በእነ ጃዋር ሲራጅ መሃመድ ላይ ተከፍቷል ከተባለው የክስ መዝገብ ጋር በተያያዘ በመጪው ሳምንት መግለጫ እንደሚሰጥ ዐቃቤሕግ አስታወቀ። ጃዋር ሲራጅ መሀመድን ጨምሮ በአጠቃላይ በ24 ሰዎች ላይ በመዝገብ ቁጥር 260215 በ10 ተደራራቢ ክሶች ማስከፈቱን ያስታወቀው ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ጉዳዩን በማስመልከት በመጪው ሳምንት የመጀመሪያ ቀናት መግለጫ እንደሚሰጥ ተገለፀ። “ክስ መመሥረት ባለበት ጊዜ ውስጥ ባለመመሥረቱ ተከሳሾቹ ከሰኞ ጀምሮ ከእሥር ሊለቀቁ ነው የሚል ወሬ በሕዝብ ዘንድ ተሰራጭቷል” መግለጫው ዐቃቤ ሕግ ተቋሙ እየሰራ ያለውን ሥራ ማኅበረሰቡ እንዲያውቀው ለማድረግ የሚሰጥ ነው ብለዋል። የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የክስ መዝገብ መከፈቱን በተመለከተ ዛሬ በይፋዊ የፌስቡክ ገጹ አጭር ጥቅል መረጃን ሰበር በሚል ርዕስ ሰጥቷል። “ፍርድ ቤት ራሱ ክሱ በዝርዝር … [Read more...] about እነ ጃዋር ይከሰሳሉ – ዐቃቤ ሕግ
Archives for September 2020
በ3 ቀናት በአዲስ አበባ ሕገወጥ 100 ሺህ ዶላርና 6.6 ሚሊዮን ብር ተያዘ
ኢትዮጵያ አዲስ የብር ኖቶችን ማስተዋወቋን ተከትሎ ከፍተኛ የሆነ ህገ-ወጥ የገንዘብ ዝዉዉር እየተስተዋለ እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ገልጿል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማም የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የብር ኖት ለዉጥ መደረጉን ተከትሎ ባደረገዉ የኦፕሬሽን እና የድንገተኛ ፍተሻ ስራ በርካታ ቁጥር ያለዉ ገንዘብ በቁጥጥር ስር አዉሏል፡፡ በጥቁር ገበያ ሲንቀሳቀስ የነበረ ከ5 ሚሊዮን ብር በላይ እንዲሁም በየኬላዎች በተደረገዉ ድንገተኛ ፍተሻ በህገ ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ የነበረ 1.6 ሚሊዮን ብርን ጨምሮ 100 ሺህ የአሜሪካ ዶላር በድምሩ 10.6 ሚሊዮን የኢትጵያ ብር በላይ በቁጥጥር ስር ማዋሉን በኮሚሽኑ የሙስና፣ ገቢዎች እና ልዩ ልዩ ወንጀሎች ምርመራ ዳይሬክተር ኮማንደር ግርማ ተሰማ ለአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ተናግረዋል፡፡ ኮሚሽኑ ህገ-ወጥ የገንዘብ ዝዉዉሩን … [Read more...] about በ3 ቀናት በአዲስ አበባ ሕገወጥ 100 ሺህ ዶላርና 6.6 ሚሊዮን ብር ተያዘ
ኦሮሞዎች በየዓመቱ ለሚያከብሩት ኢሬቻ በዓል ቦታ ተሰጠ
የኦሮሞ ተወላጆች በየዓመቱ ለሚያከብሩት የኢሬቻ በዓል መከበሪያ ቦታ በአዲስ አበባ መስጠቱን አስተዳደሩ አስታወቀ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለኢሬቻ በዓል (ሆረ ፊንፊኔ) ማክበሪያ ቦታ የባለቤትነት ማረጋገጫ ካርታ ለአባገዳዎች በዛሬው ዕለት አስረክቧል። ከዚህ በተጨማሪ ዛሬ ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዓሉ የሚከበርበትን ቦታ ከአባገዳዎች ጋር በመሆን በመጎብኘት ዝግጁነቱን አረጋግጠዋል። በኮቪድ-19 ምክንያት የዘንድሮ በዓል በአባገዳዎች በሚወሰን ትንሽ የሰው ቁጥር ብቻ እንደሚከበር ከስምምነት ላይ መደረሱን ምክትል ከንቲባ አዳነች አቤቤ አሳውቀዋል። የኢሬቻ በዓል ከገዳ ሥርዓት ጋር የተጣመረ ነው፤ ይህም ሃይማኖታዊ ክብረበዓል የገዳን ሥርዓት ሃይማኖታዊ ያደርገዋል፤ ስለዚህ የገዳ ሥርዓት እንደ ትምህርት በመንግሥት ትምህርት ቤቶች መሰጠት አይገባውም … [Read more...] about ኦሮሞዎች በየዓመቱ ለሚያከብሩት ኢሬቻ በዓል ቦታ ተሰጠ
በገንዘብ ዝውውር የተከሰሰ በ10 ዓመት ጽኑ እሥራት ይቀጣል
በሕገ-ወጥ መንገድ ገንዘብ ያዘዋወረ፣ በዝውውሩ የተሳተፈና ለአዘዋዋሪዎች ሽፋን የሰጠ 10 ዓመት የሚደርስ ጽኑ እስራትና የገንዘብ ቅጣት እንደሚጠብቀው የፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግ አስታወቀ። ባለፉት ሁለት ዓመታት በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ በሕግ አስከባሪ አካላት ቁጥጥር ስር እየዋለ መሆኑ በአገሪቱ በሕገ-ወጥ መንገድ የሚዘዋወር ገንዘብ የመኖሩ አንድ ማሳያ ነው። በመሆኑም በዚሁ የሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር ተግባር ላይ ተሳታፊ የሆነ ማንኛውም አካል በወንጀል ሕግ ከመጠየቅ እንደማይድንም ጠቅላይ አቃቤ ግህ ጠቁሟል። በኢትዮጵያ በ1996 ዓም በወጣው የወንጀል ሕግ መሰረት በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር ውስጥ ተሳትፎ የተገኝ ማንኛውም አካል እስከ 10 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ይቀጣል። ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about በገንዘብ ዝውውር የተከሰሰ በ10 ዓመት ጽኑ እሥራት ይቀጣል
ከ69 ሚሊዮን ዶላር በላይ ከመመሪያ ውጪ ከኢትዮጵያ ባንክ መባከኑ በሰነድ ተረጋገጠ
* የመለስ ፋውንዴሽን 100 ሺ ዶላር ወስዷል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ሥልጣን በያዙ ማግስት የሀገሪቱ የውጭ ምንዛሪ ካዝና ክፉኛ ተመዝብሮ ባዶ እንደነበር ተናግረው ነበር። እርሳቸውም ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ በሀገሪቱ የውጭ ምንዛሪ ከብሔራዊ ባንክ ደንብና መመሪያ ውጭ ሲባክን እንደ ነበር ሸገር ያገኘው አንድ ሰነድ ያስረዳል። ከለውጡ ወዲህ ባሉ ጊዜያትም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የውጭ ምንዛሪ ከብሔራዊ ባንክ መመሪያ ውጭ ለማይፈቀድላቸው እንደሰጠ ሸገር ካገኘው ሰነድ ተረድቷል። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአቶ በቃሉ ዘለቀ ይመራ በነበረበት በ2010 ዓመት ከግንቦት እስከ ነሐሴ ከባንኩ በትንሹ ከ69 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር በላይ (የውጭ ምንዛሪ) ከመመሪያ ውጪ ለተለያዩ ግለሰቦችና ድርጅቶች እንደተሰጡ ከሰነዱ አንብበናል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጪ ምንዛሪ … [Read more...] about ከ69 ሚሊዮን ዶላር በላይ ከመመሪያ ውጪ ከኢትዮጵያ ባንክ መባከኑ በሰነድ ተረጋገጠ
በድሬዳዋ፤ ደቡብ ኦሞና ጌዴኦ ሃሰተኛና ሕገወጥ የብር ኖቶች ተያዙ
በድሬደዋ የፀጥታ አካላት በጋራ ባካሄዱት የክትትልና ቁጥጥር ስራ በህገ -ወጥ መንገድ የሚንቀሳቀሱ የሀገርን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት የገንዘብ ኖቶች መያዛቸው ተገለፀ።ገንዘቡ በቁጥጥር ስር የዋለው ትላንት መስከረም 6/2013 ዓ/ም ሲሆን ከህበረተሰቡ በተሰጠ ጥቆማ መሰረት ባደረገ ክትልል መሆኑን ድሬ ፖሊስ አስታውቋል።ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት አላቸው ተብለው የተጠረጠሩ 4 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው በህግ መታየት መጀመሩም ተገልፃል።በቁጥጥር ስር ከዋሉት የብር ኖቶች ውስጥ በዋነኝነት፦ ዘጠኝ መቶ አርባ አርት ሺ አንድ መቶ አስር (944,110) የኢትዮጽያ ብርአንድ ሺ ሁለት መቶ ሀምሳ (1250) የአሜሪካን ዶላርአንድ መቶ ስልሳ አምስት (165) የሳውዲ ሪያልሰባት መቶ አርባ አምስት (745) ዩሮ ሲሆኑ ከእነዚህ ጋር አብሮም ከዘጠኝ በላይ የሚሆኑ … [Read more...] about በድሬዳዋ፤ ደቡብ ኦሞና ጌዴኦ ሃሰተኛና ሕገወጥ የብር ኖቶች ተያዙ
ብር የመለወጡ ቀጥተኛ ጥቅም
ብዙ ሰዎች በተደጋገሚ ብሩ በመለወጡ በቀጥታ ኢኮኖሚው ላይ የሚመጣውን ጥቅም ንገረን ብለው ጠይቀውኛል! ብር በመለወጡ የሚገኙት የአጭር ግዜ እና የረጅም ግዜ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታዎች የሚከተሉት ናቸው! የአጭር ግዜ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታዎች፡- በሀገራችን ከ113ቢሊዮን ብር በላይ ጥሬ ገንዘብ ከፋይናንስ ገበያው ቁጥጥር ውጪ አለ! ስለዚህ የገንዘብ ለውጡ ይህንን ገንዘብ ወደ ብሄራዊ ባንክ የመለወጥ እድል ይፈጥራል! ለምሳሌ፡- ምንጩ ያልታወቀ በመሆኑ ወደ ባንክ ሳይመጣ ከሚበላሸው፤ ከሀገር ውጪ በጎረቤት ሀገር በመሸሹ ከማይመለሰው፤ የመቀየሪያ ወቅቱ ከሚያልፍበት፤ በጎርፍ፤ በቃጠሎ፤ ወዘተ ከወደመው ውጪ 100 ቢሊዮን ብር እንኳን ወደ ህጋዊ የባንክ ስርዓት ቢመጣ ከፍተኛ ገንዘብ ከገበያ የመሰብሰብ እድል ስለሚፈጠር የዋጋ ንረት በሚታይ መልኩ የመቀነስ አቅም ይኖረዋል! ምንጩ … [Read more...] about ብር የመለወጡ ቀጥተኛ ጥቅም
ካርቱም ከውድመት ተረፈች
ሱዳን መዲናዋ ካርቱምን የማጥፋት አቅም ያላቸው የፈንጂ መስሪያ ተቀጣጣይ ቁሶችን በቁጥጥር ሥር አዋለች። ቁሶቹን ከ41 ተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ሥር ማዋሏን ዐቃቤ ሕግ ታገልሲር አል ሔርብን ጠቅሶ የዘገበው አፍሪካ ኒውስ ነው። የተያዘው ፈንጂ መፈብረኪያ ቁስ የዛሬ አንድ ወር ተኩል አካባቢ ቤይሩትን ያጋየው አሞኒየም ናይትሬት እንደሚገኝበት የመንግሥት ባለሥልጣናት ረቡዕ ተናግረዋል። በቁጥጥር ሥር የዋለው በርከት ያለ መጠን ያለው ተቀጣጣይ የፈንጂ ቁስ ከነሐሴ ወር ጀምሮ በአገሪቱ ደህንንነት መስሪያ ቤት ክትትል ሲደረግባቸው ከነበሩ የሽብር ቡድኖች ጋር የተያያዘ መሆኑም አፍሪካ ኒውስ በድረገፁ ዘግቧል። ሱዳን በሽግግር መንግሥት መተዳደር ከጀመረች አንድ ዓመት ያለፋት ሲሆን የህወሓት የቅርብ ወዳጅ ከነበሩት ዖማር አልበሽር ጊዜ ጀምሮ አሜሪካ በአሸባሪነት ፈርጃት ኢኮኖሚዋን … [Read more...] about ካርቱም ከውድመት ተረፈች
ስለ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ የኢሰመኮ ይፋዊ መግለጫ
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በአንዳንድ አካባቢዎች እየታዩ ያሉ የፀጥታ መደፍረሶችን ተከትሎ ያጋጠሙ ክስተቶች እጅግ አሳስበውታል፡፡ ኮሚሽኑ ከክልሉ ከመተከል ዞን፣ ቡለን ወረዳ አጳር ቀበሌ እንዲሁም ከወንበራ ወረዳ መልካን ቀበሌ እጅግ አሳሳቢ መረጃዎች እየደረሱት ነው፡፡ ኮሚሽኑ በጳጉሜ 1፤ 2012 ዓ.ም እንዲሁም ከጳጉሜ 2 አስከ መስከረም 3፤2013 ዓ.ም መካከል ቢያንስ ሁለት ጥቃቶች ማጋጠማቸውን ከክልሉ መንግስት ለማረጋጥ ችሏል፡፡ በቦታው ላይ ከሚገኝ አንድ መንግስታዊ ምንጭ መረዳት እንደተቻለው ቢያንስ በሁለት ዙር በደረሱ ጥቃቶች ባልታጠቁ ሲቪሎች ላይ ግድያዎች መፈፀማቸውን እንዲሁም በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መፈናቀላቸውን ኮሚሽኑ ማረጋገጥ ችሏል፡፡ የክልሉ መንግስት እንደጠቆመው ከተፈናቃዮቹ መካከል 300 ያህል የሚሆኑት ወደ ቀያቸው … [Read more...] about ስለ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ የኢሰመኮ ይፋዊ መግለጫ
በጋምቤላ በ10 ሺህዎች በጎርፍ መጥለቅለቅ ተፈናቅለዋል
ከ18ሺህ በላይ ሰዎች ጋምቤላ ክልል ላሬ ወረዳ ውስጥ በጎርፍ መፈናቀላቸውን የአካባቢው ባለስልጣናት አስታወቁ። የጎርፍ መጥለቅለቅ አደጋ የተከሰተበት ወረዳው ኢትዮጵያን ከሱዳን በሚያዋስን አካባቢ ነው። የጋምቤላ ክልል ፕሬስ ሴክሬታሪያት ጽ/ ቤት ከተፈናቃዮች መካከል ወ/ሮ ኛዳክ ፓችን ጠቅሶ እንደዘገበው ሰሞኑን እየጣለ ያለው ከባድ ዝናብ በፈጠረው ጎርፍ ምክናያት ቤት ንብረታቸውን ጥለው ከነቤተሰቦቻቸው በትምህርት ቤት አጥር ጊቢ ውስጥ ተጠልለው ይገኛሉ። መንግሥት የአልባሳትና የምግብ አቅርቦት ባለማድረጉም ለከፋ ችግር መጋለጣቸውን ወ/ሮ ኛዳክ ተናግረዋል። በጋምቤላ ክልል ኑዌር ዞን የላሬ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጋርዊች ቢየል በስልክ ተጠይቀው በሰጡት ምላሽ ሱዳንንና ኢትዮጵያን የሚያዋስነው ጂካዎ ወንዝ ሞልቶ በተፈጠረው ችግር ከ18ሺህ በላይ ሰዎች ተፈናቅለዋል፣ የሚኖሩትም … [Read more...] about በጋምቤላ በ10 ሺህዎች በጎርፍ መጥለቅለቅ ተፈናቅለዋል