• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለሶማሊ ክልል በስዬ አብርሃ የታሰበው “ፕሮጀክት X” ምሥጢር ሲገለጥ

February 16, 2022 10:59 am by Editor 1 Comment

የትግራይ ተወላጁ ሰለሞን ዘነበ በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ውስጥ ባለ ውድ ሆቴል ተንደላቆ የሚኖር የህወሃት ቁልፍ ሰው ነው።

ቁልፍነቱ የሚመነጨው ደግሞ ጁንታው ስዬ አብርሃ በእናቱ ወገን አጎቱ በመሆኑ ሲሆን ይህ ሰው ለቀድሞዋ የህፃናት ሚኒስትር ፊልሰን እና የሲአይኤ ኬንያ ወኪል ነኝ ባዩ አህመድ ባጄን ጨምሮ ለህወሃት ደጋፊ ሶማሌዎች ገንዘብ በማስተላለፍ በሶማሌ ክልል ሊተገበር ለታቀደው የህወሃት የጥፋት ሴራ መንገድ ጠራጊ ነው።

ባለፈው ሳምንት ሃርጌሳ ታይቶ የነበረው ሰለሞን በቆይታው በሶማሌ ክልል ውስጥ የከተማ ውስጥ ሁከት እና ረብሻ እንዲያስነሱ ለተቀጠሩ ወንጀለኞች ገንዘብ እንዳሰራጨ የታወቀ ሲሆን (የገንዘብ ዝውውር የሚያሳይ ሚስጥራዊ መረጃ የደረሰን ሲሆን አስፈላጊ በሆነ ግዜ ይፋ የሚደረግ ይሆናል) ነገር ግን ከተመደበልን ገንዘብ ቀንሶብናል ያሉና በገንዘብ ክፍያ ያልተስማሙ ቅሬታ ያላቸው አካላትን መረጃ ተመርኩዞ የኬንያ የደህንነት ምንጮች የገንዘብ ዝውውሩን አላማ ሲያነፈንፉ ስለ አንድ “ፕሮጀክት X” የተሰኘ እቅድ እጃቸው ላይ አንድ መረጃ ገብቷል።

ምሥጢራዊው “ፕሮጀክት X” ምንድነው?

ታማኝ የኬንያ የመረጃ ምንጮቻችን ትላንት ማምሻውን እንዳሳወቁን በህወሃት ቁልፍ ሰዎች መሪነት የተቆመረው እና ኬንያ ላይ ተብላልቶ በስዬ አብርሃ ዘመድ ሰለሞን ታረቀ ፋይናንስ አቅራቢነት በፊልሰን አብዱላሂ፣ መሀመድ ሀሰን (ባጄ) ወደ እንቅስቃሴ የገባው project X (ፕሮጀክት ኤክስ) የተሰኘው እቅድ ተጋልጧል።

ዕቅዱ በተለያዩ ክፍሎች የተቀመጠ ነው ያሉት ኬንያ የደህንነት የመረጃ ምንጮቻችን ከነዚህም መካከል በዋናነት

  1. በፕሮፓጋንዳ ዘርፍ
  • ፓርቲው ውስጥ መከፋፈል መፍጠር ወይም ተፈጥሯል በሚል ውዥንብር መፍጠር፣
  • መፈንቅለ መንግሥት በሚል አለመረጋጋት እንዲኖር ማድረግ፣
  • የኢኮኖሚ ሻጥር በመሥራት ህዝብ እንዲማረር ማድረግ
  • የክልሉን መንግሥት ቅቡልነት (legitimacy) ማሳጣት፣
  • ለድርቁ በቂ ትኩረት አልተሰጠም በሚል ተቃውሞ ማስነሳት
  • የክልሉን ተወላጆች በክልሉ በሚኖሩ የሌላ ብሄር ተወላጆች ላይ እንዲነሱ ማድረግ የሚሉት ይገኙበታል።

2. በተግባር

  • ነዳጅ ከሀገር እንዲወጣ እና እጥረት እንዲፈጠር ማድረግ (ኢኮኖሚ ሻጥር)
  • መሰረታዊ የፍጆታ ፍላጎት ላይ አርቴፊሻል እጥረት መፍጠር፣
  • ሕዝብ ተማርሮ መንግሥት ላይ እንዲነሳ ማድረግና የከተማ ሁከትእና ረብሻ ማስነሳት የመሳሰሉ እና ዝርዝር መረጃዎችን ያካተተ ነው ብለዋል።

3. ግቡም

ኦብነግ እና ሸኔን በመሳሰሉ ሃይሎች አጋዥነት በክልሉ የሃምሌ 28 ዓይነቱን ጭፍጨፋ በማካሄድ ኦሮሚያና ሶማሌ ክልልን የጦርነት አውድማ በማድረግ በሰሜን የሚገኘውን የሀገር መላከያ ሰራዊት ፊቱን ወደ ምስራቅ እንዲያዞር እና በሰሜን የሚገኘው ግንባር እንዲሳሳና ለጥቃት ተጋላጭ እንዲሆን የተቆመረ የወያኔ ሤራ አካል ነው።

4. የመረጃ ምንጮች መረጃ ሲገመግም

  • በከተማዋ እና በክልሉ የተለያዩ አከባቢዎች ብጥብጥና ሁከት ለመታቀዱ ማሳያ የሚሆነው ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር በዋሉ አካላት ቤት የክልሉ ልዩ ሃይል ልብስ በተለያየ ደረጃ ተደብቆ መያዙ እንዲሁም ወደ ከተማዋ በድንበር በኩል አልፈው ሊገቡ የነበሩ የጦር መሳሪያዎች በቀጥታ ለዚሁ አላማ ሊውሉ ዝግጅት እየተደረገ እንደነበር ጠቋሚ ሆነው የተገኙ ሲሆን የታሰበው የክፋት እና ሁከት ሴራ ምን ያህል የተደራጀ እንደሆነ ነው።
  • እያንዳንዷ እንቅስቃሴ ከክልሉ የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ክትትል እየተደረገበት እንደሆነ እና ለዚህ ጉዳይ ያሰማሯቸው አካላትም በፀጥታ አካላት እጅ ሲወድቁ በኬንያ የሚገኙ የቡድኑ አንቀሳቃሾች በተለይም የቀድሞዋ የህፃናት እና ሚኒስትሯ ፊልሰን አብዱላሂ በግልፅ ለክልሉ መንግሥት ህዝቡ እንዳይታዘዝ፣ ግብር እንዳይከፍል ምንም ዓይነት ትብብር እንዳያደርግም በይፋዊ የፌስቡክ ገፅዋ ጥሪ ማቅረቧ ነገሮችን አመላካች ናቸው።

5. መሬት ላይ ያለ እውነታ

  • የሶማሌ ክልል መንግስት እና የፀጥታ አካሉ እያንዳንዷን ነገር በጥንቃቄ እና በተረጋጋ ሁኔታ እየተከታተለ ሲሆን በኢኮኖሚ ሻጥር በተለይም ነዳጅ ከሀገር በህገወጥ መንገድ እንዲወጣ በማድረግ ህዝብ ላይ ያልተገባ ጫና በፈጠሩ እና ተሳታፊ በሆኑ አካላት ላይ ንብረት እስከመውረስ የደረሰ እርምጃ የወሰደ ሲሆን ሁከት እና ረብሻ ለማስነሳት ቅስቀሳ ያደረጉ ሌሎች ተጠርጣሪዎችን እያደነ መሆኑ መግለፁ ይታወሳል።
  • በመሆኑም ህዝቡ በሬ ወለደ ለሚያናፍሱ አካላት ጆሮ ባለመስጠት የወያኔ ተላላኪዎችን እና ተከፋዮቻቸውን በማጥራቱ እርምጃ ላይ የትኛውንም መረጃ ሳይንቅ ለፀጥታ ሃይሉ በማሳወቅ የወያኔን እና የተላላኪዎቿን ሴራ ማክሸፍ፣ ሀገርን በጋራ መጠበቅ፣ ሰላማችንን ከማስጠበቅ ጎን ለጎን በተፈጥሮ አደጋ ለተጎዳው ወገናችን የምናደርገውን ድጋፍ ማጠናከር አለብን መልእክታችን ነው።

በሌላ በኩል እዚህ ምስል ላይ ያሉት ወጣቶች በጠቅላላ የኦብነግ አባል ሲሆኑ ትላንት በደገሃቡር ከተማ ተሰብስቦ በግራ መጋባት ስሜት ውስጥ ሆኖ የብልጽግና አባልን ነን እያሉ መግለጫ ሲስጡ ነበር።

ለአብነት ያክል ማአሊም ቢሊግ ከኦብነግ ጀግኖች አንዱ እና የነጻነት ሰራዊት ውስጥ መንግሥትን በትጥቅ ሲታገሉ ከነበሩት ተጋይ ወታደሮች ታዋቂ ከሆኑ ሰዎች አንዱ ነበር።

መአሊም ቢሊግ በጦርነት ሲዋጉ ተይዘው ጨለማ ክፍል ውስጥ እና እስር ቤት ውስጥ ለረጅም ጊዜ ማሳለፈቸው ከመያዛቸው በፊት በጣም ከታጠቁ ወታደሮች አንዱ እንደሆነም መረጃዎቹ ይገልጻሉ።

ታጋይ ማአሊም ቢሊግ አሁን የብልጽግና የእሪምት ክንፍ ነን በሚሉ የኦብነግ ወጣቶች መካከል ታይቷል።

ይህ ጉዳይ በኬኒያ የመሸገው የሶማሌ ጉዳዮች ኮንግረስ፣ በአብድራህማን ማህዲ የሚመራው ኦብነግ አንጃ፣ በብቃት ማነስ እና በሙስና የተባረሩና ከብልጽግና አባልነት የተሰናበቱ የቀድሞ የክልሉ ባለሥልጣናት ጥምርት የፈጠረው ውዥንብር ሲሆን ዋና አላማው የሶማሌን ክልል የሁከት እና የብጥብጥ ቀጠና የማድረግ ሴራ አንድ አካል መሆነን በቂ ማስረጃ ነው።

በፎቶ ላይ የሚታዩት ወጣቶች ስለ ድርጅታቸው ኦብነግ የት እንደ ወጣና የት እንደገባም አልተናገሩም በምትኩ ብልጽግና ውስጥ ችግር እንደተፈጠር ለማስመስል በክልሉ ሁከት እና ትርምስ ለመፍጠር ራሳቸውን የብልጽግና የእርምት ክንፍ ብሎ ውዥንብር ሲፈጥሩ ታይተዋል።

(Somali Fast Info. ሶማሌ ፈጣን መረጃ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Politics, Slider Tagged With: operation dismantle tplf, Seyee Abraha, somali region, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. gi haile says

    February 16, 2022 04:25 pm at 4:25 pm

    የሕወኣት ሃይል ከሕዝባችን የተዘረውና በብድር ለአገራችን ተሰጥቶ በተዘዋዋሪ ሕወኣት እጅ የገባው ከ30 ቪሊዮን ዶላር የደረሰው የት ከተባለ ፓርቲው ለወኪሎቹ አከፋፍሎ በሌላ ክልሎች ለሽብር፣ለወንጀል ፣ለመከፋፈል ፣ለዘረፋ፣ለማፊያና አሸባሪ ካድሬዎች ምልመላ የተመደበላቸው በውጭ የፀጥታ ተቋም ሰልጥነው በኢትዮጵያ ፌዴራል ሲሰሩ የነበሩ የጌታቸው አሰፋ ምልምል ድብቅ ሰላዮች ገና ከአገሪቱ ተለቅመው ኣላለቁም ማንነታቸውም አይታወቅም። መረጃውን ሁሉ ጌታቸው አሰፋ ስላጠፋ የኣሁኑ መንግስት በስውር የሚሰሩትን የወያኔ ካድሬና ሰላዮች ለማግኘት ከባድ ጥረት ማድረግ ኣለበት። እነዚህ ካድሬዎች የሁሉም ክልል አባላት ሲሆኑ ድብቅ ማሰልጠኛ ተቋሙን ወደ ኋላ ሄዶ መመርመር ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule