• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ብር የመለወጡ ቀጥተኛ ጥቅም

September 17, 2020 04:40 pm by Editor Leave a Comment

ብዙ ሰዎች በተደጋገሚ ብሩ በመለወጡ በቀጥታ ኢኮኖሚው ላይ የሚመጣውን ጥቅም ንገረን ብለው ጠይቀውኛል! ብር በመለወጡ የሚገኙት የአጭር ግዜ እና የረጅም ግዜ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታዎች የሚከተሉት ናቸው!

የአጭር ግዜ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታዎች፡- በሀገራችን ከ113ቢሊዮን ብር በላይ ጥሬ ገንዘብ ከፋይናንስ ገበያው ቁጥጥር ውጪ አለ! ስለዚህ የገንዘብ ለውጡ ይህንን ገንዘብ ወደ ብሄራዊ ባንክ የመለወጥ እድል ይፈጥራል!

ለምሳሌ፡- ምንጩ ያልታወቀ በመሆኑ ወደ ባንክ ሳይመጣ ከሚበላሸው፤ ከሀገር ውጪ በጎረቤት ሀገር በመሸሹ ከማይመለሰው፤ የመቀየሪያ ወቅቱ ከሚያልፍበት፤ በጎርፍ፤ በቃጠሎ፤ ወዘተ ከወደመው ውጪ 100 ቢሊዮን ብር እንኳን ወደ ህጋዊ የባንክ ስርዓት ቢመጣ ከፍተኛ ገንዘብ ከገበያ የመሰብሰብ እድል ስለሚፈጠር የዋጋ ንረት በሚታይ መልኩ የመቀነስ አቅም ይኖረዋል!

ምንጩ ያልታወቀ፤ በሙስና የ ተገኘ፤ ህጋዊ ባልሆነ መንገድ ሲንቀሳቀስ የነበረ ከፍተኛ ገንዘብ በገበያ በድርጅቶች እና በሰዎች እጅ እንደሚገኝ ይታወቃል! ስለዚህ የተቀመጠውን የጥሬ ገንዘብ ገደብ (1.5 ሚሊዮን ብር ለማለት ነው!) እና ከ5 ሺህ ብር በላይ በባለቤቶች እንዲቀመጥ የሚያዘውን መመሪያ ተከትሎ ህገወጦችን ለመለየት እድል ይፈጥራል፡፡

ለምሳሌ፡- በህገወጥ መንገድ ሃብት ያከማቸ ሰው ወይም ድርጅት ህጋዊ ከሆኑት ሰዎች ተገቢ ያልሆነ Advantage እንደወሰደ ግልጽ ነው! ስለዚህ የብሩ መቀየር የተለየ እድል ያገኙ ሰዎችን በተወሰነ መልኩ ለመቆጣጠር ያሰችላል፡፡

የረጅም ግዜ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታዎች፡- ኢትዮጲያ ውስጥ በባንክ ቤቶ ች ያለው የቁጠባ መጠን ማነስ እና ባንኮች ለባለሃብቶች የሚያቀርቡት የብድር መጠን ማነስ የታወቀ ጉዳይ ነው! ስለዚህ ለምሳሌ 100 ቢሊዮኑ ቢሰበሰብ እና የጥሬ ገንዘብ ዝውውር ገደቡን ተከትሎ 80 ቢሊዮኑ በባንኮች ቢቀመጥ ተጨማሪ ቁጠባ እና ተጨማሪ የብድር አቅርቦት እንዲገኝ ያደርጋል፡፡

ለምሳሌ፡- መንግስት ባወጣዊ አዲስ መመሪያ መሰረት የግል ባንኮች የመንግስትን የግምጃ ቤት ሰነድ የመግዛት እድል ተፈጥሮላቸዋል! ስለዚህ መንግስት ወደ ፊት ለሚያስበው የበጀት ጉድለትን በሀገር ውስጥ የመሙላት ፍላጎት ተጨማሪ የገንዘብ ምንጭ ሆኖ ሊያገለግለው ይችላል፡፡

ገንዘቦች በመሰብሰባቸው እና በግል ባን ኮች ውስጥ በመቀመጣቸው የሚቀርበው ብድር የግል ሴክተሩን በማነቃቃት ተጨማሪ ምርት እንዲመረት፤ ተጨማሪ ሰራተኛ እንዲቀጠር፤ ወደ ውጪ የሚላኩ ምርቶች አድገው የውጪ ምንዛሬ ግኝት እንዲያድግ፤ የሀገር ውስጥ አምራቾች ተበረታተው ከውጪ የሚገቡትን የመተካት አቅም የሚፈጥሩ ከሆነ የውጪ ምንዛሬ እንዲቆጠብ፤ ወዘተ የማድረግ አቅም ይኖረዋል፡፡

ነገር ግን ብር መለወጡ ብቻውን ስር ነቀል ኢኮኖሚያዊ ለውጥ ያመጣል ማለት አይደለም! ምክንያቱም ዋጋ ንረት፤ ስራ አጥነት፤ የውጪ ምንዛሬ ክምችት ማነስ፤ የበጀት ጉድለት፤ ዝቅተኛ ምርት እና ምርታማነት መኖር፤ የንግድ ሚዛን መዛባት፤ ወዘተ በገንዘብ ምክንያት ብቻ የመጡም አይደሉም በገንዘብ ምክንያት ብቻም የሚፈቱ አይደሉም! ሌሎች ፖሊሲዎች እና ስራዎች በተጨማሪነት መሰራታቸው ግድ ነው።

©The Ethiopian Economist View

Filed Under: Opinions, Right Column Tagged With: new birr notes

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule