• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የተሸጠውን ግድብ ዐብይ ገዛው‼

July 24, 2020 02:20 am by Editor Leave a Comment

ታታሪው ሰው ነገሮች ሁሉ ከተጠናቀቁ በኋላ መግለጫ ሰጠ። መግለጫ እንዲህ በረከሰበት ዘመን እሱ ገላለጠው!!

“የግድቡ የመጀመሪያ ምዕራፍ ሙሌት ተጠናቅቋል። እንኳን ደስ ያለን” አለ።

እኔ ግን ከፋኝ!! ቅር አለኝ! ደነገጥኩ!! “ግድቡን የሸጠው ጠቅላይ ሚኒስትር” የሚለው ትንታኔ ተናነቀኝ። ተጽፎ፣ ተነብቦ፣ ተቀርጾ፣ ተቀናብሮ፣ ስምና ባለቤት ኖሮት ለአለም የቀረበው ትንተና ትዝ አለኝ። ዕውቀት ቀፈፈሽ።

ስዩም መስፍን ያለቀሰለት ግድብ ትዝ አለኝ። ጌታቸው ረዳ ሲሸጥ ያየው ግድብ ትዝ አለኝ። አሜሪካና አለም ባንክ፤ ግብጽና ጂዳ ተጠቃቅሰው የገዙት ግድብ ትዝ አለኝ። ተደራዳሪዎቹ እየቆራረሱ የቸበቸቡት ግድብ ትዝ አለኝ። ያለ ልምድ፣ ያለ እውቀት እና ያለሀገር ፍቅር የተመራው የድርድር ቡድን አይኔ ላይ ድቅን አለብኝ!!

ይሄ ሁሉ የክስ ናዳ፤ ይሄ ሁሉ የትንተና ካብ ስድስት ወር አልሞላውም። በጥናት ስምም አዳራሽ ሙሉ ሰው ሰብስበው መሸጡን ነገሩን። ፈጠራቸው ግቡን አልመታ ቢል፣ ይህንን አይቶ ዝም አለ የተባለው የኢትዮጵያ ህዝብም ተዘለፈ። በነሱ ዘንድ፣ ሀሜትን አለማስተጋባትም ያስወቅሳል።

ኧረ ከቀናት በፊትና በሰኔ ወር መጨረሻም ይህንኑ ደጋግመው ሲነግሩን ነበር። ግድቡን እየጨረሰው ነው ሳይሆን እያበላሸው ነው፤ እየገዛ ነው ሳይሆን እየሸጠ ነው አሉን። ህዝብን በሀሜት ለማነሳሳትም ሞከሩ።

አየህ ወገኔ!

የዘንድሮ ፖለቲካ ዋጋዋ ይህቺ ናት። የዘንድሮ ክስ እንዲህ ጋሽባለች። የዘንድሮ ተንታኝ ይህቺ ናት ምጥቀቷ። የሴራ ቁመት ከመሬትም አጥሯል። ውርደት ራሱ ተዋርዷል። ሀሜት ጥንቡን ጥሏል። አናሊሲስ ኦናሊሲስ ሆኗል። ፖለቲካ አርጅቶ የሕወሓት መጫዎቻ ሆነ።

ምንድን ጉድ ነን ግን?

መገንባቱ ባይሆንልን በትክክል ማፍረስ እንደምን ተሳነን? ምስጋናው ቢያጥረን እንደምን በወጉ መሳደብ አቃተን? መልሱ ሰውዬው ጋ ብቻ ነው ያለው።

“ዝም ብለህ ስራ” ይልሃል። ሰውዬው ሲሰራ ብቻ ሳይሆን፣ ከጨረሰ በኋላም አይፎክርም። ሌላ ብዙ የሚጨርሳቸውን ስራዎች እያማተረ ይጓዛል። መጨረስ እንጂ ማስጨፈር አይወዱም።

“እያዳሜ ድጥ ድጡን እየመረጠ ሲረግጥ እየተከተልክ አትፍረጥ” ይልሃል። እንዲህ ያለ ነበር የዛሬው መግለጫ። ከሳሾቹን መደበቂያ ነፈጋቸው። በያደፈጡበት ደመደማቸው። የትም ያልዋለ ገበያ አስተዋወቀን።

የሸጠው ገዥ ሆኖ መጣ። ሻጩ ገዝቶ መጣ። ከገዙስ አይቀር እንዲህ ነው። ድሮም በሽታቸው መግዛቱ ነበር። ድርብርብ ሞት ይሉሃል ይሄ ነው። ካተረፉስ አይቀር እንዲህ ነው።

አዲስ የግንባታ ጥበብ ታየ። ናደው ሲሉት ካበው። ‘የዐብይ አህመድ ተች’ በለው ይሄንን የግንባታ ጥበብ። አየህ! ባህሩ ሞልቷልና የሁለቱ መርከቦች መዳረሻ ታወቀ። ባለቀዳዳው ሰጥሟል፤ ሽንቁር የለሹ በኩራት እየቀዘፈ ነው።

ያቺ ሴራና ተንኮል፤ አላዋቂነትና ድርቅና የበሳሳት መርከብ ሰጠመች። ሸክሟ ይዟት ዘቀጠ። ደንዳናይቱ፤ ብረት ለበሱዋ አንጥራ መላሿ ግን በኩራት እየቀዘፈች ነው።

ሰላም፣ ትህትና እና ብልጽግናን የሸከፈችው መርከብ ግን በድል እየተንሳፈፈች ነው። ሁሉም የሸክሙ እኩያ ነው።

ዐቢይ አህመድ ዐሊ!

እንዳንተ የተዋጋ ማን ይሆን? ስንቱን ልፍስፍስ አለፍከው? ብርቱ ገጥሞ መውደቅ እኮ በስንት ጣእሙ! እንዲህ እየተጎተትክ፤ በዚህ ሁሉ የገልቱ ልፊያ ውስጥ እዚህ ጋ መድረስ ከጥንካሬ ያይላል!!

ስንቱ ሊያወርድህ ወረደ? አንተ ግን አልክ:- “የግድቡ የመጀመሪያው ምእራፍ ሙሌት ተጠናቅቆል” ብለህ እንደዋዛ አበሰርከን።

ራማፎሳ ሳቅ ካልገደለው ይገርመኛል! ሙሳ ፋቂ መገረም ካላፈነው ይደንቀኛል። አይኔን ይቅር በለው!! ተገድቦ ሳየው ባህር ያየው መሰለኝ። ወደብ ትዝ አለኝ! ናፍቆት ነው። መበደል አይጣልህ! ማጣት ክፉ ነው። ውቅያኖስ መሰለኝ! የብዙ ሚሊዮኖች እንባ መሰለኝ።

ሀቅ ያኮራኛል! እውነት ያፈካኛል!! ግድቡ መሙላት ጀምሮአል።

አንተ ግን ሞልተህ ተርፈሃል!!

ገስግስ አለቃ! 

__________

እጅግ ደስ ያሰኛል!!

የዘመናዊ እርምጃችን ጉዞ እውን ሆኖ ሲጀመር ማየት፣ የከፍታ ዘመን ጅማሮ ከትርክት ወደ እውን ሲተረጎም በእውን ለማየት መታደል፣ የራስን ሀያል አድዋ ሰርቶ ማሳየት፣ … በብዙ ምክንያት ለዚህ ቀን መብቃት የእውነት ደስስስ ያሰኛል። ለኔና ለትውልዴ ይህ የሁልጊዜ ሰበር ድላችን ነው። በወገኔና ሀገሬ ላይ የደረሰው እጅግ አሳፋሪና አስደንጋጭ ክስተት የሰበረውን አንገት፣ እንዲህ ካለው ግዙፍ ድል ውጪ ምን ቀና ማድረግ ይቻለው ነበር?

ክብር ለእናንተ…

ሀሩሩና አረሩ፣ ሽብሩና ሁከቱ፣ ዲፕሎማሲውና ጫናው፣ ዛቻና ፉከራው፣ … ሳይገታችሁ የትውልዳችንን አድዋ እውን ላደረጋችሁ ሁሉ ይሁን!!

ያዝ! ቢቢሲ የማይሰራው ዜና ርእሱ አንዲህ ይላል፤

“ከሳምንታት በፊት ትፈርሳለች፤ ትበታተናለች የተባለችውን ሀገር የሚመሩት ጠቅላይ ሚኒስትር፣ የህዳሴ ግድባቸውን የመጀመሪያ ምዕራፍ ሙሌት መጠናቀቅ አብስረዋል!” 

ሀምሌ 15 ቀን 2012 ዓ.ም… ታላቅና ታሪካዊ፣ እንዲሁም ጨዋታና አሰላለፍ ቀያሪው ልዩ ቀን!!

መሐመድ ሐሰን


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, Opinions

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule