• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በድሬዳዋ፤ ደቡብ ኦሞና ጌዴኦ ሃሰተኛና ሕገወጥ የብር ኖቶች ተያዙ

September 17, 2020 04:50 pm by Editor Leave a Comment

በድሬደዋ የፀጥታ አካላት በጋራ ባካሄዱት  የክትትልና ቁጥጥር ስራ በህገ -ወጥ መንገድ የሚንቀሳቀሱ የሀገርን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት የገንዘብ ኖቶች መያዛቸው ተገለፀ።

ገንዘቡ በቁጥጥር ስር የዋለው ትላንት መስከረም 6/2013 ዓ/ም ሲሆን ከህበረተሰቡ በተሰጠ ጥቆማ መሰረት ባደረገ ክትልል መሆኑን ድሬ ፖሊስ አስታውቋል።

ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት አላቸው ተብለው የተጠረጠሩ 4 ግለሰቦች በቁጥጥር  ስር ውለው ጉዳያቸው በህግ መታየት መጀመሩም ተገልፃል።

በቁጥጥር ስር ከዋሉት የብር ኖቶች ውስጥ በዋነኝነት፦

  • ዘጠኝ መቶ አርባ አርት ሺ አንድ መቶ አስር  (944,110) የኢትዮጽያ ብር
  • አንድ ሺ ሁለት መቶ ሀምሳ (1250) የአሜሪካን ዶላር
  • አንድ መቶ ስልሳ አምስት (165) የሳውዲ ሪያል
  • ሰባት መቶ አርባ አምስት (745) ዩሮ

ሲሆኑ ከእነዚህ ጋር አብሮም ከዘጠኝ  በላይ የሚሆኑ ሀገራት የተለያየ መጠን ያላቸው የብር ኖቶች በቁጥጥር ስር ውለዋል።

በሌላ በኩል ደቡብ ኦሞና ጌዴኦ ዞኖች ሀሰተኛ የብር ኖቶችና አዘዋዋሪዎች መያዛቸው ተገልጿል።

የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኢንስፔክተር እታገኘሁ ዜና እንዳሉት በደቡብ ኦሞና ጌዴኦ ዞኖች 35 ሺህ ባለአንድ መቶ ሃሰተኛ የብር ኖቶችና አራት ተጠርጣሪ አዘዋዋሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።፡

በቁጥጥር ስር ማዋል የተቻለው ህብረተሰቡ ባደረሰው ጥቆማ መነሻ ላለፉት ሶስት ቀናት ፖሊስ ባደረገው ክትትል ነው ብለዋል፡፡

ከሀሰተኛ የብር ኖቶች ውስጥ  27 ሺህ 900 በደቡብ ኦሞ  ጂንካ ከተማ፣ ደቡብ አሪና ኛንጋቶም ወረዳዎች ቀሪው  7 ሺህ 200 በጌዴኦ ዞን ገዴብ ወረዳ መሆኑን አመልክተዋል፡፡

የሀሰተኛ የብር ኖቶች አዘዋዋሪዎቹ ገበያዎችና ሱቆች አከባቢ በመንቀሳቀስ በያዟቸው በሀሰተኛ የብር ኖቶች  ተንቀሳቃሽ ስልኮች፣ አልባሳትና መሰል ዕቃዎች ግብይት እያካሄዱ ባሉበት ወቅት እንደተደረሰባቸው ኢንስፔክተሯ አስረድተዋል።

ሀሰተኛ የብር ኖቶችን ከሚያዘዋዉሩ መካከል ሶስቱ ከደቡብ ኦሞ ቀሪው ከጌዴኦ ዞን እንደተያዙ አመልክተው በህግ ቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እይተደረገባቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት ነባሩ የብር ኖት በአዲስ እየተቀየረ በመሆኑ በዚህ አጋጣሚ ህገ ወጥ ተግባር ለመፈጸም የሚጥሩ አካላትን ለመከላከል ፖሊስ እየተቆጣጠረ  መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: illegal money, new birr notes

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
Copyright © 2026 · Goolgule