• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ምኒልክ የድል መንፈስ!

September 5, 2022 12:02 pm by Editor Leave a Comment

የዛሬዋ ኢትዮጵያ የፖለቲካ ስበት ማዕከል የሆነው አፄ ምኒልክ ዘመን ተሻጋሪ ውርሶች ለዘመናዊት ኢትዮጵያ ጥሎ አልፏል። ዘመናዊት ኢትዮጵያ ስንል ከጨረቃ የመጣች እያልን ሳይሆን ግዛታዊ ቅርጿ ሲጠብና ሲሰፋ የነበረችው ኢትዮጵያ በአንጻራዊ ዝማኔ መመራት የጀመረችበት አስተዳደራዊ ዘመን መገለጫ ማለታችን ነው።

የዛሬዋ ኢትዮጵያ መልከዓ ምድራዊ ቅርጽ ከሞላ ጎደል የአፄው የንግሥና ዘመን ውጤት ናት። ከምንም በላይ የጥቁር ዘር የነጻነት ምልክት የሆነው የአድዋ ድል በምኒልክ መሪነት የመጣ ነው። በርግጥ ድሉ የአባቶቻችን የመደማመጥና የመተባበር ውጤት ነው። ምኒልክን አልባ የአድዋን ድል ማስመዝገብ ይቻል (ይሆን) ነበር ብሎ ማመን ይቻላል። ይሁንና በታሪክ የምናውቀውን የአድዋን ድል ያለ ምኒልክ ማሰብ ክርስትናን ያለክርስቶስ፣ እስልምናን ያለነብዩ መሐመድ እንደማሰብ ያለ ቅዥት ነው።

ይህ የታሪክ ሀቅ የማይዋጥላቸው ዝግና የተመረጠ የታሪክ ግንዛቤ ያላቸው ተገንጣይ ብሔርተኞች እንዳሉ ይታወቃል። አሁንም ቢሆን ማንነትን የታከከ የታሪክ ትርጓሜ እስካልቀረ ድረስ ይህ አይነት ምልከታ መቀጠሉ ጭራሹኑ እየሰፋ መሄዱ አይቀርም። እውነታው ግን ምኒልክ ከኢትዮጵያም አልፎ የመላ የጥቁር ዘር የነጻነት ምልክት መሆኑ ነው። ከምኒልክ ውርስ ጋር አለመታረቅ በበታችነት የሚሰቃይ ትውልድ ከመፍጠር ባለፈ አንዳች አትራፊ ነገር የለውም። እናም ታረቀው ምኒልክን!

ሃሮልድ እንደሚለው፣ የታሪክ አረዳድ ለብሔራዊ መግባባት ወሳኝ ነገር ነው። እንደ ኢትዮጵያ ባለች ጠመዝማዛ የታሪክ ጉዞ ባሳለፈች አገር ብሔራዊ መግባባት የለም ሲባል ዘርፎቹ ብዙ ናቸው። ከዘርፎቹ ውስጥ ግን ታሪክ ቀዳሚው ነው። እኛ ኢትዮጵያዊያን እንደ አገር ከዘመናዊት ኢትዮጵያ ምስረታ፤ አገር የማቀናት ዘመቻዎች ጋር ተያይዞ ከተፈጠሩ ችግሮችና ተንከባላይ የትውልድ ዕዳዎች ታጋች (hostage) ከመሆን ይልቅ መታረቅ አለብን።

ምዕራባዊያን በሥልጣኔ ወደፊት መጓዛቸውን ያላቆሙበት ምስጢር ከታሪካቸው ጋር ስለ ታረቁ ነው። የታሪክ መሰረቶች ላይ የሚቆሙ ልዩነቶችን መሻገሪያው ብቸኛ መፍትሔ ታሪክን ለታሪክ ባለሙያዎች መተው ብቻና ብቻ ነው። ከምኒልክ ጋር የመታረቂያው አንዱ መንገድ ይሄው ነው!

ታሪክን ለታሪክ ባለሙያዎች መተው ከታሪካችን ጋር እንድንታረቅ ድልድይ ይሆነናል። ያኔ የኢትዮጵያ ታሪክ ሁሉንም የባህል ቡድኖች (በሰሜን፣ በደቡብ፣ በምስራቅና በምዕራብ ያሉትን) እንዲያካልል ማድረግ ይቻላል። ታሪካችንም የ“እኛ” እና የ“እነርሱ” በሚል ሳይሆን ዜግነታዊ መሰረት ባለው መልኩ አካቶነት ያለው የጋራ ታሪክ ማንበብ እንችላለን። ይህ መንገድ… በደም የተዋጀው ቆይታችን በእኩልነት ስሜት አንድነታችን በፅኑ መሰረት እንዲቆም ያደርገዋል። ያኔ ኢትዮጵያዊነት የብዙሃኑ ስሜት ይሆናል። በዚህ አግባብ የኢትዮጵያዊነት መገለጫውን ፈልጎ የሚያጣ የፖለቲካም ሆነ የማህበራዊ ኃይል አይኖርም።

ወደ አባ ዳኛው የአመራር ጥበብ ስንመለስ፡- የምኒልክ ድል የእርሱ እና የብርሃናማዋ ንግሥት ብቻ አልነበረም። በምኒልክ የንግስና ዘመን ለተመዘገቡ ዘመን ተሻጋሪ ውርሶች፤ ዋልታና ማገር የነበሩ አባቶችን ውለታ መርሳት የሚቻል አይደለም። ራስ ጎበና ዳጬ፣ ደጃች ባልቻ ሳፎ፣ ፊትአውራሪ ሀብተጊዮርጊስ ዲነግዴ፣ ራስ መኮንን ወ/ሚካኤል ጉዲሳ፣ ራስ ዳርጌ፣ ራስ ወልደገብርኤል፣ ራስ መንገሻ አንቲከም፣ ራስ ሚካኤል (መሐመድ አሊ)… እያልን ከምንዘረዝራቸው ታላላቅ የጦር አበጋዞች ከአማራው፣ ከኦሮሞና ከደቡብ የተውጣጡ የአገር ምስረታው የፊት መስመር ተሳታፊዎች ናቸው።
እንደራስ ጎበና ዳጬ ያለ ጀግና የጦር አበጋዝ ሰባት ግዛቶችን (የደቡብና የምዕራቡን) (ጥንተ-ርስትና ግዛቶቹን) የኢትዮጵያ አካል ማድረግ ችሏል። ዛሬ ላይ “ምኒልክ የእኛ ብቻ ነው” ሊሉ የሚቃጣቸው የታሪክ ኑፋቄ የተጫናቸው ዝንጉዎች የምኒልክ ብርቱ ቀኝ እጅ የነበሩት የጦር አበጋዞች ለኢትዮጵያ የግዛት አንድነት የደከሙትን ድካም፣ የከፈሉትን ዋጋ ከዚህ አንጻር በአደባባይ እየካዱ መሆኑን ይሰመርበት።

ምኒልክ ዘር አይመርጥም፣ ስበቱ ‘ፖወር’ ነው። ከብዙ ማሳያዎች አንድ፡- የራስ ጐበና ዳጬ ልጅ ወዳጆ ጐበና የምኒልኳን ሸዋረገድን አገባ፤ በውጤቱም ወሰንሰገድ የተባለ ልጅ ተወለደ። ይህ ልጅ በአሥራ አራት አመቱ ባይቀጭ የምኒልክ አልጋ ወራሽ ይሆን ነበር። በዚህ አግባብ ምኒልክ ለጐጃም ሰው ሳይሆን ለቱለማ ኦሮሞ ይቀርባል። ከበጌምድር ሰው ይልቅ የሸዋ ኦሮሞ የምኒልክ የመጀመሪያ የንግስና ዘመናት የኃይል ምንጭ ሆኖ አገልግሏል። የመንዝም ሆነ የየጁ ገበሬ ለምኒልክ ገባር ኢትዮጵያዊ ነበሩ። የአድዋ ሰውም ሆነ የወላይታ እኩል የምኒልክ ገባሮች ናቸው። ሌላውም እንደዛው!

በምኒልክ ሃውልት ላይ ተጽፎ የሚነበበው መልዕክተ-ምኒልክ ምን ይላል መሰለህ፦ “ከትልቅ ወይም ከትንሽ ቢሆን መወለድ ሙያ አይደለም ራስን ለታላቅ ታሪክ መውለድ ግን ሙያ ነው”። አየህ ምኒልክ ግዛታዊነትን የሥልጣን መወጣጫ ብቻ ሳይሆን ያደረገው በግዛቲቱ የሚታመኑለትን መሳፍንቶችም ከተለያየ ቋንቋ ተናጋሪነት ማውጣጣት ችሏል። ከጀምሩ በቴዎድሮስ ቤት ታላቅ ራዕይን ወርሷልና በሰከነ አመራሩ ኩምሳ ሞረዳንም ሆነ አባ ጅፋርን በጥበብ ገባሪው ማድረግ ችሏል።

እንደዚያኛው ቴዎድሮስን መንገድ መርቶ እንደሸጠው መካር አልቦ ንጉሥ (አጼ ዮሃንስ) “ሰማይ አምድ የለው፤ እስላም አገር የለው” የሚል አዋጅ አላስነገረም፤ ይልቁንስ በየደረሰበት ስፍራ ሁሉ “ሁሉም ባባቱ ይደር” የሚል አዋጅ ነበር ያስነግር የነበረው። አባ ጅፋር ምኒልክን ያከበረው ለምን ይመስልሃል? ‘እኔን ምሰል’ እንደማይለው ቀድሞውንም አውቆታል-ጅፋር ነፍሴ! እንጅማ ለ“ካፊር” ይገብር ነበር? የማይሆነውን!!

ሲጠቃለል፡- ምኒልክ የዘመኑ መሪ ብቻ ሳይሆን፤ ጥቁር ሰው መሆኑን በተግባር ያስመሰከረ፤ የነጮች ጌታ! የአድማሳዊ ስብዕና ባለቤት ነበር!!
መንጋው ብዙ ብዙ ሲል ወደን አይደለም ዝንተ-ዓለም ምኒልክ የምንለው!

[‘ከአንድ ስኬታማ ወንድ ጀርባ አንዲት ጠንካራ ሴት አለች’ የሚለው አባባል መነሻው ምኒልክ ቤተ-መንግሥት ነው። ያለ እቴጌዋ ፥ ምኒልክ የጥቁር ዘር ብርሃን መሆን ባልቻለ ነበር። ካላመንክ በ Chris Prouty የተፃፈውን “Empress Taytu and Menilk 1883-1910” መጽሃፍ ፈልገህ አንብብ]

ምኒልክ ጥቁር ሰው፤ የነጮች ጌታ!! ምንጭ፡ Gulilat Geletaw

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, Opinions Tagged With: emiye menelik, operation dismantle tplf, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule