በኢትዮ-ሶማሌ ክልል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ የመጣው የሰብዓዊ መብት ጥሰትና መፈናቀል በክልሉ አስተዳደር በኩል መፍትሔ ተሰጥቶት እንዲስተካከል በፌዴራል መንግሥት በኩል የተለያዩ ጫናዎችና የሽምግልና መድረኮች ላይ የእርቅ ስምምነቶች ሲደረጉ ቆይተዋል። ሆኖም ግን የሰብዓዊ መብት ጥሰቱ ሲብስበት እንጂ ሲቀንስ አልታየም፤ በዚህ ጊዜ ደግሞ የፌዴራል መንግሥት ነገሮችን በቸልታ እንዳያይ የሚያደርገውና ጫን ያለ እርምጃ እንዲወስድ የሚያስችለው የህግ ማዕቀፍ አለው። ይኸውም የፌዴራል መንግሥት በክልሎች ጉዳይ ጣልቃ የሚገባበትን ሁኔታ የሚደነግገው አዋጅ ቁጥር 359/2003 (95) ሲሆን በዚህ አዋጅ መሠረት የፌዴራል መንግሥት በክልሎች ጉዳይ ጣልቃ የመግባት ወሰኑ እስከምን ድረስ እንደሆነ በግልፅ ተደንግጓል። የፌደራል መንግሥት በክልሎች የሚፈፀሙ ህገመንግሥታዊም ሆነ ሰብዓዊ መብት ጥሰተቶች … [Read more...] about በክልሎች ጉዳይ የፌዴራል መንግስት ጣልቃ ገብነት እስከምን ድረስ ነው?
Law
የሕግ ያለህ
ግንቦት 20 በህግ የታወቀ የህዝብ በዓል ነው?
በእኛ ሀገር የሚከበሩ የህዝብ በዓላት በህግ የታወቁ ናቸው። ኢትዮጵያ ውስጥ የሚሠሩ መንግሥትና መንግሥታዊ ያልሆኑ ዓለምአቀፍ ተቋማት እንዲሁም ኢምባሲዎች እና የቆንፅላ ጽ/ቤቶችም የእኛን ሕዝብ በዓላቶች እንዲያከብሯቸው ይጠበቃል። ምክንያቱም በዓላቱን ማክበር ህዝብን ማክበር ከዚያም ሲያልፍ ሀገሪቱ ሉዓላዊ መሆኗን ማረጋገጥ ነውና። እነዚህ በዓላት የዘመን መለወጫ በዓል (መስከረም 1)፣ የዓደዋ ድል መታሰቢያ ቀን (የካቲት 23)፣ የድል ቀን (ሚያዝያ 27)፣ የዓለም የሠራተኞች ቀን፣ መስቀል (መስከረም 17)፣ ጥምቀት (ጥር 11)፣ የክርስቶስ ልደት(ታህሳስ 29/28) እንዲሁም ቀናቸው በየዓመቱ የሚቀያር ስቅለት፣ ትንሳዔ፣ ፣ኢድ አልአድሃ፣ መውሊድና ኢድ አል ፈጥር ናቸው። በእነዚህ ቀናት እንደሁኔታው የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች፣ የግል ድርጅቶችና የንግድ ሱቆች ለሕዝብ አገልግሎት ዝግ … [Read more...] about ግንቦት 20 በህግ የታወቀ የህዝብ በዓል ነው?
State of Emergency in Ethiopia! A Constitutional Coup D’état?
Introduction What an eventful and an emotional roller-coaster ride February 2018 was in Ethiopia. First, the Oromo People’s Democratic Organization (OPDO) released a groundbreaking and a far-reaching statement. Then the Oromo population, led by the Oromo youth group, Qeerro, staged a hugely successful market boycott along with political rallies throughout Oromia. Within the second day of the Qeerro’s action, the Ethiopia government released thousands of political prisoners, including prominent … [Read more...] about State of Emergency in Ethiopia! A Constitutional Coup D’état?
ህወሓት፡ የHR 128 ፍርሃቻ እና የማግኒትስኪ ሕግ
ከዚህ በፊት በአሜሪካ ምክርቤት በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ በረቂቅ ሕግነት ከቀረቡት መካከል ህወሓት/ኢህአዴግ HR 128 እጅግ ፈርቶታል። ይህንን ረቂቅ ሕግ ለማክሸፍም የውትወታ (ሎቢ) ሥራ ከመሥራት ጀምሮ የአሜሪካ ባለሥልጣናትንና የፖለቲካ መሪዎችን በ“አልሻባብ ምስራቅ አፍሪካን ይወራል” ድራማ ለማስፈራራት ተደጋጋሚ በርካታ ሙከራዎችን ቢያደርግም አልተሳካለትም። ላለፉት በርካታ ወራትም (በቅርቡ ወደ አሜሪካ የመጡትን እነ ወርቅነህን ጨምሮ) ሊያሳምኑ ይችላሉ የሚላቸውን ሹሞቹን በመላክ ረቂቅ ሕጉ በተግባር እንዳይውል የአሜሪካ ባለሥልጣናትንን - ጊዜ ስጡን፣ ሁሉን እናስተካክላለን፣ … የመሳሰሉ ተማጽንዖዎችን ሲያቀርብ ቆይቷል። በግምባር ቀደምትነትም የህወሓት ወዳጅ የሆኑት ሴናተር ኢንሆፍ ህወሓት/ኢህአዴግን ለመታደግ ኢትዮጵያ ድረስ እስኪሄዱ ያደረሰ የውትወታ ሥራ ተካሄዷል። ይህንን ረቂቅ … [Read more...] about ህወሓት፡ የHR 128 ፍርሃቻ እና የማግኒትስኪ ሕግ
ግልጽ ደብዳቤ፦ ለኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ)
ጉዳዩ፦ በቂሊንጦ እሳት ሰበብ ስለታሰሩት ሰዎች የተደረገውን ምርመራ በተመለከተ እንደሚታወቀው ኢሰመኮ በቀን 20 ጥቅምት 2010፣ በደብዳቤ ቁጥር ሰመኮ/2.1/29/2010 እንደገለጸው ነሐሴ 1/2008 አዲስ አበባ ማረሚያ ቤት (ቂሊንጦ) ግቢ ውስጥ የተነሳውን እሳት መንስዔ ለማጣራት በተደረገው ምርመራ አሰቃቂ የመብቶች ጥሰቶች ተፈፅመዋል። በእነ መቶ ዐለቃ ማስረሻ ሰጤ መዝገብ (38 ተከሳሾችን) በተመለከተ መንግሥት ባለበት አገር ይፈፀማሉ ተብለው የማይጠበቁ የጥፍር መንቀል፣ በሚስማር ሰውነት የመብሳት፣ ግርፋት እና የመሳሰሉት አካላዊ ጉዳት የሚያደርሱ፣ ሰብኣዊ ክብርን የሚያዋርዱ የጭካኔ ተግባራት በተያዙ ሰዎች ላይ ተፈፅሞባቸዋል። ይሄ ሁሉ የሆነው ፍርድ ቤት በአደራ እንዲጠብቃቸው ያስረከበው የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ኃላፊነቱን ባለመወጣቱ ነው። ሆኖም፣ ዋነኞቹ የምርመራው (ወይም … [Read more...] about ግልጽ ደብዳቤ፦ ለኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ)
የገዱ አንዳርጋቸው ፈተና
በህወሓት ተመልምለውና ለሥልጣን በቅተው ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ “የለውጥ ኃይል” እየተባሉ ከሚወደሱት መካከል አንዱ የሆነው ገዱ አንዳርጋቸው ለምስክርነት መጥሪያ ተቆርጦለታል። ገዱና ሌሎች ህወሓት እንደ ጭቃ ጠፍጥፎ የሠራው ብአዴን አባላት የተጠሩት በነ ንግሥት ይርጋ ክስ በመከላከያ ምስክርነት ነው። ህዝባዊ ዓመጹ የተነሳው “በመልካም አስተዳደር ችግር” ምክንያት እንደነበር እነ ገዱ በተደጋጋሚ በየሚዲያው ሲናገሩ ቆይተዋል። ዓቃቤሕግ ደግሞ ክሱን የመሠረተው ሕዝባዊ ዓመጹን ከ“ሽብር” ጋር በማገናኘት ነው። በ“ለውጥ ኃይልነት” ሲወደስ የነበረው ገዱ አንዳርጋቸው ታማኝነቱ ለማን እንደሆነ በይፋ የሚያሳይበት ፈታኝ ወቅት ላይ የሚገኝ ሲሆን አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች “አንገቱ ላይ ያለውን ገመድ ለማጥበቅ በህወሓት የታቀደ ሤራ ነው” ብለውታል። በተለይ ሃይለማርያም ደሳለኝ እና ደመቀ መኮንን … [Read more...] about የገዱ አንዳርጋቸው ፈተና
ሆላንድ ዜጋቸውን ጨፍጭፈው ለሚመጡ ወንጀለኞች መደበቂያ ገነት አትሆንም – ፍትህ ሚኒስትር
መቶ አለቃ እሸቱ አለሙ እድሜልክ እስራት ተፈረደባቸው ዛሬ ዲሴምበር 15 ቀን 2017 ከቀትር በኋላ በሆላንድ ዘሄግ ከተማ የዋለው ችሎት በመቶ አለቃ በእሸቱ አለሙ አቃቤ ህግ ባቀረበባቸው የጦር ወንጀል ክስ እድሜልክ እስራት በይኖባቸዋል። በተጠቀሳባቸው ክስ በሙሉ ጥፋተኛ ተብለዋል። ከሁለተኛው አለም ጦርነት በኋላ እንዲህ አይነት ፍርድ በሆላንድ ሃገር ሲሰጥ የመጀመርያው መሆኑን አቃቤ ህግ ተናግረዋል። በሃገሪቱ ህግ የእድሜ ልክ እስራት አመክሮ የለውም። ዜጋቸውን ጨፍጭፈው ለሚመጡ ወንጀለኞች የመደበቅያ ገነት እንደማትሆን የሆላንድ ፍትህ ሚኒስትር አስታወቁ። አቶ እሸቱ አለሙ በውሳኔው ሰዓት ችሎቱ ላይ መገኘት አልፈለጉም። በአራት ዳኞች በተሰየመው በዚህ International Crime Chamber የተሰኘ ችሎት የመሃል ዳኛዋ ማርየት ሬከንስ የፍርድ ውሳኔውን ባሰሙበት ወቅት … [Read more...] about ሆላንድ ዜጋቸውን ጨፍጭፈው ለሚመጡ ወንጀለኞች መደበቂያ ገነት አትሆንም – ፍትህ ሚኒስትር
ሕገመንግሥቱ የፀደቀው በቀጥታ ሕዝቡ ወስኖበት ሳይሆን በተወካዮች ነው – ዶ/ር ነጋሦ ጊዳዳ
በህወሓት ትዕዛዝና አርቃቂነት በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የተጫነውን "ሕገ መንግሥት" "አርቃቂ" ኮሚሲዮን በሊቀመንበርነት የመሩት ዶ/ር ነጋሦ ጊዳዳ "ከዚህ በፊት ህገ መንግስቱን ስናፀድቅ ህዝቡ በቀጥታ አልወሰነበትም፡፡ በተወካዮች በኩል ነው የወሰነው" በማለት ከሌሎች አዲስ አድማስ ቃለ meጠይቅ ካደረገላቸው ግለሰቦች ጋር በመሆን "የማይገሠሠው ሕገ መንግሥት" "ክብሩ"ን አውርደውታል፡፡ ዘገባው እንዲህ ቀርቧል:- በፓርቲዎች ድርድር ኢህአዴግ፤ “ልደራደርባቸውም አልችልም” በሚል ውድቅ ካደረጋቸው አጀንዳዎች አንዱ የህገ መንግስቱ መሻሻል ጉዳይ ነው፡፡ በእርግጥ ህገ መንግስቱ ለፖለቲካ ፓርቲዎች ድርድር መቅረብ የሚችል አይደለም? ኢህአዴግ ለምን ለድርድርና ለውይይት እንዳይቀርብ ፈለገ? ህገ መንግስቱ ሲጸድቅ ተሳትፎ የነበራቸው አንጋፋ ፖለቲከኞችን ጨምሮ ምሁራን አስተያየት ሰጥተውበታል፡፡ … [Read more...] about ሕገመንግሥቱ የፀደቀው በቀጥታ ሕዝቡ ወስኖበት ሳይሆን በተወካዮች ነው – ዶ/ር ነጋሦ ጊዳዳ
“… ተድብድቤ በቃሬዛም ቢሆን ያምጡኝ እንጂ ካሁን በኋላ በራሴ ፈቃድ ‘ወደ ችሎት’ አልመጣም” በቀለ ገርባ
"… ተድብድቤ በቃሬዛም ቢሆን ያምጡኝ እንጂ ካሁን በኋላ በራሴ ፈቃድ አልመጣም” በፍርድ ሂደቱ ሲሉ መሰላቸታቸውን አቶ በቀለ ገርባ ተናገሩ። አቶ በቀለ ይህንን የተናገሩት ሃሙስ ባስቻለው ችሎት የመናገር እድል እንዲሰጣቸው ጠይቀው ሲፈቀድላቸው ነው። ከሁለት ቀን በፊት አቃቤ ህግ በማስረጃነት አቀርበዋለሁ ሲለው የነበረውን የድምጽ ከምስል ማስረጃ አስተርጉሞ እንዲያቀርብና የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኤጀንሲ ሃላፊ ችሎት እንዲገኙ ትዕዛዝ ሰጥቶ ነበር። ይሁን እንጂ በቀጠሮው በትዕዛዙ መሰረት ዓቃቤ ሕግ በእነ አቶ በቀለ ገርባ ላይ ያቀረበውን የድምፅ ከምስል ማስረጃ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዛሬም እንዳላስተረጎመው አሳውቋል። የኤጀንሲው ሃላፊ ችሎት አለተገኙም። የክልሎች ቋንቋ ሃላፊ ጸጋ ልዑል ወልደኪዳን "ብቁ ጋዜጠኞች ስለሌሉ አልተተረጎመም” በማለት የሰጡትን ምክንያት ፍርድ … [Read more...] about “… ተድብድቤ በቃሬዛም ቢሆን ያምጡኝ እንጂ ካሁን በኋላ በራሴ ፈቃድ ‘ወደ ችሎት’ አልመጣም” በቀለ ገርባ
ባለቤት ያጣ ሕገ መንግሥት?
የፌዴራል ሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን የቀድሞው የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ መላኩ ፈንታና በሌሎች ግለሰቦች ላይ የጉምሩክ አዋጅ ቁጥር 60/89፣ 368/95፣ 622/2001 እና የወንጀል ሕግን በመጥቀስ፣ በሥልጣን አለአግባብ በመገልገልና በጥቅም በመተሳሰር የቀረጥ ነፃ መብትን ያላግባብ በመገልገል፡ እንዲመረመር አለማድረግ ወይም እንዳይመረመር ማድረግ፣ ገደብና ቁጥጥር የሚደረግባቸውን ዕቃዎች (መድኃኒቶች) በማስገባት ወንጀል ክስ አቅርቦባቸው፣ ጉዳያቸው በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 15ኛ ወንጀል ችሎት እየታየ እያለ አዲሱ የጉምሩክ አዋጅ ቁጥር 859/2006 ወጥቷል፡፡ አዲሱ አዋጅ ነባር የጉምሩክ አዋጆችን ሙሉ በሙሉ ሽሯል፡፡ ስለዚህም ከላይ የተጠቀሱት ድርጊቶች በአዲሱ ሕግ ወንጀልነታቸው ቀርቷል፡፡ የኢፌዴሪ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 22 ንዑስ … [Read more...] about ባለቤት ያጣ ሕገ መንግሥት?