• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የተሸጠውን ግድብ ዐብይ ገዛው‼

July 24, 2020 02:20 am by Editor Leave a Comment

ታታሪው ሰው ነገሮች ሁሉ ከተጠናቀቁ በኋላ መግለጫ ሰጠ። መግለጫ እንዲህ በረከሰበት ዘመን እሱ ገላለጠው!!

“የግድቡ የመጀመሪያ ምዕራፍ ሙሌት ተጠናቅቋል። እንኳን ደስ ያለን” አለ።

እኔ ግን ከፋኝ!! ቅር አለኝ! ደነገጥኩ!! “ግድቡን የሸጠው ጠቅላይ ሚኒስትር” የሚለው ትንታኔ ተናነቀኝ። ተጽፎ፣ ተነብቦ፣ ተቀርጾ፣ ተቀናብሮ፣ ስምና ባለቤት ኖሮት ለአለም የቀረበው ትንተና ትዝ አለኝ። ዕውቀት ቀፈፈሽ።

ስዩም መስፍን ያለቀሰለት ግድብ ትዝ አለኝ። ጌታቸው ረዳ ሲሸጥ ያየው ግድብ ትዝ አለኝ። አሜሪካና አለም ባንክ፤ ግብጽና ጂዳ ተጠቃቅሰው የገዙት ግድብ ትዝ አለኝ። ተደራዳሪዎቹ እየቆራረሱ የቸበቸቡት ግድብ ትዝ አለኝ። ያለ ልምድ፣ ያለ እውቀት እና ያለሀገር ፍቅር የተመራው የድርድር ቡድን አይኔ ላይ ድቅን አለብኝ!!

ይሄ ሁሉ የክስ ናዳ፤ ይሄ ሁሉ የትንተና ካብ ስድስት ወር አልሞላውም። በጥናት ስምም አዳራሽ ሙሉ ሰው ሰብስበው መሸጡን ነገሩን። ፈጠራቸው ግቡን አልመታ ቢል፣ ይህንን አይቶ ዝም አለ የተባለው የኢትዮጵያ ህዝብም ተዘለፈ። በነሱ ዘንድ፣ ሀሜትን አለማስተጋባትም ያስወቅሳል።

ኧረ ከቀናት በፊትና በሰኔ ወር መጨረሻም ይህንኑ ደጋግመው ሲነግሩን ነበር። ግድቡን እየጨረሰው ነው ሳይሆን እያበላሸው ነው፤ እየገዛ ነው ሳይሆን እየሸጠ ነው አሉን። ህዝብን በሀሜት ለማነሳሳትም ሞከሩ።

አየህ ወገኔ!

የዘንድሮ ፖለቲካ ዋጋዋ ይህቺ ናት። የዘንድሮ ክስ እንዲህ ጋሽባለች። የዘንድሮ ተንታኝ ይህቺ ናት ምጥቀቷ። የሴራ ቁመት ከመሬትም አጥሯል። ውርደት ራሱ ተዋርዷል። ሀሜት ጥንቡን ጥሏል። አናሊሲስ ኦናሊሲስ ሆኗል። ፖለቲካ አርጅቶ የሕወሓት መጫዎቻ ሆነ።

ምንድን ጉድ ነን ግን?

መገንባቱ ባይሆንልን በትክክል ማፍረስ እንደምን ተሳነን? ምስጋናው ቢያጥረን እንደምን በወጉ መሳደብ አቃተን? መልሱ ሰውዬው ጋ ብቻ ነው ያለው።

“ዝም ብለህ ስራ” ይልሃል። ሰውዬው ሲሰራ ብቻ ሳይሆን፣ ከጨረሰ በኋላም አይፎክርም። ሌላ ብዙ የሚጨርሳቸውን ስራዎች እያማተረ ይጓዛል። መጨረስ እንጂ ማስጨፈር አይወዱም።

“እያዳሜ ድጥ ድጡን እየመረጠ ሲረግጥ እየተከተልክ አትፍረጥ” ይልሃል። እንዲህ ያለ ነበር የዛሬው መግለጫ። ከሳሾቹን መደበቂያ ነፈጋቸው። በያደፈጡበት ደመደማቸው። የትም ያልዋለ ገበያ አስተዋወቀን።

የሸጠው ገዥ ሆኖ መጣ። ሻጩ ገዝቶ መጣ። ከገዙስ አይቀር እንዲህ ነው። ድሮም በሽታቸው መግዛቱ ነበር። ድርብርብ ሞት ይሉሃል ይሄ ነው። ካተረፉስ አይቀር እንዲህ ነው።

አዲስ የግንባታ ጥበብ ታየ። ናደው ሲሉት ካበው። ‘የዐብይ አህመድ ተች’ በለው ይሄንን የግንባታ ጥበብ። አየህ! ባህሩ ሞልቷልና የሁለቱ መርከቦች መዳረሻ ታወቀ። ባለቀዳዳው ሰጥሟል፤ ሽንቁር የለሹ በኩራት እየቀዘፈ ነው።

ያቺ ሴራና ተንኮል፤ አላዋቂነትና ድርቅና የበሳሳት መርከብ ሰጠመች። ሸክሟ ይዟት ዘቀጠ። ደንዳናይቱ፤ ብረት ለበሱዋ አንጥራ መላሿ ግን በኩራት እየቀዘፈች ነው።

ሰላም፣ ትህትና እና ብልጽግናን የሸከፈችው መርከብ ግን በድል እየተንሳፈፈች ነው። ሁሉም የሸክሙ እኩያ ነው።

ዐቢይ አህመድ ዐሊ!

እንዳንተ የተዋጋ ማን ይሆን? ስንቱን ልፍስፍስ አለፍከው? ብርቱ ገጥሞ መውደቅ እኮ በስንት ጣእሙ! እንዲህ እየተጎተትክ፤ በዚህ ሁሉ የገልቱ ልፊያ ውስጥ እዚህ ጋ መድረስ ከጥንካሬ ያይላል!!

ስንቱ ሊያወርድህ ወረደ? አንተ ግን አልክ:- “የግድቡ የመጀመሪያው ምእራፍ ሙሌት ተጠናቅቆል” ብለህ እንደዋዛ አበሰርከን።

ራማፎሳ ሳቅ ካልገደለው ይገርመኛል! ሙሳ ፋቂ መገረም ካላፈነው ይደንቀኛል። አይኔን ይቅር በለው!! ተገድቦ ሳየው ባህር ያየው መሰለኝ። ወደብ ትዝ አለኝ! ናፍቆት ነው። መበደል አይጣልህ! ማጣት ክፉ ነው። ውቅያኖስ መሰለኝ! የብዙ ሚሊዮኖች እንባ መሰለኝ።

ሀቅ ያኮራኛል! እውነት ያፈካኛል!! ግድቡ መሙላት ጀምሮአል።

አንተ ግን ሞልተህ ተርፈሃል!!

ገስግስ አለቃ! 

__________

እጅግ ደስ ያሰኛል!!

የዘመናዊ እርምጃችን ጉዞ እውን ሆኖ ሲጀመር ማየት፣ የከፍታ ዘመን ጅማሮ ከትርክት ወደ እውን ሲተረጎም በእውን ለማየት መታደል፣ የራስን ሀያል አድዋ ሰርቶ ማሳየት፣ … በብዙ ምክንያት ለዚህ ቀን መብቃት የእውነት ደስስስ ያሰኛል። ለኔና ለትውልዴ ይህ የሁልጊዜ ሰበር ድላችን ነው። በወገኔና ሀገሬ ላይ የደረሰው እጅግ አሳፋሪና አስደንጋጭ ክስተት የሰበረውን አንገት፣ እንዲህ ካለው ግዙፍ ድል ውጪ ምን ቀና ማድረግ ይቻለው ነበር?

ክብር ለእናንተ…

ሀሩሩና አረሩ፣ ሽብሩና ሁከቱ፣ ዲፕሎማሲውና ጫናው፣ ዛቻና ፉከራው፣ … ሳይገታችሁ የትውልዳችንን አድዋ እውን ላደረጋችሁ ሁሉ ይሁን!!

ያዝ! ቢቢሲ የማይሰራው ዜና ርእሱ አንዲህ ይላል፤

“ከሳምንታት በፊት ትፈርሳለች፤ ትበታተናለች የተባለችውን ሀገር የሚመሩት ጠቅላይ ሚኒስትር፣ የህዳሴ ግድባቸውን የመጀመሪያ ምዕራፍ ሙሌት መጠናቀቅ አብስረዋል!” 

ሀምሌ 15 ቀን 2012 ዓ.ም… ታላቅና ታሪካዊ፣ እንዲሁም ጨዋታና አሰላለፍ ቀያሪው ልዩ ቀን!!

መሐመድ ሐሰን


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Filed Under: Middle Column, Opinions

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule