• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከሚገድለኝ ሰይጣን ይልቅ የሚሰድበኝ ባለስልጣን ይሻለኛል! ሽመልስ የተናገረው በወቅቱ ትክክል ነው‼️

August 9, 2020 03:51 pm by Editor 3 Comments

አቶ ሽመልስ አብዲሳ “በትላንትናው እለት የተናገረው ነው” ተብሎ የተሰራጨው መረጃ ከሰባት ወር በፊት የብልፅግና ፓርቲ ገና በምስረታ ሂደት ላይ እያለ የተናገረው መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። በወቅቱ የድርጅቱን አባላትና አመራሮች በኦቦ ለማ መገርሳ፣ ወ/ሮ ጠይባ እና በዶ/ር ሚልኬሳ ከሚመራው ብሔርተኛ ቡድን ለመነጠልና በድርጅቱ ውስጥ ተፈጥሮ በነበረው የኃይል ሹኩቻ አሸናፊ ሆኖ ለመውጣት በሚደረግ ጥረት የተናገረው እንደሆነ ተረጋግጧል።

አቶ ሽመልስ የተናገረበት ግዜና ቦታ ምን ያህል የተለያየ ቢሆንም አዲስ አበባን አስመልክቶ የተናገረው ነገር መቼም፥ እንዴትም ትክክል አይሆንም። ይሁን እንጂ በወቅቱ ድርጅቱ ውስጥ የጃዋር መሃመድ ጉዳይ አስፈፃሚ የነበሩት ከላይ የተጠቀሱት የኦዴፓ አመራሮች ከኮዬ_ፈቼ ኮኖደሚኒዬም ጋር በተያያዘ ሲያራምዱት የነበረው አቋምና ጉዳዩ በብሔርተኞቹ ዘንድ የነበረው ድጋፍ ሲታሰብ እነ ሽመልስ የነበሩትን አጣብቂኝ በግልጽ ያሳያል። ያ ባይሆን ኖሮ ተቀናቃኙ ቡድን አሸናፊ ቢሆን ኖሮ አሁን ላይ ጃዋር_መሃመድ መገኛው እስር ቤት ሳይሆን ቤተመንግሥት ይሆን ነበር። ስለዚህ አቶ ሽመልስ የተናገረውን ነገር ከዚህ አንፃር ማየት ተገቢ ነው።

ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ ከሰባት ወር በፊት የተደረገውን ንግግር ልክ ትላንት እንደተደረገ ተደርጎ የወጣው የጃዋር ጉዳይ አስፈፃሚዎች ለግምገማ ሲቀርቡ እንደሆነ መገንዘብ ይቻላል። ስለዚህ የመንግሥት ሥልጣንና ኃላፊነት ይዘው በአክቲቪስት የሚመሩ፤ ለምሳሌ ጥቅምት 12/2012 ማታ አቶ ጃዋር መሃመድ ባስነሳው ሁከትና ብጥብጥ በንፁሃን ዜጎች ላይ ጥቃትና ጉዳት እንዳይደርስ ከመከላከል ይልቅ የጃዋር ጠባቂ ለመሆን በውድቅት ሌሊት መኖሪያ ቤቱ ድረስ የሄዱት ለማና ጠይባ፣ ልክ በድርጅቱ ግምገማ ሲደረግባቸው ከሰባት ወር በፊት የተቀዳን ንግግር ለፅንፈኛ የአማራ አክቲቪስቶች Leak አደረጉ። ህዝቤ እየተነሳ እሪሪሪሪ አለ።

