• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አንድ ጣሳ ማሽላ በ250 ብር በሚሸጥበት አላማጣ ተከማችቶ የነበረ ከ3 ሺሕ ኩንታል በላይ የእርዳታ እህል ተገኘ

October 28, 2022 01:57 am by Editor Leave a Comment

በአላማጣ ከተማ አሸባሪው ህወሓት ለታጣቂዎቹ አከማችቶት የነበረው ከ3 ሺሕ ኩንታል በላይ የእርዳታ እህል ተገኝቷል።

አሸባሪውና ወራሪው የወያኔ ቡድን ለራያ አላማጣ ህዝብ የሚመጣውን የእርዳታ እህል ለህዝቡ ሳያደርስ ለታጣቂዎቹ ቀለብ እንዲውል በየ መጋዝኖቹ እና ወፍጮ ቤቶች አከማችቶት መገኘቱን ነው መረጃው ያመለከተው።

ተከማችቶ የተገኘው የእርዳታ እህልም ከ2 ሺሕ 500 ኩንታል በላይ የዩ ኤስ አይዲ የተፈጨ የስንዴ ዱቄት፣ ከ400 ኩንታል በላይ ከረጢት የታሸገ ስንዴ፣ ከ100 ኩንታል በላይ ብስኩቶች እና ኃይል ሰጪ ምግቦች መሆኑም ተገልጿል።

የሽብር ቡድኑ ካለፈው 1 ዓመት ከ4 ወር በላይ በሆነ ጊዜ ውስጥ ለሰብዓዊ እርዳታ እንዲውል የሚገባ የትኛውንም አይነት ድጋፍ ከህዝቡ እየነጠቀ ለታጣቂዎቹ ሲያከማችና ሲቀልብ እንደነበር የአላማጣ ከተማ ነዋሪዎች ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።

ወይዘሮ ሰዓዳ አደም የአላማጣ ከተማ ነዋሪ ሲሆኑ ከሐምሌ/2013 ዓ.ም ጀምሮ ምንም ዓይነት እርዳታ ደርሷቸው እንደማያውቅ ገልፀው ልጆቻቸውን ለመመገብ በችግር እና በእንግልት ማሳለፋቸውን በተስፋ መቁረጥ ስሜት ውስጥ ሆነው ተናግረዋል።

አገዳ እየሸጡ እና በቆሎ እየጠበሱ በመሸጥ በሚያገኟት ገቢ ለልጆቻቸው እህል በውድ እንደሚሸምቱ የተናገሩት ው/ሮ ሰዓዳ አንድ ጣሳ ማሽላ በ250 ብር ይገዙ እንደነበርም ተናግረዋል።

የሽብር ቡድኑ እንኳንስ የእርዳታ እህል ሊሰጠን ቀርቶ ለልጆቻችን ቀለብ በውድ የገዛኋትን ትንሽ ማሽላ አስፈጭቼ ሳላቦካ ዱቄት አምጪ ብለው አስፈራርተው ይወስዱብኛል ብለዋል።

በሌላ በኩል አሸባሪው ህወሓት በመጋዘን አከማችቶ ለተዋጊው ቀለብ ሲጠቀምበት የነበረው ስንዴ ለህዝብ መከፋፈሉ ተገለጸ፡፡

አሸባሪው ህወሓት በሰብአዊ ድጋፍ ስም ወደ ትግራይ ክልል ሲገባ የነበረውን ስንዴ በመጋዘን አከማችቶ ለተዋጊ ሰራዊቱ ቀለብ ሲጠቀምበት የነበረውን 120 ኩንታል ስንዴ የመከላከያ ሰራዊት በመቆጣጠር ለ2 ሺህ 767 አባወራዎችና እማወራዎች አከፋፍሏል፡፡

የዕዙ ስነ-ልቦና ግንባታ ኃላፊ የመከላከያ ሠራዊት የበይ ተመልካች ለነበረው የኮረም ከተማ ነዋሪዎች የዕርዳታ እህል በማደል ለህዝብ ደራሽ መሆኑን በተግባር አሳይቷል ብለዋል፡፡

ከአሸባሪው ህወሓት ነፃ የወጡ ነዋሪዎች ሠራዊቱ የህዝቡን ደህንነት በመጠበቅ እና አሸባሪ ቡድኑ ለጦርነት አላማ ሊያውለው የነበረውን የእርዳታ እህል በመከፋፋላቸው ደስተኛ እንደሆኑ ገልፀዋል።

ነዋሪዎችም ሰራዊቱ ላደረገላቸው በጎ ተግባር ያላቸውን ምስጋና ገልፀው ባሳለፉት ጊዜያት በሽብር ቡድኑ ምክንያት ለረሃብና እንግልት ተጋልጠን ቆይተናል ማለታቸውን ከመከላከያ ሰራዊት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። (ዋልታ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ


Filed Under: News, Right Column Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule