳኝ ይመስለኛል። የሁላችንም ሀገር የሆነችው ቤተሰብ፣ ዘመድ፣ አዝማዶች፣ ወገኖችና፣ ባጠቃላይም ህዝባችን የሚኖርባት ሀገረ ኢትዮጵያ ውስጥ እየሆነ ያለው ሁኔታ ፍጹም ወደ … [Read more...] about ዘረኛ ፋሺስቶችን ለፍርድ እናቅርብ
እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እንደ ስያሜው የኢትዮጵያዊያን ነው። ከአቶ ተፈራ ደግፌ 1956 ዓ.ም. እስከ አቶ በቃሉ ዘለቀ 2010 ዓ.ም. በትውልድ ቅብብሎሽ ዘር ሳይለይ፣ ጎሳ ሳይመርጥ የኢትዮጵያና የኢትዮጵያዊያን ሆኖ የዘለቀ አንጋፋ ባንክ። አቶ ተፈራ ደግፌ መጋቢት 12 ቀን 1956 ዓ.ም. ባንኩን ከመረከባቸው በፊት፣ ባንኩ ለኢትዮጵያዊያንና ለአገራችን እምብዛም ግድ በማይሰጣቸው ለራሳቸው ጥቅምና የኢኮኖሚ ዕድገት በሚታትሩ የውጭ አገር ዜጎች ይመራ ነበር። ህንዳዊያን፣ አርመኖች፣ ግብፆችና አውሮፓዊያን አቶ ተፈራ ወደ ሥልጣን ከመምጣታቸው በፊት ባንኩን የኢትዮጵያ መንግሥት ባንክ በሚል ስያሜ ያስተዳድሩ የነበሩ ናቸው። ይህን የተረዱት አፄ ኃይለ ሥላሴ ጣሊያን አገራችንን ከለቀቀ በኋላ ኢትዮጵያዊያን የባንክ፣ የኢንሹራንስና የሕግ ዕውቀቶችን እንዲያዳብሩ ወደ ተለያዩ የአውሮፓ … [Read more...] about እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥
ኢትዮጵያ ስንት ልጆች ወለደቸ፤ ስንቱን አስተማራቸ፤ ስንቱን አቋቁማ ለአቅመ ዓዳም አበቃች፤ ስንት ጉድስ ተሸከመች። ቆጥረን ስለማንዘልቀው ቤቱ ይቁጠረው ብለን ብናልፈው ይበቃል። ብዙ ጉድ እንደተሸከመች ብናውቅም ብዙ ልጆቿ ሸክሟን ለማቅለል፤ ችግሯን ለመቅረፍ፤ እድገቷን ለማፋጠን ብዙ ጥረውላታል። በእውቀታቸው፤ በጉልበታቸውና በሃብታቸው ባቻ ሳይሆን ሕይወታቸውን ጭምር ገብረውላታል፤ እየገበሩም ይገኛል። በአንፃሩ በሃብቷ ተምረው ስሟን ያጎደፉ፤ ሕልውናዋን የተፈታተኑ ከሃዲዎች መኖራቸውን ስናይ እናዝናለን። እነዚህን የመሰሉ ልጆቿ ሃገሪቱን አመድ አፋሽ አርገዋታል። ይህ የቅርብ ጊዜ ክስተት ብቻ ሳይሆን በሶስት ሽህ ዘመን ጉዞዋ ሁሉ ሲከሰት የኖር ለመሆኑ ታሪክ ይነግረናል። ያአሁኑን ከጥንቱ ለየት የሚአደርገው ያለንበት ሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን መሆኑ፤ ልጆቿ ዘመናዊ ትምህርት … [Read more...] about ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥
ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል?
የዛሬ ሃምሳ ዓመት ገደማ መሰለኝ የያኔው ወጣት የዩኒቬርሲቲ ተማሪው ኢብሳ ጉተማ “ኢትዮጵያዊው ማን ነው?” በሚል ርዕስ አንድ ጽሁፍ አቅርቦ ለውጥ ፈላጊውን የዩኒቬርሲቲውን ማህበረሰብ ጥም ለማርካት የሞከረው። አብዛኛው የዩኒቨርሲቲው ተማሪ የፊውዳል ሥርዓቱ አገሪቷን ወደፊት እንዳትራመድ ጠፍንጎ የያዛት መሆኑን የተረዱና ሥርዓቱ ካልተለወጠ የሕዝቦቿ አብሮነት ውሎ አድሮ መሸረሸሩ አይቀሬ መሆኑን ተገንዝበው ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ለማናበብ መላ ይመቱ ነበርና የዚህ ንቁ ተማሪ ግጥም ጊዜውን ጠብቆ የመጣ ነበር። በዚሁ ጊዜ ነበር ከተማሪው እንቅስቃሴ መሪዎች አንዱ የነበረው ዋለልኝ መኮንን የብሄር ጥያቄን አስመልክቶ ታሪካዊውን ጽሁፍ ያቀረበው። አንዳንዶች ያኔም ሆነ ዛሬ እነዚህን ጽሁፎችን አስመልክቶ ሁለቱን ንቁ የተማሪው ማህበረሰብ አባላትን አገሪቷን ለመበታተን ሆን ብለው … [Read more...] about ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል?
“ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል”
የዚህች ሃገር ችግር የሴራ ፓለቲካ ነው። ጀዋር ሞሃመድ ዛሬ (ሰኞ) ለማየት የሚሰቀጥጥ አንድ ቪዲዮ ለጠፈ። በጣም አንጀት የሚበላ ጥቁርም ሆነ ነጭ ኦሮሞም ሆነ አማራ፤ የሰውን ልጅ እንደዛ በጭካኔ ማሰቃየት ከባድ የሰብዓዊነት ጥሰት ነው። የህግ ተጠያቂነት ደግሞ ግድ ነው፤ ግን ደግሞ ማነው ይህን ወንጀል የፈጸመው? ዋናው ነገር ይህንን ወንጀል የፈጸመውን እና ያስፈጸመውን ለይቶ ለህግ ማቅረብ ነው። ቪዲዮው ልጁ ግፍ ሲፈጸምበት እንጂ ግፍ የፈጸሙትን አያሳይም ለምን ወንጀለኞችን መደበቅ አስፈለገ? ታስቦበት ስለተፈጸመ ነው። በሴራ ከመዘፈቅ ይልቅ ወንጀሉን የፈጸሙትን በማጋለጥ ለህግ የበላይነት መተባበር ነበር። ግን ያንን ትተው ግፍ የተፈጸመበትን በማሳየት ህዝብን ማበሳጨት ነበር የተፈለገ። ወንጀሉን የፈጸመውን በመደበቅ አማራ ኦሮሞን አሰቃየ ማለት የፖለቲካ ሴራ ነው። ነገሩ … [Read more...] about “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል”
ለዋዜማ ሬዲዮ – የህዳሴውን ግድብ ዜናችሁን ላስተካክልላችሁ
የውሃ ሃብት ባለሙያ ነኝ፤ የግድቡ ጉዳይ ቀጥታ ከሙያዬ ጋር ባይገናኝም እንደዜጋ ሁኔታውን በቅርብ እከታተላለሁ፤ ፖለቲካንም እንዲሁ። የዋዜማን ሰዎች ዋዜማ ሳትሆኑ ነው የማውቃችሁ፤ ካገር ከመውጣታችሁ በፊት ማለቴ ነው። የማውቃችሁም በግል ሳይሆን እንደማንኛውም የሚዲያ ተጠቃሚ ነው፤ ስለዚህ እናንተ አታውቁኝም። አሁንም ዋዜማን እከታተላለሁ። ከዳያስፖራ ከሚመነጩት የዜና ዘገባዎችና መረጃዎች የእናንተ በተሻለ መጠን ተዓማኒነትና ሥርዓት የያዘ ነው ብዬ ስለማምን አነባችኋለሁ። “ኢትዮጵያን ቋሚ ባለዕዳ የሚያደርገው የህዳሴ ግድብ ስምምነት ላይ መንግስት የመፈረም ፍላጎት እያሳየ ነው” በሚል ርዕስ ያወጣችሁትን ዘገባ አንብቤዋለሁ። ዘገባው እንደሚለው ለረጅም ጊዜ የተጠበቀውን ሰነድ ስምምነት እንድትፈርም ኢትዮጵያ ግፊት እየተደረገባት እንደሆነ፤ ይህም “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ … [Read more...] about ለዋዜማ ሬዲዮ – የህዳሴውን ግድብ ዜናችሁን ላስተካክልላችሁ
ካድሬውና ገጣሚው
ሁለትም ናቸው። በግብ ግን የሚለያቸው የለም። ያን ጊዜ በአካል ላይተዋወቁ ይችሉ ይሆናል። በመንፈስ ግን የአንድ እናት ልጆች ናቸው። ትላንት ገጽ ለገጽ ሳይገናኙ፡ በስምም ሳይተዋወቁ በአንድ ካምፕ ለአንድ ሰፈር ሲጫወቱ ነበር። በመሃል መንገዳቸው ተለያየና በየፊናቸው ህይወትን ቀጠሉ። አንደኛው የህወሀት ቃለቀባይ ስጋጃ አንጣፊ ሆኖ ተከሰተ። ሌላኛው በኪነጥበብና መዝናኛ መድረኮች የጭቃ ውስጥ እሾህ ባህርይ ተላብሶ ብቅ አለ። ነገ እንደሚገናኙ ላያውቁ ይችሉ ይሆናል። አንድ ቀን የመንፈስ ጥምረታቸውን በአካል ተገናኝተው የሚያጠናክሩበት ጊዜ እንደሚኖር ሀገር ቤት ሳሉ ላያውቁት ይችሉም ይሆናል። የባህርይ አምላክ፡ በመንፈስ ያጣመራቸው ጌታ ፍቃድ ሆኖ ግን ሳያውቁት በባህር ማዶ ተገናኙ። በአካልም በመንፈስም ተቀራረቡ። በየግል በልባቸው የተከመረውን የጥላቻና የእኩይ መንፈስ በጋራ … [Read more...] about ካድሬውና ገጣሚው
ፕሮግራም አልባ “የሕዝብ አደራ” ተሸካሚዎች
ባላፈው ሳምንት “ከዘቀጥንበት ወጥተን እንዴት ወደ ፊት እንራመድ?” በሚል ርዕስ ያቀረብኩት ጽሁፍ በተለያዩ የሚዲያ ገጾች ላይ ከታተመ በኋላ፣ በቅርጽ የተለያዩ በይዘት ግን የሚመሳሰሉ ብዙ አስተያየቶች ከተለያዩ አቅጣጫዎች ደርሰውኝ ይዘታቸውን ከገመገምኩ በኋላ ያነሳሁት ጉዳይ ተጨማሪ ትኩረት የሚያስፈልገው መስሎ ስለታየኝ ይህንን ተከታይ ጽሁፍ ለማሳተም ወሰንኩ። በዚህ ጽሁፌ ሁለት ቁም ነገሮችን ማለትም “ሕዝባዊ አደራና” “የፖሊቲካ ድርጅቶች ፕሮግራም ግልጽ አለመሆንን” በተመለከተ አንዳንድ አስተያየት ሰጥቼ ሌሎችም የየበኩላቸውን አንዲያዋጡ ለመጋበዝ እሻለሁ። የኔ ሃሳብ ብቻ ትክክል ነው ከሚለው ፊውዳላዊና ኋላ ቀር አስተሳሰብ ተላቅቀን በየበኩላችን የሚሠማንን ወደ ውይይት መድረኩ ካመጣን አንድ ታላቅ ታሪካዊ እርምጃ የወሰድን መሆኑን አውቀን ሁላችንም እንድንካፈልበት ከወዲሁ ለማሳሰብ … [Read more...] about ፕሮግራም አልባ “የሕዝብ አደራ” ተሸካሚዎች
የኢትዮጵያ ጣምራ ፌደራሊዝም ተቋም
ኢትዮጵያ ወደ ፍጹም ህብረት! Towards a Perfect Union! ቀን 1/27/20 የኢትዮጵያ ጣምራ ፌደራሊዝም ተቋም የመጀመሪያ ሰሚናሩን አጠናቀቀ! የኢትዮጵያ ጣምራ ፌደራሊዝም ተቋም (DFIE Dual Federalism Institute for Ethiopia) በ January 18, 2020, በኢትዮጵያ ኤምባሲ አዳራሽ ውስጥ ክቡር አምባሳደር ፍጹም አረጋን ጨምሮ የተለያዩ የፖለቲካና ሲቪክ ድርጅት ተወካዮችና ምሁራን በተገኙበት የአንድ ቀን ሙሉ ሰሚናር አድርጓል። በዚህ ሰሚናር ላይ ለኢትዮጵያ ተብሎ የተዘጋጀውን አዲስ ቅርጸ መንግስት (Government Structure) አስተዋውቋል። ይህ አዲስ ቅርጸ መንግስት የኢትዮጵያ ጣምራ ፌደራሊዝም ይሰኛል። በዚሁ እለት የኢትዮጵያውያንን ህብረት ታሪካዊ ጉዞ በመገምገም ህብረታችንን ወደ ፍጹም ህብረት ሊያደርስ … [Read more...] about የኢትዮጵያ ጣምራ ፌደራሊዝም ተቋም