ነገር ግን ይሄን መረጃ አሾልኮ ያወጣው ቡድን ቀንደኛ የጃዋር ጉዳይ አስፈፃሚዎች፣ ይህንንም ያደረጉት ጃዋርንና ግብረ-አበሮቹን ለማስፈታትና እንደለመደው አናታችን ላይ እንዲፈነጭ ለማድረግ ነው። ስለዚህ ይህን ሤራና ተንኮል የጠነሰሱት በግምገማ ከአባልነት ሊሰረዙ እንደሆነ ሲያውቁ ነው። ነገር ግን የእነሱ ቡድን አሸናፊ ሆኖ ቢወጣ ኖሮ ሽመልስ የተናገረውን እነሱ በተግባር የሚያደርጉትን እና ያደረጉትን ነው። የኮዬ ፈጬ ኮንደሚኒየም ለነዋሪዎች ሊተላለፍ በኦሮሚያና አዲስ አበባ መካከል ያለው የድንበር ጉዳይ መፍትሔ ስላላገኘ ብለው የፃፉት ደብዳቤ ለዚህ ማሳያ ነው። በአጠቃላይ አቶ ሽመልስ ከሰባት ወር በፊት የተናገረው ከዚህ ፅንፈኛ ቡድን ጋር በነበረው የኃይል ሽኩቻ አሸናፊ ሆኖ ለመውጣት ነው።

“ዋሽቶ ማስታረቅ” እንደሚባለው አቶ ሽመልስ የተናገረውን ተናግሮ ድርጅቱና የክልሉ መንግሥትን ከእንዲህ ያለ ፅንፈኛ ቡድን መታደግ በመቻሉ ሊያስመሰግነው ይገባል። ከሰባት ወር በፊት ሆነ ትላንት በተለይ በአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ የተንፀባረቀውን አቋም ፋሽታዊ ነው በማለት አውግዤያለሁ። ነገር ግን ሽመልስ ሆነ ሌላ ሰው ይሄን የተናገረው በእውን የተረጋገጠ ፋሽታዊ አቋምና አመለካከት ያላቸው አመራሮች በክልሉም ሆነ በሀገር ደረጃ አሸናፊ ሆነው እንዳይወጡ ለማድረግ በሚል ስለሆነ “እሰይ አበጀህ” ብዬዋለሁ። ምክንያቱም ያ ቡድን ባይገታ ኖሮ ምን ሊከሰት እንደሚችል በዚህ አመት ጥቅምት 12 እና ሰኔ 22 በተግባር አይተንዋል።

ስዩም ተሾመ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Right Column

Reader Interactions

Comments

  1. getachew says

    August 10, 2020 07:40 am at 7:40 am

    እንደው ዝም ይሻላል

    Reply
  2. በለው ! says

    August 10, 2020 09:25 pm at 9:25 pm

    “ከሚገድለኝ ሰይጣን ይልቅ የሚሰድበኝ ባለስልጣን ይሻለኛል! ሽመልስ የተናገረው በወቅቱ ትክክል ነው‼️” ስዩም ተሾመ
    ቼ በለው!
    ** ይህ ተርቦም፡ ተጠምቶም፡ ታርዞም፡ ተቃጥሎም ፡ተቆራርጦም፡ተፈናቅሎም፡ተገሎም የሚጨፍር ቆራጥ የፈረደበት ቦርቃቃ ሕዝብ ከሰይጣንና ከባለሥልጣን ውግረት ሌላ ምን ምርጫ አለው! ወደሽ ነው ገጣቢት ንጉስ ትመርቂ…
    “አቶ ሽመልስ አብዲሳ “በትላንትናው እለት የተናገረው ነው” ተብሎ የተሰራጨው መረጃ ፒፒፒ (የፒኮክ ብልጥገና ፓርቲን )ከብሔርተኛ ቡድን ለመነጠልና በድርጅቱ ውስጥ ተፈጥሮ በነበረው የኃይል ሹኩቻ አሸናፊ ሆኖ ለመውጣት በሚደረግ ጥረት የተናገረው እንደሆነ ተረጋግጧል።”…
    **ይህ ንግግር ስለተፎካካሪ ቡድን አክራሪና ፅንፈኛ ጎራ መለየት አያወራም! በትክክል የሸፍጥ(ሴራ፡ሰሬ) ፓለቲካ የህወሓት ትምህርቶችን ብልጥገና እንዴት በፈጠነና በተቀናጀ መልኩ ኢዴፓን አጃጅለን…(አግባብተንም ግራ አጋብተንም) ኢትዮጵያን በልካችን አፍርሰን ሠርተን፤ በገዳ ሥርዓት በአፍሪካ ቀንድ የበላይነትን ተቀዳጅተን በሕዝብ ቁጥር ለሚቀጥሉት ሶስት ሺህ ዓመት በኦሮሙማ የሚመረጥና በኦሮሞ የሚመራ ብልጥገና እንዴት እንደሚቀጥል የተነደፈ ሐሳብ የተንፀባረቀበት ንግግር ቀደሞ፡ ሽመልስ አብዲሳም ይሁን ዓብይ አህመድ ሰበርናቸው አበረርናቸው ተመልሰው ያለእኛ ፍቃድ እዚህ አይደርሱም ዘመንና ሥልጣን በእጃችን ነው ” ሲሉ አባራሪና ተባራሪ፡ ባለቤትና መጤ ፡ባለግዜና ባለብዙ የሰው ኅይል አንደኛና ሁለተኛ ዜጋ ብልጥግና መሥርቷል! ስለዚህ ከሰይጣንና ከሥድብ ማማረጥ ቅንጦት ነው።
    እንዳለች እንደወረድች መዋጥ ሕገመንግስታዊ ግዴታ መሆኑን መረዳት ያሻል…አንዳንዴ ሲተነተን መበተን አለ!!
    “… ተቀናቃኙ ቡድን አሸናፊ ቢሆን ኖሮ አሁን ላይ ጃዋር_መሃመድ መገኛው እስር ቤት ሳይሆን ቤተመንግሥት ይሆን ነበር። ስለዚህ አቶ ሽመልስ የተናገረውን ነገር ከዚህ አንፃር ማየት ተገቢ ነው።”
    **ጀዋር ኮዬ ፈጬ ላይ ሰው ሊፈጭ ሜንጫና ሚስማር ይዞ ሲወጣ ሁለተኛው መንግስት ሆኖ ታምኖበት እንጂ የሕንጻው መሐንዲስ ወይም ቁጠባ ያደረገ ቡድን አዛዥ ሆኖ አልነበረም። ማነህ? ወዴት ነህ? ያለው የለም! ያም የሚነግረን “አንተ በዚያ ቅደም እኛ በሩቁ እንጠብቅሃለን የፈራ ይሸሻል ትወርሳላችሁ” ተብሎ ነው።የቡራዩን የዘር ማፅዳት የተመከረበት ሥራ ታዝበናል፡ በጦፈው የኮረና የዓለም ሥጋት ወረርሽኝ በሽታ ዘመን መንገድ የተጣሉ ዜጎችን አይተናል፡ ሥራውም በደንብ የተቀናጀ በሥላጣን ተዋረድ በመመሪያ የተደገፈ ነው ሽመልስ አሁን የተናገረውም በቋንቋና በኢኮኖሚ ውህድ ማንነት ያለውን ጥሩ የአዲስ አበቤን ሕዝብ ኑሮ ማተራመስ፡ መስበርና ማፍረስ! አጠና ገጀራ ይዞ ከማስፈራራት የሰለጠነና ጥሩ ቁማር ነው።
    “ጥቅምት 12/2012 ማታ አቶ ጃዋር መሃመድ ባስነሳው ሁከትና ብጥብጥ በንፁሃን ዜጎች ላይ ጥቃትና ጉዳት እንዳይደርስ ከመከላከል ይልቅ የጃዋር ጠባቂ ለመሆን በውድቅት ሌሊት መኖሪያ ቤቱ ድረስ የሄዱት ለማና ጠይባ፣ ልክ በድርጅቱ ግምገማ ሲደረግባቸው ከሰባት ወር በፊት የተቀዳን ንግግር ለፅንፈኛ የአማራ አክቲቪስቶች Leak አደረጉ።”
    *** ሽመልስ አብዲሳ ይሁን ዓብይ አህመድ “ጀውር አባ ሜንጫ ወንድማችን አጋራችን፤ መካሪችን ዋ! ተተኪያችን በእሱና በዓይን ቀልድ የለም” ሲሉ ነበር እንጂ ስለወደመ ንብረትም ይሁን ስለተጨፈጨፈው ህዝብና ተዘቅዝቆ ለተገደለው ዜጋ ትንፍሽ አላሉም… እንዲያውም የሀገሪቱ
    ጠ/ሚ መሆኑ የሠራዊቱ አዛዥ መሆኑን ዘንግቶ ወረዳና ቀበሌ አላስተዳድርም እራስህን ጠብቅ ይልሃል!? ጥቃት ከመፈፀሙ ቀድመው ራስመጠበቂያ መሳሪያህን ያስፈቱሃል…መጓጓዣ መኪና ክብሪትና ጋዝ ያቀርባሉ.. ፖሊስና ጸጥታ አስከባሪው የመከላከል ትዕዛዝ አልደረሰንም ሲሉ ቆመው በድሃ ዕንባና ደም ይዝናናሉ! ሲበረታም መሳሪያቸውን ለወንበዴ ያውሳሉ… በዚያው ሹፈት የተበረታታ መንጋ መዝረፍ፡መድፈር፡ ማረድ፡ ማቃጠል፡ የዘርማፅዳቱን ዘመቻ ቀጥሎበታል።
    “ዋሽቶ ማስታረቅ” እንደሚባለው አቶ ሽመልስ የተናገረውን ተናግሮ ድርጅቱና የክልሉ መንግሥትን ከእንዲህ ያለ ፅንፈኛ ቡድን መታደግ በመቻሉ ሊያስመሰግነው ይገባል።በክልሉም ሆነ በሀገር ደረጃ አሸናፊ ሆነው እንዳይወጡ ለማድረግ በሚል ስለሆነ “እሰይ አበጀህ” ብዬዋለሁ”
    ** “ዋሽቶ ነፍስ ማዳን” ሲባል ተሰምቷል! አስታራቂው ውሸታም ከሆነ ምኑን አስታረቀው!? አዋለቀው እንጂ… ዓይኔን ግንባር ያርገው ካልሆነ አሁን ብልፅግና ብልግና ሆኖ ሕዝብ ንብረትና ሀገር ሲፈርስ ፅንፈኛው ቡድን የሚሰራውን እየሰራ ያለውን እና ሊሰራ ያቀደውን ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ የአፓርታይድ ወይም አክራሪ ወራሪ የካድሬ ሥልጠና ላይ የተነገረን እውነትእንጂ ከማንም ጋር የሚነካካ አደለም። ለማስተባበል የተሄደበት መንገድ በራሱ ፅንፈኛና ሽመልስ እንዳለው ” የገባውን አሳምነሀ ያልገባውን አወዛግበህ ትልምህን ማሳካት!” ለምን ተምታታበት (ተወዛገበ) ብለህ አትጠይቅ!።”
    ልክ እንደዚህ ፅሑፍ ግለሰቡ የፖለቲካ ተንታኝ ነውና ያመነውን አሳምን ያልገባውን ግራ አጋባው ትወና ማለት ነው። ከሚያጠፉት ሰዎች ይልቅ ጥፋትን የሚያጣፉት ሰዎች አጭቤ እጅግ አደገኞች ናቸው። አራት ነጥብ። ሰዩመ ብልጥ’ገና !

    Reply
  3. Natnael says

    August 12, 2020 05:08 am at 5:08 am

    እንደ ስዩም ዓይነት አድርባይ ባንዳ በዚህ ምድር አላየሁም። ሽመልስ በአማራ ላይ ሲቀልድ የመጀመርያው አይደለም። መስቀል አደባባይ ላይ የተናገረውን ማስታወስ በቂ አይደለምን? ቆይ እውነትን መደበቅ ይቻላል? ይጠቅማል? እስከመቼ?

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule