• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ይቅርታና ምህረት አድራጊው ይወገዳል! የተደረገለትም ይሞታል!

September 3, 2020 09:50 pm by Editor 4 Comments

መሃል ሰፋሪ አሊያም ገለልተኛ ይመስል የነበረው የኦሮሞ አክቲቪስቶች በሙሉ የጃዋር ግልገል መሆናቸው የምታውቀው፤ ልክ እንደ አይን-አፋር ሴት እየተቅለሰለሱ፣ እንደ ሽምግሌ ምሳሌ እያበዙ ከሄዱ በኋላ በማጠቃለያው ላይ “ጃዋር መሃመድ በይቅርታ ከእስር ቢፈታ ለሀገርና ህዝብ ይጠቅማል!” ሲሉ ነው። በእርግጥ በእስር ላይ ያለ ሰው እንዲፈታ ማሰብ፣ አማላጅ መላክ ወይም Lobby ማድረግ በተለይ እንደ ኢትዮጵያ ባለ ሀገር ውስጥ የተለመደ ነው።

በዚህ ረገድ በሰኔ15ቱ ግድያ ተጠርጥረው የታሰሩ ሰዎች መፈታታቸው በተደጋጋሚ እንደ ማሳያ ተጠቅሷል። ነገር ግን በሰኔ 15ቱ ግድያ የተሳተፉ አካላት በስልጣን ሽኩቻና አለመግባባት ምክንያት የተፈጠረ ነው። በዚህ ምክንያት የተጎዱ ሰዎች መኖራቸው እርግጥ ነው። ነገር ግን በአማራ ክልል የሚገኙ አማራዎችን ወይም ሙስሊሞችን ለማጥፋት ታቅዶ የተፈፀመ አይደለም። በክልሉ ሆነ በፌደራል ደረጃ ስልጣን ለመያዝ ያስችላቸው ዘንድ በአማራ ክልል የሚገኙ ኦሮሞዎችን ግደሉ የሚል የዘር ማጥፋት ጥሪ አላቀረቡም። ከሁሉም በላይ የሚያስተዛዝበው ነገር ጃዋር መሃመድ ጥቅምት 12/2012 በአርሲና ባሌ ተመሣሣይ የሆነ የዘር ዕልቂት እንዲፈፀም ያቀረበውን ጥሪ ተከትሎ 87 ሰዎች በአሰቃቂ ሁኔታ ያስገደለ መሆኑ ነው።

በመሰረቱ እንደ ጃዋር መሃመድ ላለ ሰው፤ መቻቻል ማለት መጃጃል ነው! ትዕግስት ፍርሃት ነው! ጨዋነት ማለት ሞኝነት ነው! ይቅርታ ማለት ሽንፈት ነው! ይህ ግለሰብ ቅንጣት ያህል ሰብዓዊነት እና ማስተዋል ቢኖረው ኖሮ በባዶ ሜዳ ተከበብኩኝ ብሎ የዕልቂት ጥሪ አያቀርብም። እንደው ፍፁም በተለየ ሁኔታ ጥሪውን ቢያቀርብ እንኳን በዚያ ምክንያት ንፁሃን ሰዎች በአሰቃቂ ሁኔታ በመገደላቸው ትንሽ …. በጣም ትንሽ የፀፀት ስሜት ይኖረዋል። በአደባባይ መፀፀቱን ለመግለጽ ቢቸገር እንኳን አመት እንኳን ሳይሞላው ከስምንት ወር በኋላ ሰኔ 22/2012 ላይ በተመሳሳይ ቦታና ህዝብ ላይ ተመሣሣይ የሆነ የዕልቂት ጥሪ በማቅረብ ከባለፈው እጥፍ የሚበልጡ ንፁሃንን በአሰቃቂ ሁኔታ አያስገድልም።

እንዲህ ያለ ሰው ሰብዓዊ ርህራሄ የሚባለው ነገር ከውስጡ አንጠፍጥፎ የጨረሰ፣ በንፁሃን ሞትና ስቃይ ሃሴት የሚያደርግ፣ የዘር ዕልቂት እና ሁከት በማስነሳት የስልጣን ጥማቱን እና የጥቅም ሱሱን የሚያረካ ፍፁም ሰይጣናዊ የሆነ ፍጥረት ነው። ጃዋር መሃመድ ህሊና ቢኖረው ኖሮ ያደረገውን ሁሉ አያደርግም ነበር። መስሎት በስህተት አሊያም በአጉል ድፍረት አድርጎት ቢሆን እንኳን በጥቅምት ወር ላይ ለፈፀመው ግፍና መከራ በህግ አግባብ ተጠያቂ ሳይሆን በመቅረቱ በምድር ላይ እጅግ በጣም ትልቅ የሚባል ይቅርታ ተደርጎለታል። ይሄ ከሌሎች ሀገራት ነባራዊ አንፃር ሲታይ በችሎት ፊት ሞት የተፈረደበትን ወንጀለኛ በተከሳሾቹ ፊት ምህረት የመስጠት ያህል ከባድ ነው።

በመሆኑም ጃዋር በጥቅምት ወር ለፈፀመው ወንጀል ተከስቶ በትንሹ ዕድሜ ይፍታህ ሊፈረድበት ሲገባ ለፍርድ ሳይቀርብ በመቅረቱ በውስጡ ትልቅ ደስታን፣ በተጎጂዎች ዘንድ ትልቅ የሆነ ሰቀቀን ይችላል። በእርግጥ የጃዋርን ጥሪ ተከትሎ ቤተሰቦቻቸው በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደሉባቸው ዜጎች በሀዘን ሰቆቃ ውስጥ እያሉ አቶ ጃዋር ሰኔ 22 ያቀረበውን ጥሪ ተከትሎ ከመጀመሪያው በእጥፍ የሚበልጡ ሰዎች በተመሣሣይ ሁኔታ ተገድለዋል። ይሄ የሚያሳየው አቶ ጃዋር መሃመድ ለሰው ልጅ ህይወት ቅንጣት ያህል ክብርና ዋጋ የማይሰጥ ሰይጣናዊ ፍጡር ከመሆኑ በተጨማሪ ሰብዓዊነትና ማስተዋል የሚባል ነገር ያልፈጠረበት፣ ይቅርታና ምህረት ስለሚባለው ነገር ፈፅሞ ግንዛቤ የሌለው፣ ልክ እንደ ትላንቱ ሰዎችን በአሰቃቂ ሁኔታ እያስገደለ የፈለገውን ነገር ማድረግ እንደሚችል የሚያስብ፣ ከሰውነት ተርታ የወጣ ግዑዝ ፍጥረት ነው።

በአጠቃላይ እንደ ጃዋር መሃመድ ላለ ሰው ይቅርታና ምህረት ማድረግ ማለት በሰብዓዊነት እና ፍትህ ላይ ከማላገጥ የዘለለ ትርጉምና ፋይዳ የለውም። ለዚህ ሰው ይቅርታና ምህረት በማድረግ በሰዎች ህይወት ላይ ቁማር መጫወት የሚሻ የመንግስት አካል ካለ ከተቻለ በምርጫ ካልሆነም በአመፅ ከስልጣን ማስወገድ ትክክል እና አግባብ ነው። ከዚያ በፊት ግን ጥቅምት ላይ ላስገደላቸው 87 ሰዎች ተጠያቂ ባለመሆኑ፣ ለሀገርና ለህዝብ ሲባል በቁጭት፣ በቸልታና በይቅርታ መታለፉን እንደ ዕውቀትና ጀግንነት ቆጥሮ በቀጣዩ ሰኔ ወር በእጥፍ የሚበልጡ ሰዎችን አስገድሎ ሲፎክር የነበረ ወንጀለኛ በምህረት የተለቀቀ ዕለት የሚገባውን ፍርድና ቅጣት በመስጠት ፍትህን ማረጋገጥ ተገቢ ከመሆኑም በላይ የሞራል ግዴታ ነው። ነፃነትና ፍትህ የሚረጋገጠው በመስዋዕት ነው። የተከፈለው መስዕዋትነት ተከፍሎ ነፃነትና ፍትህ ይረጋገጣል እንጂ በንፁሃን ደም በሚቀልድ እብድ ተረግጦ መኖር የሚሻ ሰው የለም!

ስዩም ተሾመ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Middle Column, Opinions Tagged With: jawar, jawar massacre

Reader Interactions

Comments

  1. ነፃ ሕዝብ says

    September 4, 2020 02:10 pm at 2:10 pm

    ስዩም ተሾመ ቃለ ህይወት ያሰማልን ብለናል ፥ ሌላው በትናንትናው ዕለት ስለፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ያቀረብከውም ትንታኔ በእጅጉ ይበል የሚያሰኝ ስለሆነ አንዳንድ ጊዜ ባልተጨበጠና ባልተረጋገጠ ነገር ላይ በስሜት የምትሰጣቸውን ትንታኔዎች አቁመህ በእውነት ላይ ብቻ አስረግጠህ ብትጽፍ መልካም ነው ፥ ለማንኛውም ከዚህ በላይ ላቀረብከው ትንታኔ ከፍ ያለ ምሥጋና ይገባሃል ።

    Reply
  2. Baba says

    September 4, 2020 05:18 pm at 5:18 pm

    Seyoum Teshome is one angry man with misguided political agenda and a slave of his financiers. All he wrote above is baseless and it based on the hate he has for Jawar. Not only that Seyoum suffers from inferiority complex. All that is exhibited in his above writings. Jawar is a prisoner of conscience and the government needs to release him asap.

    Reply
    • HAYMAN says

      September 15, 2020 02:09 pm at 2:09 pm

      Mr baba may the Almigty God give you heart or mind to think for those who has been brutally killed by the words of your god Jawar mohamed justis will prevail for those who suffered and killed becouse of their Religion or Race by the Rasist words of Jawar and his assocites. Mr. Baba come to your sences dont insult peopels if they think otherwise. you will not defit them. Come to your senses.

      Reply
  3. ዘረ-ያዕቖብ says

    September 20, 2020 01:54 pm at 1:54 pm

    Under ዐብይ አህመድ እስካሁን ድረስ ለህዝብ ያሻገረውና የሠጠው ዴሞክራሲ ወይም ሠላም የለም!!! (ዘ ኢኮኖሚስት) – ሚሊዮን ዘአማኑኤል -Zehabesha:

    አቢይ ብቻዉን ስለፈለገ ዴሞክራሲ አይመጣም፣ ግን ከትግራይ በስተቀር አንድ ለኢትዮጵያ እናትና ልጆች የመጣ ጉዳይ ቢኖር፣ እናትና ልጅ በገዛ ቤታቸው ተማምነው እንዲኖሩ የሆነ ይመስላል፣ ማለትም የአቢይ ካድሬ በየቤቱ እየገባ እናትና ልጅን አያናክስም ማለት የሆነ ይመስላል:: ህወሓት ግን ከተወለደበት ከዛሬ 45 ዓመታት ጀምሮ በየቤተሰብ መሃከል እየገባ መናከስንና መጠራጠርን ስላሰፈነ Globally በትግራይ ህብረተሰብ ውስጥ ህብረተሰባዊ የሆነን ኑሮ የሚመራ የለም:: ከዚህም በመነሳት የኢትዮጵያ እናቶች ከልጄ ጋራ በሰላም ተቃቅፌ ለመኖር ያበቃሄኝ አምላክ ተመስገን ማለት ያለባቸውና ከዚያም ቀጥሎ ለሌሎች ተስፋማ ለውጦች ሰላማዊ ትግላቸውን መቀጠል ያለባቸው ይመስለኛል:: Hostage ውስጥ የሚገኙት የትግራይ እናቶች ግን አሁንም፣ ለኔም እንደ ሌሎቹ ኢትዮጵያውያን እናቶች ከልጄ ጋር በሰላምና ካለምንም መሰላለል የምኖርበትን ጊዜ አምጥልኝ ብሎ ከመፀለይ አልፎ አንዳችም መንቀሳቀስ እንኳን ለመሞከር የማይችሉበት ሁናቴ ውስጥ ስለሚገኙ የተሻለ ቀን ብቻ ያምጣ ከማለት ሌላ ምን አለ?
    ከዚያም በላይ ደግሞ ዴሞክራሲ እንዳይመጣ ከሚያውኩት ጉዳዮች አንዳንዶችን ለመጥቀስ ያህል: (ግን ደግሞ ዴሞክራሲ ሲባል ያ ማኒፑላቲቩ ነው ወይስ ሻል ያለ አለ)
    1. ከድሮውኑ የለውጡ አውጠንጣኞች ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲ አስበዉለት ሳይሆን፣ ለውጡን ያቀነባበሩት ቻይናን ከአፍሪቃ ለማባረር ያሉት ዜቤ ነበርና፣ አሁን ችንጉርትን ተክሎ ድንችን ለምን ወደ ገበያ አታቀርቡም እንደመለት ነገርን ቢተውሳ፣
    2. የለውጡ አውጠንጣኞች የለውጡ ሃይሎችን ሲያስተቃቅፉ ከ1965 (ፈረንጅ) እስከ ዛሬይቱ እለት ድረስ በሕረዶ ቕተሎ ባህል ብቻ አድገው ያረጁን ሃይሎችን ሲከቱበት ሌላን በማሰብ እንጂ ዴሞክራሲን በማሰብ አልነበረምና፣ አሁን ከችንኩርት ተከላ እንዴት ተብሎ ነው ድንች ገበየ እንዲቀርብ የሚጠበቀው?
    3. የኖቤል ሽልማቱ ከጉቦነት ጋራ እንጂ ከሌላ ጉዳይ ጋራ የተያያዘ አልነበረምና ስለሱ ማውራቱን ብናቆም የተሻለ ይሆናል፣
    4. አፉን ከፍቶ የመርካቶ ኪስ አውላቂነትን ሲዋደቅ ከስልጣን የተከነበለው TPLF የያልበረደለት አይነት ጎረምሳ በጥባጭነትን በሚጫወትበት አካባቢ ዘንዳ ዴሞክራሲን መርሳትና ለዴሞክራሲ ከምብሓዲሽ ትግል መጀመር ሊያስፈልግ ነው፣
    5. የአምሓራ ሓሳድነትም እኔ ደደብ ነኝና፣ እኔ ካላስተዳደርኳችሁ የሓሳድነት ሚናን ከመጫወት በስተቀር ሌላ ቀና ተግባር አይታየኝም አዲስ አበባም ሰላም አታገኝም፣ ይሄንን እርኩስ ጠባዬን ግን ራሴን አሞኝቼ ሌላውንም አሞኘሁኝ ስል፣ ጭራች የማህተመ ጋንዲ ነው እላችኋለሁኝ ባዮች እስካሉ ጊዜ ድረስ ዴሞክራሲን ለሚቀጥለው 3000 (ሶስት ሺህ) አመታትም ልንረሳው እንችላለን::
    6. የተወሰኑ ኦሮሞ ሃይሎች በአንድ በኩል በብረት ሃገሪቱን ማመስና በሌላ በኩል ደግሞ ዴሞክራሲ ብሎ መጮህ ውጤቱ አሁን ያለውን ሁናቴ አናርኪን እንጂ ሌላን አያስከትልምና እንዴት ነው የአስተሳሰብ ጉዳይ?
    7. እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ራሱን በራሱ ለማስተዳደር እንጂ በየሃያላን መንግስታት ዘንዳ እየተጎነበሰ አንዳችም ነገር የሚጠብቅ ከሆነ መሰረታዊ ለውጥ የሚባል ነገር አይመጣም፣ ለምን ቢባል ሃያላን ሃይሎች ንጥረ ሃብትን እንጂ የሰው ልጅን ወደው አያውቁምና
    8. ለህዝባቸው የሚያስቡ ኢትዮጵያውያን ሃይሎች ምናልባት ካሉ፣ ውድድር ሲካሄድ በውድድሩ ዘንዳ መሸነፍም እንዳለ ግልፅ እንዲሆንላቸው ያስፈልጋል፣ ስለሆነም በስልጣን ላይ እስካሉ ጊዜ ድረስ በህዝባቸው የሚያስመሰግናቸው እንጂ የሚያስነውራቸው ተግባራት ዘንዳ መውደቅ የለባቸውም
    9. በእንዲህ ሲንቀሳቀሱ ከቆዩ በኋላም ስልጣንን በሚለቁበት ጊዜ ካለ ምንም ፍርሃት አገራቸው ውስጥ ሊኖሩ ስለሚችሉ፣ ወይኔ በኋላ ወዴት ልገባ ነው ከሚለው ፍርሃት ጋራ አይነታረኩም፣ እንደ ምሳሌ ወይዘሮ ክሊንተንን እንውሰድ፣ ለነገሩ ወይዘሮ ክሊንተን ኦባማንም ሆነ ትራምፕን ማሸነፍ ይገባት ነበረ፣ ኣይተ ክሊንተም፣ ለባለቤቱ ምርጫ ፉክክር በሚደረግበት ጊዜ ወደ ሃርለም ብቅ ብሎ “ጥቁሩ ፕረዚደንታችሁ እኔ ነኝ እንጂ ኦባማ አይደለም” ያለው ነገር በተወሰነ መልኩ ሃቅነት አለው፣ እስካሁን ጊዜ ድረስ እኔ ካየኋቸው የአሜሪካን ፕረዚደንቶች የተሻለው እሱ ነበርና ነው፣ እና እርሱ ከወረደበት ጊዜና ባለቤቱም ከትሸነፈችበት ጊዜ ድረስ ካለ ምንም ስጋት በገዛ አገራቸው ተዝናንተ ይኖራሉ እንጂ ምን ልሁን ወዴት ልሽሽ ከሚል ጣጣ ጋር አይናቆቱም፣ የኛዎቹም ጠቅላላ ሂይወታችሁን አገራችው ውስጥ አዝናንቶ ከሚያኖራችሁ መልካም ተግባራት ላይ ብቻ እንጂ ከሌላ ነገር ጋራ አለመያያዝ፣
    10. የምእራብ ጋዜጠኛ ምን ጊዜም የምእራቡን ፍላጎትን ነውና የሚያስጠብቀው፣ የምእራቡ ፍላጎት ደግሞ ንጥረ ሃብትን መበዝበዝና፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ህዝብ በረሃብ ሲቆላ የምእራቡ ጋዜጠኛ ግን በአመት አስር ጊዜ ቸቸለንና ሆኖሉሉ እየበረረ ፀሃይ መቆላትን ነው ቅድሚያ የሚሰጠው፣
    11. Unity in diversity

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule