የትግራይ ተወላጁ ሰለሞን ዘነበ በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ውስጥ ባለ ውድ ሆቴል ተንደላቆ የሚኖር የህወሃት ቁልፍ ሰው ነው። ቁልፍነቱ የሚመነጨው ደግሞ ጁንታው ስዬ አብርሃ በእናቱ ወገን አጎቱ በመሆኑ ሲሆን ይህ ሰው ለቀድሞዋ የህፃናት ሚኒስትር ፊልሰን እና የሲአይኤ ኬንያ ወኪል ነኝ ባዩ አህመድ ባጄን ጨምሮ ለህወሃት ደጋፊ ሶማሌዎች ገንዘብ በማስተላለፍ በሶማሌ ክልል ሊተገበር ለታቀደው የህወሃት የጥፋት ሴራ መንገድ ጠራጊ ነው። ባለፈው ሳምንት ሃርጌሳ ታይቶ የነበረው ሰለሞን በቆይታው በሶማሌ ክልል ውስጥ የከተማ ውስጥ ሁከት እና ረብሻ እንዲያስነሱ ለተቀጠሩ ወንጀለኞች ገንዘብ እንዳሰራጨ የታወቀ ሲሆን (የገንዘብ ዝውውር የሚያሳይ ሚስጥራዊ መረጃ የደረሰን ሲሆን አስፈላጊ በሆነ ግዜ ይፋ የሚደረግ ይሆናል) ነገር ግን ከተመደበልን ገንዘብ ቀንሶብናል ያሉና በገንዘብ ክፍያ … [Read more...] about ለሶማሊ ክልል በስዬ አብርሃ የታሰበው “ፕሮጀክት X” ምሥጢር ሲገለጥ
tplf
በሱዳን ስደተኛ ካምፕ የነበሩት ሳምሪዎች ለትህነግ ተዋግተዋል
የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽን (ዩኤንኤችሲአር) ከትግራይ ክልል ወጥተው በሱዳን መጠለያ ጣቢያ የነበሩ ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው በጦርነት መሳተፋቸውን ባወጣው መግለጫ አመለከተ። ዩኤንኤችሲአር ከትግራይ ክልል ተፈናቅለው በሱዳን መጠለያ ጣቢያ የሚገኙና ድጋፍ የሚደረግላቸውን ስደተኞች የመረጃ ሁኔታን ከልሷል። በዚሁ መሰረት በመጠለያ ጣቢያው ተመዝግበው የነበሩ ስደተኞች ቁጥር ከቅርብ ወራት ወዲህ መቀነሱንና በስደተኛነት ተመዝግበው የነበሩ ሰዎች ወደ ኢትዮጵያ ይመለሱ ወይም የት ይሂዱ የሚያውቀው ነገር እንደሌለ ይፋ አድርጓል። በግጭት ውስጥ የተሳተፈን ሰው በስደተኛነት የማይቀበለው ዩኤንኤችሲአር በስደተኛነት ተመዝግቦ በግጭት ውስጥ የተሳተፈ ማንኛውንም ሰው ዳግም እንደማይቀበል አድርጓል። ከኢትዮጵያ ግጭት ሸሽተው በሱዳን መጠለያ ጣቢያ ውስጥ … [Read more...] about በሱዳን ስደተኛ ካምፕ የነበሩት ሳምሪዎች ለትህነግ ተዋግተዋል
ሽንፋን በአራት አቅጣጫ ከብቦ ጦርነት የከፈተው ትህነግ እርምጃ እየተወሰደበት ነው
ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም አሸባሪው እና ተስፋፊው የትህነግ ቡድን በሀገር መከላከያ ሠራዊት ላይ ጥቃት መሰንዘሩን ተከትሎ በተካሄደው የሕግ ማስከበር እርምጃ የተረፈው የጠላት ጦር የሸሸው ምዕራብ ጎንደርን በሚያዋስነው የሱዳን ጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያዎች ነበር፡፡ ከሕግ ማስከበር እርምጃው በኋላ ላለፉት 10 ወራት በአካባቢው ጥቃት ለመሰንዘር ተደጋጋሚ ሙከራዎችን ቢያደርጉም በስፍራው ባለው የወገን ጦር እየተመታ ተመልሷል፡፡ ዛሬ ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ የጠላት ጦር ሽንፋን በአራት አቅጣጫ በኩል በመክበብ ጦርነት ከፍቶ ነበር ያሉት የምዕራብ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ደሳለኝ ጣሰው በሁሉም ግንባሮች በአካባቢው የጥምር ጦር አባላት ተገቢው እርምጃ ተወስዶበታል ብለዋል፡፡ በጦርነቱ የጠላትን ጦር በማገዝ እና በመምራት የአሸባሪው እና ተስፋፊው የትህነግ ቡድን ሌላኛው ሴል … [Read more...] about ሽንፋን በአራት አቅጣጫ ከብቦ ጦርነት የከፈተው ትህነግ እርምጃ እየተወሰደበት ነው
አሸባሪዎቹ ሸኔ እና ህወሓት መደምሰስ አለባቸው፡- ዶ/ር ዓለሙ
በወሎ ግንባር የተገኙት በሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል አስተባባሪ ሚኒስትር ዶክተር ዓለሙ ስሜ አሸባሪዎቹ ሸኔ እና ህወሓት ለኢትዮጵያ የማይጠቅሙ በመሆናቸው መደምሰስ አለባቸው ብለዋል። የወያኔ እና ሸኔ ጥምረት ለኦሮሞና ለኢትዮጵያ ሕዝብ ያላቸውን ንቀት የሚያሳይ ነው ያሉት ዶ/ር ዓለሙ ስሜ ትህነግም ሸኔን በአንድ ላይ መደምሰስ አለባቸውም ነው ያሉት። የሸኔና የህወሓት ጋብቻ አዲስ ሳይሆን ህወሓት መንግሥት ሆኖም ሳለ ኦሮሞን ለማተራመስ ሲፈልግ ሸኔን ይመሩት እንደነበር ነው ያስታወሱት። አሸባሪው ህወሓት በግንባር ጀግንነት እንደሌለው የገለጹት ዶክተር ዓለሙ ለሚያሠራጨው የሐሰት ፕሮፖጋንዳ ጆሮ ሳይሰጥ ህብረተሰቡ እንዲታገል ጥሪ አቅርበዋል። አሸባሪው ህወሓት ወጣቶችን በሀሽሽ እያደነዘዘ እየላከ መሆኑን የገለጹት ዶ/ር ዓለሙ ስሜ ብዙ የአሸባሪው … [Read more...] about አሸባሪዎቹ ሸኔ እና ህወሓት መደምሰስ አለባቸው፡- ዶ/ር ዓለሙ
“አማራው ጌታቸው ረዳ ትግራይን አይመራም” በረኸኞቹ ትህነጎች
በተከታታይ በቲውተር ገጹ መረጃ የሚያሰራጨው የአሸባሪው ትህነግ አባል ጌታቸው ረዳ ትግራይን እንደማይመራ ክርክር ተነስቷል። የራያ ልጅ የሆነውና ፍጹም የአማራ ደም ያለው ባንዳው ጌታቸው ቀደም ሲል በዩኒቨርስቲ መምህርነቱ ወቅት በረኸኞቹን ትህነጎች “ህግ የማያውቁ፣ ደደቦች፤ ምንም የማይገባቸው፤ መሃይም ደናቁርት” እያለ ክፍል ውስጥ ሲያንኳስስ እንደ ነበር የሚናገሩት ተማሪዎቹ የትህነግ አባል መሆኑ ይፋ ከሆነ ማግስት ጀምሮ ግን ለትህነግ አጎብዳጅና ተገዢ እየሆነ መምጣቱን እነዚሁ ተማሪዎችና በቅርብ የሚውቁት ይመሰክራሉ። “እዳ በዝቶበት መክፈል ሲያቅተው የትህነግ አባል ሆኖ ማገልገል ጀመረ፤ ለፕሮጀክት የተሰጠውን ገንዘብ ሙልጭ አድርጎ በላው፤ ወሰበበት፣ ጠጣበት፤ ትህነጎችም በስልት አበሰበሱት” ሲሉ ጌታቸውን በቅርብ የሚውቁት ይናገራሉ። በቀጣይም “ዕዳ ስረዛ ተደርጎለት … [Read more...] about “አማራው ጌታቸው ረዳ ትግራይን አይመራም” በረኸኞቹ ትህነጎች
“ለዶሮ በሽታ በሬ ማረድ ትክክል አይደለም” ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ
አንዳንዶች ከሁለት አሥርት ዓመታት በላይ በቆዩበት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልነት የመጨረሻ ዘመንና የመጨረሻው ሳምንት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ጋር ሰኔ 28 ቀን 2013. ዓ.ም. በነበራቸው ጥያቄና መልስ፣ በአገሪቱ ታሪክ ከፍተኛ የተባለውን 561 ቢሊዮን ብር የ2014 ዓመታዊ በጀት እንዲሆን የቀረበውን የውሳኔ ሐሳብ በሙሉ ድምፅ በማፅደቅ የመጨረሻ የውሳኔ አሻራቸውን አሳርፈዋል፡፡ በዕለቱ ከፍተኛ የአገሪቱ የመንግሥት ኃላፊዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ የተፎካካሪ ፓርቲ መሪዎች፣ የግሉ ዘርፍ ተወካዮችና ሌሎችም አካላት በተገኙበት በዚሁ የፓርላማው ስድስተኛ ዓመት አራተኛ ልዩ ስብሰባ በወቅታዊ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ያመዘኑ በርከት ያሉ ጥያቄዎች ከ15 የምክር ቤት አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀርበውላቸው ነበር፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ምክር ቤቱን … [Read more...] about “ለዶሮ በሽታ በሬ ማረድ ትክክል አይደለም” ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ
የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!?
ከመግቢያው በፊት ይህንን ዘገባ በቴድሮስ አድሃኖም ላይ የሠራነው ከዓመት በፊት April 12, 2020 ነው። ትህነጉ ቴድሮስ አገራችንን ወክሎ የዓለም ጤና ጥበቃ ሃላፊ መሆን እንደሌለበት ገና ለምርጫ ሲወዳደር ጀምሮ አጥብቀን ተቃውመናል። አሁን ወቅቱ የደረሰ ይመስላል። ጥያቄው እየቀረበ ነው። ቴድሮስ አሸባሪውን ህወሃት እስካሁን እየደገፈ ያለ በመሆኑ ብቻ ከሥልጣኑ መወገድ ብቻ ሳይሆን ለፍርድም መቅረብ ያለበት ነው። ዘገባውን በድጋሚ አትመነዋል። እንደ መግቢያ ሰሞኑንን ከኮቪድ - 19 ጋር ተያይዞ የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር ቴድሮስ አድሓኖም አጣብቂኝ ውስጥ መግባቱ ይታወሳል። ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ካወደመው፣ የዘር ፖለቲካን ከሚያራምደው ፍጹም ጽንፈኛና ዘረኛ፣ እንዲሁም በከፍተኛ ደረጃ ኢትዮጵያውያንን በዘራቸው፣ በፖለቲካ እምነታቸው ካኮላሸ፣ ከጨፈጨፈ፣ ቶርቸር … [Read more...] about የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!?
“ለትግራይ እንደ ጫማ ሶል ሆነን ነው ስናገለግል የነበረው … ለእኛ ይህ አይገባም ነበር” – ብ/ጀነራል ናስር አባ ዲጋ
የክፋት አለቃው ህወሀት መራሹ ወንበዴ ቡድን በክፋት ሰይፉ ጉዳት ካደረሰባቸው የሰራዊት ክፍሎች መካከል ብ/ጀነራል ናስር አባዲጋ የሚመሩት የ8ኛ ሜካናይዝድ ክ/ጦር ይገኝበታል። ሜካናይዝድ ክፍለ ጦሩ የደረሰበትን የክፋት ጥቃት ተቋቁሞ ሃይሉንና ትጥቁን በመያዝ እየተዋጋ ወደ ጎረቤት ሃገር ኤርትራ ከተሻገረ በኋላ እንደገና ሃይሉንና ትጥቁን አቀናጅቶ እየተዋጋ የገባ ክፍለ ጦር ነው። እስከ ሽራሮ እየተዋጋ መጥቶም፣ ከሰሜን ምዕራብ ግንባር ዳንሻ ጀምሮ እየተዋጋ ከመጣው ምዕራብ ዕዝ ጋር በመቀናጀት እስከ መቀሌ ከዛም ጁንታው ተበጣጥሶ በረሃ እስከገባበት ጊዜ ድረስ በውጤት እርቀቱ ሆኖ ከባድ ምት በማሳረፍ የነበረው ሚና በቃላት ከሚገለፀው በላይ ነው። መቀሌን እንደተቆጣጠርን የሜካናይዝድ አዛዡን ብ/ጀነራል ናስር አባዲጋን አግኝቼ ስለ ጥቃቱ አናግሪያቸው ነበር። እሳቸውም … [Read more...] about “ለትግራይ እንደ ጫማ ሶል ሆነን ነው ስናገለግል የነበረው … ለእኛ ይህ አይገባም ነበር” – ብ/ጀነራል ናስር አባ ዲጋ
የመለስ ዜናዊ አካዳሚ ለ21ኛው ክፍለዘመን የማይመጥን ስም በመሆኑ ተቀየረ
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ "የመለስ ዜናዊ የአመራር አካዳሚ" "የአፍሪካ የአመራር ልህቀት ማዕከል" (‘African Leadership Excellence Academy’) በሚል መቀየሩን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው አስታውቀዋል። አካዳሚው ከስም ለውጥ ጋር የ21 ኛው ክፍለዘመን የአመራር ጥያቄዎችን ለማሟላት የሚያስችል ዐቅም ያላቸውን ልሂቃን የሚያፈራ እና የዕድገት ተኮር አስተሳሰብን የሚያንፀባርቅ የትምህርት ተቋም እንዲሆን ያለመ ነው ብለዋል። ሌሎችም ከአሸባሪው ህወሃት ጋር የተቆራኙ ስሞችና መጠሪያዎች እንዲሁ እንዲቀየሩ አስተያየት ሰጪዎች ተናግረዋል። ከዚህ በፊት አካዳሚውን እንዲመሩ የተሾሙት ዮሐንስ ቧያለው የአካዳሚው ስም በመጸየፍ አልመራም ማለታቸው ይታወሳል። ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about የመለስ ዜናዊ አካዳሚ ለ21ኛው ክፍለዘመን የማይመጥን ስም በመሆኑ ተቀየረ
“በተለምዶ ‘ሸኔ’ የሚባለው ራሱን ‘የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት’ ብሎ የሚጠራው ቡድን ነው”
በርካቶች 'ሸኔ' እያለ እራሱን የሚጠራ ድርጅት በሌለበት እንዴት አሸባሪ ተብሎ ይሰየማል ሲሉ ይጠይቃሉ። ይህ ስያሜ አንዳች ነገር ለመሸፈን ተፈልጎ ነው በሚል ጥርጣሬያቸውን የሚገልፁ ምሁራንም አልጠፉም። ለመሆኑ 'ሸኔ' ማነው? በዚህ ጉዳይ ላይ በዛሬው ዕለት የተጠየቁት የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ዶ/ር ጌድዮን ጢሞቲዮስ ተከታዩን ማብራሪያ ሰጥተዋል፦"በተለምዶ 'ሸኔ' የሚባለው እራሱን ደግሞ 'የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት' ብሎ የሚጠራው ቡድን ነው። በምዕራብ ኦሮሚያ፣ በሌሎችም ክልሎች እየተንቀሳቀሰ ጥቃት የሚያደርስ ድርጅት ነው። እራሱ ለእራሱ የሰጠውን ስያሜ ግን እኛ የምናፀድቅበት ምክንያት የለንም፤ ተገቢም አይሆንም ብለን እናምናለን። ይህ ቡድን ከዚህ በፊት እንደ 'ህወሓት' ተመዝግቦ፣ ህጋዊ እውቅና፣ ህጋዊ ሰውነት እና ሰርተፊኬት ኖሮት የሚያውቅ አይደለም፤ … [Read more...] about “በተለምዶ ‘ሸኔ’ የሚባለው ራሱን ‘የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት’ ብሎ የሚጠራው ቡድን ነው”