• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ምኒልክ የድል መንፈስ!

September 5, 2022 12:02 pm by Editor Leave a Comment

የዛሬዋ ኢትዮጵያ የፖለቲካ ስበት ማዕከል የሆነው አፄ ምኒልክ ዘመን ተሻጋሪ ውርሶች ለዘመናዊት ኢትዮጵያ ጥሎ አልፏል። ዘመናዊት ኢትዮጵያ ስንል ከጨረቃ የመጣች እያልን ሳይሆን ግዛታዊ ቅርጿ ሲጠብና ሲሰፋ የነበረችው ኢትዮጵያ በአንጻራዊ ዝማኔ መመራት የጀመረችበት አስተዳደራዊ ዘመን መገለጫ ማለታችን ነው።

የዛሬዋ ኢትዮጵያ መልከዓ ምድራዊ ቅርጽ ከሞላ ጎደል የአፄው የንግሥና ዘመን ውጤት ናት። ከምንም በላይ የጥቁር ዘር የነጻነት ምልክት የሆነው የአድዋ ድል በምኒልክ መሪነት የመጣ ነው። በርግጥ ድሉ የአባቶቻችን የመደማመጥና የመተባበር ውጤት ነው። ምኒልክን አልባ የአድዋን ድል ማስመዝገብ ይቻል (ይሆን) ነበር ብሎ ማመን ይቻላል። ይሁንና በታሪክ የምናውቀውን የአድዋን ድል ያለ ምኒልክ ማሰብ ክርስትናን ያለክርስቶስ፣ እስልምናን ያለነብዩ መሐመድ እንደማሰብ ያለ ቅዥት ነው።

ይህ የታሪክ ሀቅ የማይዋጥላቸው ዝግና የተመረጠ የታሪክ ግንዛቤ ያላቸው ተገንጣይ ብሔርተኞች እንዳሉ ይታወቃል። አሁንም ቢሆን ማንነትን የታከከ የታሪክ ትርጓሜ እስካልቀረ ድረስ ይህ አይነት ምልከታ መቀጠሉ ጭራሹኑ እየሰፋ መሄዱ አይቀርም። እውነታው ግን ምኒልክ ከኢትዮጵያም አልፎ የመላ የጥቁር ዘር የነጻነት ምልክት መሆኑ ነው። ከምኒልክ ውርስ ጋር አለመታረቅ በበታችነት የሚሰቃይ ትውልድ ከመፍጠር ባለፈ አንዳች አትራፊ ነገር የለውም። እናም ታረቀው ምኒልክን!

ሃሮልድ እንደሚለው፣ የታሪክ አረዳድ ለብሔራዊ መግባባት ወሳኝ ነገር ነው። እንደ ኢትዮጵያ ባለች ጠመዝማዛ የታሪክ ጉዞ ባሳለፈች አገር ብሔራዊ መግባባት የለም ሲባል ዘርፎቹ ብዙ ናቸው። ከዘርፎቹ ውስጥ ግን ታሪክ ቀዳሚው ነው። እኛ ኢትዮጵያዊያን እንደ አገር ከዘመናዊት ኢትዮጵያ ምስረታ፤ አገር የማቀናት ዘመቻዎች ጋር ተያይዞ ከተፈጠሩ ችግሮችና ተንከባላይ የትውልድ ዕዳዎች ታጋች (hostage) ከመሆን ይልቅ መታረቅ አለብን።

ምዕራባዊያን በሥልጣኔ ወደፊት መጓዛቸውን ያላቆሙበት ምስጢር ከታሪካቸው ጋር ስለ ታረቁ ነው። የታሪክ መሰረቶች ላይ የሚቆሙ ልዩነቶችን መሻገሪያው ብቸኛ መፍትሔ ታሪክን ለታሪክ ባለሙያዎች መተው ብቻና ብቻ ነው። ከምኒልክ ጋር የመታረቂያው አንዱ መንገድ ይሄው ነው!

ታሪክን ለታሪክ ባለሙያዎች መተው ከታሪካችን ጋር እንድንታረቅ ድልድይ ይሆነናል። ያኔ የኢትዮጵያ ታሪክ ሁሉንም የባህል ቡድኖች (በሰሜን፣ በደቡብ፣ በምስራቅና በምዕራብ ያሉትን) እንዲያካልል ማድረግ ይቻላል። ታሪካችንም የ“እኛ” እና የ“እነርሱ” በሚል ሳይሆን ዜግነታዊ መሰረት ባለው መልኩ አካቶነት ያለው የጋራ ታሪክ ማንበብ እንችላለን። ይህ መንገድ… በደም የተዋጀው ቆይታችን በእኩልነት ስሜት አንድነታችን በፅኑ መሰረት እንዲቆም ያደርገዋል። ያኔ ኢትዮጵያዊነት የብዙሃኑ ስሜት ይሆናል። በዚህ አግባብ የኢትዮጵያዊነት መገለጫውን ፈልጎ የሚያጣ የፖለቲካም ሆነ የማህበራዊ ኃይል አይኖርም።

ወደ አባ ዳኛው የአመራር ጥበብ ስንመለስ፡- የምኒልክ ድል የእርሱ እና የብርሃናማዋ ንግሥት ብቻ አልነበረም። በምኒልክ የንግስና ዘመን ለተመዘገቡ ዘመን ተሻጋሪ ውርሶች፤ ዋልታና ማገር የነበሩ አባቶችን ውለታ መርሳት የሚቻል አይደለም። ራስ ጎበና ዳጬ፣ ደጃች ባልቻ ሳፎ፣ ፊትአውራሪ ሀብተጊዮርጊስ ዲነግዴ፣ ራስ መኮንን ወ/ሚካኤል ጉዲሳ፣ ራስ ዳርጌ፣ ራስ ወልደገብርኤል፣ ራስ መንገሻ አንቲከም፣ ራስ ሚካኤል (መሐመድ አሊ)… እያልን ከምንዘረዝራቸው ታላላቅ የጦር አበጋዞች ከአማራው፣ ከኦሮሞና ከደቡብ የተውጣጡ የአገር ምስረታው የፊት መስመር ተሳታፊዎች ናቸው።
እንደራስ ጎበና ዳጬ ያለ ጀግና የጦር አበጋዝ ሰባት ግዛቶችን (የደቡብና የምዕራቡን) (ጥንተ-ርስትና ግዛቶቹን) የኢትዮጵያ አካል ማድረግ ችሏል። ዛሬ ላይ “ምኒልክ የእኛ ብቻ ነው” ሊሉ የሚቃጣቸው የታሪክ ኑፋቄ የተጫናቸው ዝንጉዎች የምኒልክ ብርቱ ቀኝ እጅ የነበሩት የጦር አበጋዞች ለኢትዮጵያ የግዛት አንድነት የደከሙትን ድካም፣ የከፈሉትን ዋጋ ከዚህ አንጻር በአደባባይ እየካዱ መሆኑን ይሰመርበት።

ምኒልክ ዘር አይመርጥም፣ ስበቱ ‘ፖወር’ ነው። ከብዙ ማሳያዎች አንድ፡- የራስ ጐበና ዳጬ ልጅ ወዳጆ ጐበና የምኒልኳን ሸዋረገድን አገባ፤ በውጤቱም ወሰንሰገድ የተባለ ልጅ ተወለደ። ይህ ልጅ በአሥራ አራት አመቱ ባይቀጭ የምኒልክ አልጋ ወራሽ ይሆን ነበር። በዚህ አግባብ ምኒልክ ለጐጃም ሰው ሳይሆን ለቱለማ ኦሮሞ ይቀርባል። ከበጌምድር ሰው ይልቅ የሸዋ ኦሮሞ የምኒልክ የመጀመሪያ የንግስና ዘመናት የኃይል ምንጭ ሆኖ አገልግሏል። የመንዝም ሆነ የየጁ ገበሬ ለምኒልክ ገባር ኢትዮጵያዊ ነበሩ። የአድዋ ሰውም ሆነ የወላይታ እኩል የምኒልክ ገባሮች ናቸው። ሌላውም እንደዛው!

በምኒልክ ሃውልት ላይ ተጽፎ የሚነበበው መልዕክተ-ምኒልክ ምን ይላል መሰለህ፦ “ከትልቅ ወይም ከትንሽ ቢሆን መወለድ ሙያ አይደለም ራስን ለታላቅ ታሪክ መውለድ ግን ሙያ ነው”። አየህ ምኒልክ ግዛታዊነትን የሥልጣን መወጣጫ ብቻ ሳይሆን ያደረገው በግዛቲቱ የሚታመኑለትን መሳፍንቶችም ከተለያየ ቋንቋ ተናጋሪነት ማውጣጣት ችሏል። ከጀምሩ በቴዎድሮስ ቤት ታላቅ ራዕይን ወርሷልና በሰከነ አመራሩ ኩምሳ ሞረዳንም ሆነ አባ ጅፋርን በጥበብ ገባሪው ማድረግ ችሏል።

እንደዚያኛው ቴዎድሮስን መንገድ መርቶ እንደሸጠው መካር አልቦ ንጉሥ (አጼ ዮሃንስ) “ሰማይ አምድ የለው፤ እስላም አገር የለው” የሚል አዋጅ አላስነገረም፤ ይልቁንስ በየደረሰበት ስፍራ ሁሉ “ሁሉም ባባቱ ይደር” የሚል አዋጅ ነበር ያስነግር የነበረው። አባ ጅፋር ምኒልክን ያከበረው ለምን ይመስልሃል? ‘እኔን ምሰል’ እንደማይለው ቀድሞውንም አውቆታል-ጅፋር ነፍሴ! እንጅማ ለ“ካፊር” ይገብር ነበር? የማይሆነውን!!

ሲጠቃለል፡- ምኒልክ የዘመኑ መሪ ብቻ ሳይሆን፤ ጥቁር ሰው መሆኑን በተግባር ያስመሰከረ፤ የነጮች ጌታ! የአድማሳዊ ስብዕና ባለቤት ነበር!!
መንጋው ብዙ ብዙ ሲል ወደን አይደለም ዝንተ-ዓለም ምኒልክ የምንለው!

[‘ከአንድ ስኬታማ ወንድ ጀርባ አንዲት ጠንካራ ሴት አለች’ የሚለው አባባል መነሻው ምኒልክ ቤተ-መንግሥት ነው። ያለ እቴጌዋ ፥ ምኒልክ የጥቁር ዘር ብርሃን መሆን ባልቻለ ነበር። ካላመንክ በ Chris Prouty የተፃፈውን “Empress Taytu and Menilk 1883-1910” መጽሃፍ ፈልገህ አንብብ]

ምኒልክ ጥቁር ሰው፤ የነጮች ጌታ!! ምንጭ፡ Gulilat Geletaw

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Middle Column, Opinions Tagged With: emiye menelik, operation dismantle tplf, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule