• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አንድ ጣሳ ማሽላ በ250 ብር በሚሸጥበት አላማጣ ተከማችቶ የነበረ ከ3 ሺሕ ኩንታል በላይ የእርዳታ እህል ተገኘ

October 28, 2022 01:57 am by Editor Leave a Comment

በአላማጣ ከተማ አሸባሪው ህወሓት ለታጣቂዎቹ አከማችቶት የነበረው ከ3 ሺሕ ኩንታል በላይ የእርዳታ እህል ተገኝቷል።

አሸባሪውና ወራሪው የወያኔ ቡድን ለራያ አላማጣ ህዝብ የሚመጣውን የእርዳታ እህል ለህዝቡ ሳያደርስ ለታጣቂዎቹ ቀለብ እንዲውል በየ መጋዝኖቹ እና ወፍጮ ቤቶች አከማችቶት መገኘቱን ነው መረጃው ያመለከተው።

ተከማችቶ የተገኘው የእርዳታ እህልም ከ2 ሺሕ 500 ኩንታል በላይ የዩ ኤስ አይዲ የተፈጨ የስንዴ ዱቄት፣ ከ400 ኩንታል በላይ ከረጢት የታሸገ ስንዴ፣ ከ100 ኩንታል በላይ ብስኩቶች እና ኃይል ሰጪ ምግቦች መሆኑም ተገልጿል።

የሽብር ቡድኑ ካለፈው 1 ዓመት ከ4 ወር በላይ በሆነ ጊዜ ውስጥ ለሰብዓዊ እርዳታ እንዲውል የሚገባ የትኛውንም አይነት ድጋፍ ከህዝቡ እየነጠቀ ለታጣቂዎቹ ሲያከማችና ሲቀልብ እንደነበር የአላማጣ ከተማ ነዋሪዎች ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።

ወይዘሮ ሰዓዳ አደም የአላማጣ ከተማ ነዋሪ ሲሆኑ ከሐምሌ/2013 ዓ.ም ጀምሮ ምንም ዓይነት እርዳታ ደርሷቸው እንደማያውቅ ገልፀው ልጆቻቸውን ለመመገብ በችግር እና በእንግልት ማሳለፋቸውን በተስፋ መቁረጥ ስሜት ውስጥ ሆነው ተናግረዋል።

አገዳ እየሸጡ እና በቆሎ እየጠበሱ በመሸጥ በሚያገኟት ገቢ ለልጆቻቸው እህል በውድ እንደሚሸምቱ የተናገሩት ው/ሮ ሰዓዳ አንድ ጣሳ ማሽላ በ250 ብር ይገዙ እንደነበርም ተናግረዋል።

የሽብር ቡድኑ እንኳንስ የእርዳታ እህል ሊሰጠን ቀርቶ ለልጆቻችን ቀለብ በውድ የገዛኋትን ትንሽ ማሽላ አስፈጭቼ ሳላቦካ ዱቄት አምጪ ብለው አስፈራርተው ይወስዱብኛል ብለዋል።

በሌላ በኩል አሸባሪው ህወሓት በመጋዘን አከማችቶ ለተዋጊው ቀለብ ሲጠቀምበት የነበረው ስንዴ ለህዝብ መከፋፈሉ ተገለጸ፡፡

አሸባሪው ህወሓት በሰብአዊ ድጋፍ ስም ወደ ትግራይ ክልል ሲገባ የነበረውን ስንዴ በመጋዘን አከማችቶ ለተዋጊ ሰራዊቱ ቀለብ ሲጠቀምበት የነበረውን 120 ኩንታል ስንዴ የመከላከያ ሰራዊት በመቆጣጠር ለ2 ሺህ 767 አባወራዎችና እማወራዎች አከፋፍሏል፡፡

የዕዙ ስነ-ልቦና ግንባታ ኃላፊ የመከላከያ ሠራዊት የበይ ተመልካች ለነበረው የኮረም ከተማ ነዋሪዎች የዕርዳታ እህል በማደል ለህዝብ ደራሽ መሆኑን በተግባር አሳይቷል ብለዋል፡፡

ከአሸባሪው ህወሓት ነፃ የወጡ ነዋሪዎች ሠራዊቱ የህዝቡን ደህንነት በመጠበቅ እና አሸባሪ ቡድኑ ለጦርነት አላማ ሊያውለው የነበረውን የእርዳታ እህል በመከፋፋላቸው ደስተኛ እንደሆኑ ገልፀዋል።

ነዋሪዎችም ሰራዊቱ ላደረገላቸው በጎ ተግባር ያላቸውን ምስጋና ገልፀው ባሳለፉት ጊዜያት በሽብር ቡድኑ ምክንያት ለረሃብና እንግልት ተጋልጠን ቆይተናል ማለታቸውን ከመከላከያ ሰራዊት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል። (ዋልታ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ


Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Right Column Tagged With: ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule