ሳይዋጋ የሚያሸንፍ ጠንካራ የመከላከያ ሰራዊት እየገነባን ነው የመከላከያ ሠራዊት ቀንን ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀ "የጥንካሪያችን ምንጭ ሕዝባችን ነው" በሚል መልዕክት የፓናል ውይይት ተካሄደ። በመርሃ ግብሩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የመከላከያ ሚኒስቴር ሚኒስትር አብርሐም በላይ (ዶክተር)፣ አሁን በኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት ግንባታ ከፍተኛ አቅም ተፈጥሯል፤ ከሩቁ የሚፈራ መከላከያ ሠራዊት ፈጥረናል ብለዋል። የኢትዮጵያ ጠላቶች ሳንቆም ሊጥሉን ሞክረዋል፤ አሁን ቆመን ማንም ሊነቀንቀን የማይችልበት ደረጃ ደርሰናል ያሉት ሚኒስትሩ፣ በአሁኑ ጊዜ ሳይዋጋ የሚያሸንፍ ሠራዊት መገንባት መቻሉን አንስተዋል። ኢትዮጵያ የግዛት አንድነቷ በማንም እንደማይሸረፍ በመስዋዕትነት የሚያረጋግጥ ጀግና ወታደር ያላት ሀገር እንደሆነች የገለጹት ሚኒስትሩ፣ ይህን በተግባር እያረጋገጠ … [Read more...] about “ከሩቁ የሚፈራ የመከላከያ ሠራዊት ፈጥረናል”
tplf
ከ፴ ዓመት በኋላ በሰፈሩት ቁና መሰፈር እንደ ትህነግ
አደራውን ለባለ አደራው ሰጥተው የልማት ሥራዎችን እየተዘዋወሩ የሚመለክቱትና የአረንጓዴ ዘመቻ መመሪያ እየሰጡ ያሉ ዐቢይ አሕመድ ከአዲሱ ዓመት ጀምሮ የወትሮ ጭንቀትና ያለመመቸት ስሜት ፊታቸው ላይ አይታይም። በመንግሥት የዘመኑ ዕቅድ ላይም በተያዘው ዓመት አስተማማኝ ሰላም እንደሚሰፍን ተመልክቷል። ዐቢይ አህመድ ለበዓላት ባስተላለፉት መልዕክቶቻቸውና በፕሮጀክት ምረቃ ላይ “አትጠራጠሩ የሰሜኑ ጦርነት ያበቃል” ብለዋል። “አሁን” ሲሉ መረጃ የሰጡ ወገኖች “አሁን የሰኞው ንግግር ልክ እንደ 1991ዓም (እኤአ) ድርድር ዋጋ የለውም። ምክንያቱም የትህነግ አመራሮች ጊዜ የሚፈጁበት አንዳችም የድርድር ቀብድ የላቸውም”። ከዚሁ ጋር ተያይዞ ቴድሮስ አድሃኖም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር ደውሎ መማጸኑ ተሰምቷል። ምላሽም አግኝቷል። ከመቀሌ ውጪ ቀሪዋ ትልቅ ከተማ አዲግራትና አድዋ … [Read more...] about ከ፴ ዓመት በኋላ በሰፈሩት ቁና መሰፈር እንደ ትህነግ
“በመከላከያ ኃይላችን መሥዋዕትነት” የሰላም ንግግሩ ይቀጥላል – የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ቁልፍ የሚባሉ የትግራይ ከተሞችን መቆጣጠሩን ቀጥሏል ሲል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገለጸ። ይህንን ሲያደርግም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በከተሞች ውጊያ ሳይደረግ የህወሓትን ወታደራዊ ዐቅም ለማሽመድመድ የሚያስችል ስልት ተጠቅሟል። የኢትዮጵያ መንግሥት ከሰብአዊ የርዳታ ተቋማት ጋር በመቀናጀት በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች ሰብአዊ ርዳታ እንዲደርስ እየሠራ ይገኛል። የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት በእነዚህ አካባቢዎች አገልግሎት ለመጀመር የሚያስችል ዝግጅት እንዲያፋጥኑ እያደረገ ነው። ከየአካባቢው ማኅበረሰብ ጋር በመነጋገር ሕዝባዊ አስተዳደር የሚቋቋምበትንና ማኅበራዊ አገልግሎቶች የሚጀምሩበትን መንገድ እያመቻቸ ይገኛል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በአፍሪካ ኅብረት በኩል በደቡብ አፍሪካ በሚደረገው የሰላም ንግግር የሚሳተፍ ይሆናል። አጋጣሚውንም … [Read more...] about “በመከላከያ ኃይላችን መሥዋዕትነት” የሰላም ንግግሩ ይቀጥላል – የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ እደራደራለሁ ያለው ትህነግ ውጊያ ከፍቷል
በመግለጫው ትህነግ የሚያዋጣው የብልጽግና መንገድ ነው አለ ለትግራይ ህጻናት ዕልቂት ተጠያቂው ማን ነው? ብልጽግናን እንደማይቀላቀል አስታውቆ ወደ ትግራይ ያፈገፈገው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር (ትህነግ) “በአዲሱ ዓመት ግጭቱን አቁመን ለሰላም ዕድል በመስጠት የሰላም እና ብልጽግና መንገድ እንጀምር” ሲል በይፋ የተናጠል ተኩስ አቁም ማወጁን አስታወቀ። መግለጫውን ተከትሎ “ላለቁት የትግራይ ህጻናት ተጠያቂ ማን ሊሆን ነው? ለዚህ ለዚህ ለምን ውጊያ ውስጥ ገባን?” በሚል ደጋፊዎቹ ንዴት አዘል ጥያቄ እያነሱ ነው። ጦርነቱ ከመጀመሩ በፊት “አፍንጫቸውን ይዘን ቅድመ ሁኔታችንን ተቀብለው ወደ ድርድር እናመጣቸዋለን። ካልሆነም እንወጋቸዋለን” በማለት የወንበዴው ቡድን መሪ ደብረጽዮን መግለጫ ሰጥቶ ነበር። መንግሥት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በየትኛውም ቦታ ለመደራደር ፈቃደኛ … [Read more...] about ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ እደራደራለሁ ያለው ትህነግ ውጊያ ከፍቷል
የአዲስ አበባዎቹ አሸባሪ የትህነግ ወንበዴዎች (“ሰላማዊ ነዋሪዎች”) በቁጥጥር ሥር ዋሉ
ባለፈው ሳምንት ባወጣነው ዘገባ ከአዲስ አበባ ሆነው የትህነግን ሥራ የሚያስፈጽሙ ወንበዴዎች መኖራቸውንና መንግሥት በጉዳዩ ምላሽ እንዲሰጥ ጠቁመን ነበር። በወጣው ዘገባ መሠረት ከአዲስ አበባ ሆነው የት ህነግን ሥራ የሚያስፈጽሙ በተለይም በትዊተር በተለቀቀው መልዕክት 88% የተላከው ከአዲስ አበባ መሆኑን በማስረጃ የተደገፈ መረጃ ነበር የቀረበው። የአዲስ አበባ “ሰላማዊ” ነዋሪዎች – አፍቃሪ ትህነጎች ማንነት በማስረጃ የኢትዮጵያ የጋራ የጸጥታ ግብረኃይል ሲከታተላቸው የነበሩና እጅግ ውስብስብ በሆነና ሕዝብን በሚያሸብር ተግባር ላይ ተሰማርተው የነበሩ 19 የሽብር ቡድን አባላትና የትህነግ አስፈጽሚ ወንበዴዎች በቁጥጥር ሥር ውለዋል። ከፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ያወጣው መግለጫ እንዲህ ይነበባል፤ ጠላቶቻችን አዲስ አበባን የሽብር ማዕከል እናደርጋለን ብለው … [Read more...] about የአዲስ አበባዎቹ አሸባሪ የትህነግ ወንበዴዎች (“ሰላማዊ ነዋሪዎች”) በቁጥጥር ሥር ዋሉ
የህወሓት የሽብር ሰነድ ሲገለጥ…
አሸባሪው ህወሓት ሀገርን የሚያፈርስበትና የኢትዮጵያን ህዝብ በመበቀል ለመከራ የሚዳርግበት አዲስ ሰነድ አዘጋጅቶ ወደ ተግባር ገብቷል። አሁን እያካሄደ ያለው ውጊያም የዚሁ አካል ነው። ፅሁፉ ሰፊ ከመሆኑ የተነሳ በማሳጠርና መታየት ያለባቸው ነጥቦች ብቻ ቀርቧል። ከሰነዱ የተወሰዱ ዋና ወና ሃሳቦች: ስለ ሰላም አማራጮች ያላቸው አቋም:- • የሰላም አማራጭ በሚል ስትራቴጂው፣ በአንድ በኩል ጊዜ ወስዶ ለአጠቃላይ ዘመቻ ለመዘጋጀት በሌላ በኩል ደግሞ ህወሓት ሰላም ፈላጊ አይደለም ብሎ ለዓለም ማህበረሰብ ጥላቻ ለማሰተጋባት እንዲያግዘው በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት የጀመረው አካሄድ በፍፁም የማያዋጣና የትግራይ ህዝብን ጥቅም የማያስከብር መሆኑን ያስቀምጣል። • የውስጥ ትግላችን በማገዝ የሚንቀሳቀሱ እንደ ኦነግ የመሳሰሉ አጋሮቻችን እንዲሁም በተለያዬ የዓለም … [Read more...] about የህወሓት የሽብር ሰነድ ሲገለጥ…
“ውረሩ፣ ያገኛችሁትን ግደሉ እየተባልን ነው የምንመጣው” እጃቸውን የሠጡ የትህነግ ታጣቂዎች
በኢትዮጵያ እና በኢትዮጵያውያን ላይ የተነሳው የሽብር ቡድን በሕዝብ ላይ አያሌ በደሎችን አድርሷል። ከእኩይ ቡድን አቅራቢያ የሚገኙ የአማራና የአፋር ክልል ነዋሪዎች ደግሞ የሽብር ቡድኑ ግፍና ወረራ ገፈት ቀማሾች ናቸው። ለሦስተኛ ጊዜ ጦርነት ያነሳው የትህነግ የሽብር ቡድን የትግራይ ተወላጆችን ከሕፃናት እስከ አዛውንት ድረስ እየመለመለ ለጦርነት እየላካቸው ነው። የሽብር ቡድኑ በአማራና አፋር ክልል በወረራ በያዛቸው አካባቢዎች ንፁሐንን በጅምላ ረሽኗል፣ ሃብትና ንብፈታቸውን ዘረፏል አውድሟል። የሽብር ቡድኑ የሚልካቸው ታጣቂዎች ሀገሩን እየተከላከለ በሚገኘው ጥምር ጦር እየተመቱ ብዙዎች ይረግፋሉ። እድል የቀናቸው እጃቸውን ሰጥተው ሕይወታቸውን ያተርፋሉ። የሽብር ቡድኑ ታጣቂዎች በወልቃት ጠገዴ ሰቲት ሑመራ ዞን ለሚገኘው ጀግናው የሀገር መከላከያ በርካቶች እጃቸውን እየሰጡ … [Read more...] about “ውረሩ፣ ያገኛችሁትን ግደሉ እየተባልን ነው የምንመጣው” እጃቸውን የሠጡ የትህነግ ታጣቂዎች
ምኒልክ የድል መንፈስ!
የዛሬዋ ኢትዮጵያ የፖለቲካ ስበት ማዕከል የሆነው አፄ ምኒልክ ዘመን ተሻጋሪ ውርሶች ለዘመናዊት ኢትዮጵያ ጥሎ አልፏል። ዘመናዊት ኢትዮጵያ ስንል ከጨረቃ የመጣች እያልን ሳይሆን ግዛታዊ ቅርጿ ሲጠብና ሲሰፋ የነበረችው ኢትዮጵያ በአንጻራዊ ዝማኔ መመራት የጀመረችበት አስተዳደራዊ ዘመን መገለጫ ማለታችን ነው። የዛሬዋ ኢትዮጵያ መልከዓ ምድራዊ ቅርጽ ከሞላ ጎደል የአፄው የንግሥና ዘመን ውጤት ናት። ከምንም በላይ የጥቁር ዘር የነጻነት ምልክት የሆነው የአድዋ ድል በምኒልክ መሪነት የመጣ ነው። በርግጥ ድሉ የአባቶቻችን የመደማመጥና የመተባበር ውጤት ነው። ምኒልክን አልባ የአድዋን ድል ማስመዝገብ ይቻል (ይሆን) ነበር ብሎ ማመን ይቻላል። ይሁንና በታሪክ የምናውቀውን የአድዋን ድል ያለ ምኒልክ ማሰብ ክርስትናን ያለክርስቶስ፣ እስልምናን ያለነብዩ መሐመድ እንደማሰብ ያለ ቅዥት ነው። ይህ … [Read more...] about ምኒልክ የድል መንፈስ!
በኢሊባቦር ዞን ለዘረፋ የገባው አሸባሪው ሸኔ በጥምር ፀጥታ ሀይሉ መመታቱ ተገለፀ
በኢሊባቦር ዞን ዳሪሙ ወረዳ ዱጳ ከተማን ለማውደምና ለመዝረፍ አልሞ የመጣው የአሸባሪው ሸኔ ቡድን መመታቱን በስፍራው የሚገኘው የክ/ጦር ዋና አዛዥ ተናገረዋል። የዘራፊው ስብስብ ቡድን ሠላምና ፀጥታ በመንሣት አካባቢውን የሽብር ቀጠና ለማድረግ እና የህብረተሠቡን የተረጋጋ ኑሮ ለማወክ አቅዶ ቢመጣም ከክ/ጦሩ ጋር የተጣመረው የፀጥታ ኃይሉ በከፍተኛ ቁርጠኝነት ሙትና ቁስለኛ በማድረግ አካባቢውን ከስጋት ነፃ ማድረግ መቻሉን ዋና አዛዡ ገልፀዋል። ዋና አዛዡ አክለውም የአካባቢው የፀጥታ ኃይል እና ማህበረሰቡ ያደረገውን ተጋድሎ በማመስገን ለቀጣይም ጠንክረው ለአካባቢያቸው ሠላም ከፀጥታ አካላቱ ጋር ተባብረው እንዲሠሩ መልዕክት አስተላልፈው የአሸባሪውን ሸኔ ስብስብ በገባበት ገብተን ለመደምሰስ ቀን ከሌት እንሠራለን ብለዋል። ክፍለ ጦሩ እግር በእግር ተከታትሎ ከመታው የሸኔ ዘራፊ … [Read more...] about በኢሊባቦር ዞን ለዘረፋ የገባው አሸባሪው ሸኔ በጥምር ፀጥታ ሀይሉ መመታቱ ተገለፀ
አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል
50 ሚሊዮን ሕዝብ የሚኖርበት የአማራ ክልል ዓመታዊ በጀት ሰማኒያ ቢሊዮን ነው በትግራይ ክልል ለአምስት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ሕዝብ ሰብዓዊ ድጋፍ እየተሰጠ መሆኑን የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታወቀ። እስካሁን ወደ ትግራይ የሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦት ይዘው ከሄዱ አንድ ሺህ 626 ከባድ ተሽከርካሪዎች የተመለሱት ተሽከርካሪዎች 596 ብቻ እንደሆኑ አመልክተዋል። ክልሉን የሚያስተዳድረው ትህነግ በበኩሉ የሚገባው እርዳታ ከሚፈለገው አንጻር በቂ እንዳልሆነ ገልጿል። ዕርዳታ ጭነው የሚገቡትን ከባድ ተሽከረካሪዎች ለምን እንደሚያግታቸው ምክንያት አላቀረበም። የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ደበበ ዘውዴን ጠቅሶ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንዳስታወቀው፤ ምግብ፣ ምግብ ነክ ያልሆኑና መድኃኒት እንዲሁም የትራንስፖርትና የጥሬ … [Read more...] about አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል










