የክፋት አለቃው ህወሀት መራሹ ወንበዴ ቡድን በክፋት ሰይፉ ጉዳት ካደረሰባቸው የሰራዊት ክፍሎች መካከል ብ/ጀነራል ናስር አባዲጋ የሚመሩት የ8ኛ ሜካናይዝድ ክ/ጦር ይገኝበታል። ሜካናይዝድ ክፍለ ጦሩ የደረሰበትን የክፋት ጥቃት ተቋቁሞ ሃይሉንና ትጥቁን በመያዝ እየተዋጋ ወደ ጎረቤት ሃገር ኤርትራ ከተሻገረ በኋላ እንደገና ሃይሉንና ትጥቁን አቀናጅቶ እየተዋጋ የገባ ክፍለ ጦር ነው። እስከ ሽራሮ እየተዋጋ መጥቶም፣ ከሰሜን ምዕራብ ግንባር ዳንሻ ጀምሮ እየተዋጋ ከመጣው ምዕራብ ዕዝ ጋር በመቀናጀት እስከ መቀሌ ከዛም ጁንታው ተበጣጥሶ በረሃ እስከገባበት ጊዜ ድረስ በውጤት እርቀቱ ሆኖ ከባድ ምት በማሳረፍ የነበረው ሚና በቃላት ከሚገለፀው በላይ ነው። መቀሌን እንደተቆጣጠርን የሜካናይዝድ አዛዡን ብ/ጀነራል ናስር አባዲጋን አግኝቼ ስለ ጥቃቱ አናግሪያቸው ነበር። እሳቸውም … [Read more...] about “ለትግራይ እንደ ጫማ ሶል ሆነን ነው ስናገለግል የነበረው … ለእኛ ይህ አይገባም ነበር” – ብ/ጀነራል ናስር አባ ዲጋ
tplf
የመለስ ዜናዊ አካዳሚ ለ21ኛው ክፍለዘመን የማይመጥን ስም በመሆኑ ተቀየረ
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ "የመለስ ዜናዊ የአመራር አካዳሚ" "የአፍሪካ የአመራር ልህቀት ማዕከል" (‘African Leadership Excellence Academy’) በሚል መቀየሩን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው አስታውቀዋል። አካዳሚው ከስም ለውጥ ጋር የ21 ኛው ክፍለዘመን የአመራር ጥያቄዎችን ለማሟላት የሚያስችል ዐቅም ያላቸውን ልሂቃን የሚያፈራ እና የዕድገት ተኮር አስተሳሰብን የሚያንፀባርቅ የትምህርት ተቋም እንዲሆን ያለመ ነው ብለዋል። ሌሎችም ከአሸባሪው ህወሃት ጋር የተቆራኙ ስሞችና መጠሪያዎች እንዲሁ እንዲቀየሩ አስተያየት ሰጪዎች ተናግረዋል። ከዚህ በፊት አካዳሚውን እንዲመሩ የተሾሙት ዮሐንስ ቧያለው የአካዳሚው ስም በመጸየፍ አልመራም ማለታቸው ይታወሳል። ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about የመለስ ዜናዊ አካዳሚ ለ21ኛው ክፍለዘመን የማይመጥን ስም በመሆኑ ተቀየረ
“በተለምዶ ‘ሸኔ’ የሚባለው ራሱን ‘የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት’ ብሎ የሚጠራው ቡድን ነው”
በርካቶች 'ሸኔ' እያለ እራሱን የሚጠራ ድርጅት በሌለበት እንዴት አሸባሪ ተብሎ ይሰየማል ሲሉ ይጠይቃሉ። ይህ ስያሜ አንዳች ነገር ለመሸፈን ተፈልጎ ነው በሚል ጥርጣሬያቸውን የሚገልፁ ምሁራንም አልጠፉም። ለመሆኑ 'ሸኔ' ማነው? በዚህ ጉዳይ ላይ በዛሬው ዕለት የተጠየቁት የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ዶ/ር ጌድዮን ጢሞቲዮስ ተከታዩን ማብራሪያ ሰጥተዋል፦"በተለምዶ 'ሸኔ' የሚባለው እራሱን ደግሞ 'የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት' ብሎ የሚጠራው ቡድን ነው። በምዕራብ ኦሮሚያ፣ በሌሎችም ክልሎች እየተንቀሳቀሰ ጥቃት የሚያደርስ ድርጅት ነው። እራሱ ለእራሱ የሰጠውን ስያሜ ግን እኛ የምናፀድቅበት ምክንያት የለንም፤ ተገቢም አይሆንም ብለን እናምናለን። ይህ ቡድን ከዚህ በፊት እንደ 'ህወሓት' ተመዝግቦ፣ ህጋዊ እውቅና፣ ህጋዊ ሰውነት እና ሰርተፊኬት ኖሮት የሚያውቅ አይደለም፤ … [Read more...] about “በተለምዶ ‘ሸኔ’ የሚባለው ራሱን ‘የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት’ ብሎ የሚጠራው ቡድን ነው”
የስኳር ፋብሪካዎች ተሽጠው ዕዳቸውን እንዲከፍሉ ተወሰነ
በመንግሥት ባለቤትነት ሥር ከሚገኙት 13 ስኳር ፋብሪካዎች ውስጥ አሥሩ ለግል ባለሀብቶች ተሸጠው፣ ከሽያጩ የሚገኘው ገቢ በከፍተኛ የዕዳ አጣብቂኝ ውስጥ ናቸው ተብለው ለተለዩ ሰባት የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ዕዳ ክፍያ ጥቅም ላይ እንዲውል ተወሰነ። ሪፖርተር ያገኘው መንግሥታዊ መረጃ እንደሚያመለክተው ሰባቱ የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ካለባቸው አጠቃላይ ዕዳ ውስጥ፣ አመዛኙ እንደ አዲስ ወደ … [Read more...] about የስኳር ፋብሪካዎች ተሽጠው ዕዳቸውን እንዲከፍሉ ተወሰነ
እነ ስብሃት ነጋ ጥያቄያቸው ውድቅ ሆነ
እነ አቶ ስብሃት ነጋ ጉዳያችን በትግራይ ክልል ፍርድ ቤት ይታይልን ሲሉ አቤቱታ አቅርበው ነበር። ይህን አቤቱታ ያቀረቡት ዛሬ (ማክሰኞ) በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድቤት አራዳ ምድብ ችሎት ነው። በችሎት የተገኙት የጠቅላይ አቃቤ ህግ ቡድን በበኩሉላቸው የፌዴራል መንግስትን ስልጣን ለመጣል በሚል የሽብር አዋጁን በመተላለፍ በመላው ሀገሪቱ የተፈጸመ ወንጀል መሆኑን በመጥቀስ ተጠርጣሪዎቹ መቀሌ ሆነው በሰጡት ትዕዛዝ ባህርዳር እና ጎንደርን በሮኬት ማስደብደባቸው አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል። በተጨማሪም ተከሳሾቹ ስልጣን ተከፋፍለው በተለያዩ ቦታዎች የተፈጸመ ወንጀል ነው ያለው አቃቤ ህግ ዶክተር አዲስ አለም ባሌማ የድርጅቱ ስራ አስፈጻሚ ሆነው አዲስ አባባ ቁጭ ብለው ሲፈጽሙ የነበረው ወንጀል አንድ ቦታ አለመሆኑን ማመላከቻ ነው ብሏል በምላሹ። ይህ … [Read more...] about እነ ስብሃት ነጋ ጥያቄያቸው ውድቅ ሆነ
አሜሪካ በሴናተሯ አማካይነት “ለቅሶ” ደረሰች
የፕሬዚዳንት ባይደን የቅርብ ወዳጅ የሆኑት ሴናተር ክሪስቶፈር ኩንስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን ለማነጋግር አዲስ አበባ መጥተው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንንን አነጋግረዋል። የኋይት ሐውስ የፕሬዚዳንቱ የብሔራዊ ጸጥታ አማካሪ የሆኑት ጄክ ሱለቫን ባወጡት አጭር መግለጫ እንዳሰፈሩት በትግራይ አለ በሚባለው የሰብዓዊ መብት ገረጣና ሰብዓዊ ቀውስ ባይደን ያላቸውን ትልቅ ጭንቀት ሴናተር ኩንስ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እንደሚያቀርቡ ነበር የጠቆሙት። በተጨማሪም ሁኔታው የአፍሪካ ቀንድን አለመረጋጋት ውስጥ ሊከተው የሚችል በመሆኑ ሴናተሩ ከአፍሪካ ኅብረት ጋር እንደሚመክሩበት አማካሪ በመግለጫቸው አመልክተው እንደነበር ይታወሳል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ በተገኙበት አቶ ደመቀ ተቀብለው አስፈላጊው ማብራሪያ እንደተሰጣቸው የውጭ ጉዳይ … [Read more...] about አሜሪካ በሴናተሯ አማካይነት “ለቅሶ” ደረሰች
ኤርሚያስ ለገሰ “የወያኔ የፕሮፖጋንዳ ሰራተኛ እያለ የለመደው የቁጥር ጫወታ አለቀቀውም”
የቀድሞው ኢህአዴግ ካድሬዎች እና የህወሓት ጀነራሎች ሂሳብ አስተማሪው ኤርሚያስ ለገሰ ሆን ብሎ በቁጥር ሊጫወት ሞክሯል፡፡ አላማው ኢዜማ የክልል ምክር ቤት ወንበሮችን ሊያሸንፍ እንደማይችል አስመስሎ መሳል ነው፡፡ ድመት መንኩሳ አመሏን አትረሳ ሆኖበት ነው፡፡ ኤርምያስ ሹመት አስቦ የለውጡ ደጋፊ የነበረ ጊዜ የተናገረው የወያኔ የፕሮፖጋንዳ ሰራተኛ እያለ የለመደው የቁጥር ጫወታ አለቀቀውም፡፡ ምናልባት እንዲገባው ከዚህ በፊት ከነበረው የተቃዋሚዎች ዕጩዎች ቁጥር በ11% እድገት አሳይተናል እንበለው ይሆን?? ምንም እንኳን [ለእንደዚ አይነቱ አውቆ አበድ መፍትሄው] ንቆ መተው ቢሆንም ያቀረበውን የተንኮል መረጃ እንደ እውነት ሊወስዱ የሚችሉ ቅኖችን ከስህተት ለማዳን ዝርዝር መረጃውን ከዚህ በታች አቅርቤዋለሁ፡፡ ምርጫ የሚደረገው በዘጠኝ ክልሎች እና በሁለት ከተማ አስተዳደሮች … [Read more...] about ኤርሚያስ ለገሰ “የወያኔ የፕሮፖጋንዳ ሰራተኛ እያለ የለመደው የቁጥር ጫወታ አለቀቀውም”
በማይካድራ የጅምላ መቃብር ተገኘ፤ በህወሓት የተገደሉት ቁጥር ከ1300 እንደሚበልጥ ተነገረ
የማይካድራ ከተማ ከንቲባን አቶ ቸሩ ሀጎስ የቀበሌ 01 ሊቀመንበር አብሪሁ ፋንታሁን እና የከተማዋን ነዋሪዎች ጠቅሶ ጌቲ ኢሜጅስ በምስል አስደግፎ ባሰራጨው መረጃ ላይ እንደተገለጸው፤ እአአ ማርች 5/2020 በአቡነ አረጋዊ ቤተክርስቲያን የጅምላ ቃብ ውስጥ ከ1300 በላይ የአማራ ብሄር ተወላጅ የሆኑ ሰዎች አስከሬን ተገኝቷል። የአማራ ብሄር ተወላጅ የሆኑት እነዚሁ ሟቾች ህወሓት ሳምሪ በሚል ባደራጃቸው ወጣቶች፣ ሚሊሻዎች እና በፖሊሶቹ አማካኝነት የተገደሉ መሆኑን ታዋቂው ዓለምአቀፍ ሚዲያ ጌቲ ኢሜጅስ በዘገባው ጠቅሷል። ሟቾቹ በአከባቢው ላሉ ባለሀብቶች በጉልበት ስራ ተቀጥረው የሚሰሩ ንጹሀን መሆናቸውን ያስታወሰው ዘገባው፤ ገዳዮቹ ቤት ለቤት እየሄዱ የአማራ ብሄር ተወላጆችን እየመረጡ ጭፍጨፋውን መፈጸማቸውን ገልጿል። አብዛኛዎቹ ሟቾች በስለታማ መሳሪያዎች ተጨፍጭፈው … [Read more...] about በማይካድራ የጅምላ መቃብር ተገኘ፤ በህወሓት የተገደሉት ቁጥር ከ1300 እንደሚበልጥ ተነገረ
“የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ
ጠቅላይ ኤታ ማጆር ሹም ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ ከባላገሩ ቲቪ ጋር ቃለምልልስ አድርገዋል። ስለ ትልውድና አስተዳደጋቸው፣ ቀድሞው ሠራዊት በህወሓት/ትህነግ “ጨፍጫፊ” ስለመባሉ፣ በህወሓት ላይ የተወሰደው ዘመቻና ውጤቱ፣ ስለተያዙት የትህነግ ሹሞች፣ ወዘተ ሰፋ ያለ መግለጫ ሰጥተዋል። ዘመቻው በድል የተጠናቀቀው በሁለት ሳምንት መሆኑን የጠቆሙት ጄኔራሉ የወንበዴዎቹ ለቀማ ብቻ ተጨማሪ ጊዜ የወሰደ መሆኑን ጠቁመዋል። “እኛ የመግደል ሱስ የለብንም” ያሉት ኤታማጆር ሹሙ አብዛኛዎቹ የትህነግ አመራሮች እጃቸውን እንደሰጡ የቀሩትም እንዲሰጡ አሁንም ጥያቄ እናቀርባለን። ካልሆነ ግን የገቡበት ገብተን አንድም ሰው ሳናስቀር ለሕግ እናቀርባቸዋለን - በተለም አመራሩን ብለዋል። ትህነግ አደርገዋለሁ ስለሚለው ቀጣይ የሽምቅ ውጊያ ሲናገሩ፤ “ይሄ ሽምቅ እናደርጋለን ምናምን የሚሉት ጠቅላላ … [Read more...] about “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ
የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ
በቅርቡም በትግራይ ክልል በተካሄደው የሕግ ማስከበር ዘመቻ ላይ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትን የሚዲያ ባለሙያዎች ወደስፍራው በመላክ ትክክኛ መረጃ ወደህዝቡ እንዲደረስ ማድረጉ ይታወቃል። የሚዲያ ባለሙያዎቹ በስፍራው ተገኝተው የሠሯቸውን ዘገባዎችና ያስቀሯቸውን ምስሎች የሚዘክር የፎቶ አውደ ርዕይም ከጥር 22 ጀምሮ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ከፍቶ ለህዝብ በማሳየት ላይ ይገኛል። “ዘመቻ ለፍትህ” በሚል ርዕስ የተዘጋጀውን ይህንን የፎቶ አውደ ርዕይ የኢፌዴሪ የባህር ሃይል ዋና አዛዥና ሬር አድሚራል ክንዱ ገዙ፣ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት የቦርድ ሰብሳቢ አቶ አወሉ አብዲ እና የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ጌትነት ታደሰ በጋራ የከፈቱ ሲሆን፣ በዕለቱ የባህር ሃይል ዋና አዛዥ ሬር አድሚራል ክንዱ ገዙ ያሰሙትን መልዕክት አዲስ ዘመን እንደሚከተለው አጠናቅሮ … [Read more...] about የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