• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

Law
የሕግ ያለህ

“የክስ መቋረጥ” ወይስ የኦባማ ጉብኝት?

July 13, 2015 03:59 am by Editor 1 Comment

“የክስ መቋረጥ” ወይስ የኦባማ ጉብኝት?

"ክሴን አቋርጫለሁ" ከማለት ባለፈ ምክንያቱን ከመናገር ተቆጥቧል ከአንድ ዓመት በፊት ሚያዝያ 26 እና 27 ቀን 2006 ዓ.ም. በድንገት ተይዘው ከታሰሩ በኋላ፣ በፌዴራል ዓቃቤ ሕግ ክስ ተመሥርቶባቸውና የሰነድና የሰው ማስረጃ ቀርቦባቸው፣ ለብይን የተቀጠሩበትን ቀን እየተጠባበቁ ከነበሩት አሥር ተከሳሾች መካከል አምስቱ በድንገት ሐምሌ 1 እና 2 ቀን 2007 ዓ.ም. መፈታታቸው እያነገጋገረ ነው፡፡ ለተከሳሾቹም ሆነ ወክለዋቸው ለሚከራከሩላቸው ጠበቆቻቸው ምንም ዓይነት መረጃ ሳይደርሳቸው በድንገት፣ ‹‹ዓቃቤ ሕግ ክሱን አቋርጣል፡፡ በመሆኑም ከዛሬ ጀምሮ ከእስር ተለቃችኋል፤›› የተባሉት ተከሳሾች ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ፣ አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስ፣ ኤዶም ካሳዬና ጦማሪያን ዘለዓለም ክብረትና ማህሌት ፋንታሁን ናቸው፡፡ ክሱ እንደተቋረጠ በማረሚያ ቤት ኃላፊዎች ከማወቃቸው … [Read more...] about “የክስ መቋረጥ” ወይስ የኦባማ ጉብኝት?

Filed Under: Law Tagged With: Left Column

አቶ መላኩና አቶ ገብረዋህድ የቀረበባቸውን ክስ ክደው ተከራከሩ

June 29, 2014 04:29 am by Editor 3 Comments

አቶ መላኩና አቶ ገብረዋህድ የቀረበባቸውን ክስ ክደው ተከራከሩ

"ልንመሰገንበት በሚገባ ሥራ ወንጀለኛ መባላችን ያሳዝናል"  አቶ መላኩ ፈንታ በከባድ የሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ክስ የተመሠረተባቸው የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ የቀድሞ ዋና ዳይሬክተር አቶ መላኩ ፈንታና የሕግ ማስከበር ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ገብረዋህድ ወልደጊዮርጊስ፣ የቀረበባቸውን ክስ ክደው በመከራከር ድርጊቱን አለመፈጸማቸውንና ጥፋተኛም እንዳልሆኑ ለፍርድ ቤት ሰኔ 18 ቀን 2006 ዓ.ም. አስረዱ፡፡ የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ዓቃቤ ሕግ፣ በተጠርጣሪዎቹ ላይ በሦስት የክስ መዝገቦች ክስ ማቅረቡ ይታወሳል፡፡ አንደኛውን የክስ መዝገብ እንዲያሻሽል የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 15ኛ ወንጀል ችሎት ያዘዘው ቢሆንም፣ ዓቃቤ ሕግ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት በትዕዛዝ ላይ ይግባኝ በማለቱና በማሳገዱ ተጠርጣሪዎቹ በሁለቱ የክስ መዝገቦች ላይ ብቻ የእምነት … [Read more...] about አቶ መላኩና አቶ ገብረዋህድ የቀረበባቸውን ክስ ክደው ተከራከሩ

Filed Under: Law Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

የሽብርተኝነት እንቆቅልሽ

April 13, 2014 10:00 pm by Editor Leave a Comment

የሽብርተኝነት እንቆቅልሽ

መንግስታት በተለያየ መልኩ ትርጉመው ያቀረቡትን ሽብርተኝነት ለመዋጋት በሚል ህግ ያወጣሉ፡፡ በእርግጥ በአዲስ መልክ በሽብር ላይ የታወጀው ዘመቻ በአሜሪካ ግፊት የመጣ ነው፡፡ እ.ኤ.አ በ2001 አሜሪካ ከደረሰባት የሽብር ጥቃት በኋላ "war on terror" እንዲሁም "counter ter­rorism" የተሰኙ ዘመቻዎችን ነድፋ ተንቀሳቅሳለች፡፡ አሜሪካ ወዳጅም ሆነ የቀዩ ባላንጣዎቿን ሳይቀር ደልላም ሆነ ተማጽና የጀመረችው ይህ "ጸረ ሽብር ዘመቻ" መንግስታት በየ አገራቸው የራሳቸውን ጥቅም የሚያስጠብቁ አፋኝ "የጸረ ሽብር" ዘመቻ እንዲያወጡ እድል ሰጣቸው፡፡ አሜሪካ የሰብአዊ መብት ይጥሳሉ እያለች ስትወቅሳቸው የነበሩ ስርዓቶች ሳይቀሩ የተደላደለ የዴሞክራሲያዊ መሰረት ባልተጣለበት ሁኔታ ዴሞክራሲያዊና ሰብአዊ መብቶችን የሚደፈጥጡ አዋጆች አጽድቀው ሲተገብሩ ከሀያሏ አገር የገጠማቸው ወቀሳና … [Read more...] about የሽብርተኝነት እንቆቅልሽ

Filed Under: Law Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

የፀረ ግብረ ሰዶማዊነት ሕጋችን ቢከለስስ?

March 13, 2014 09:26 am by Editor Leave a Comment

የፀረ ግብረ ሰዶማዊነት ሕጋችን ቢከለስስ?

የዛሬው ጽሑፌ መነሻውና መድረሻው በዚህ ሳምንት አነጋጋሪ ስለነበረው የኡጋንዳ የፀረ ግብረ ሰዶም ሕግና አገራችን በንፅፅር የምትወስደውን ልምድ መቃኘት ነው፡፡ ኡጋንዳ ይህንን ሕግ በማውጣቷ ዓለም ተደንቋል፡፡ አፍሪካን ግን የሚደንቅ አይደለም፡፡ አገራችንንማ ሕጓን እንድታጠነክር ካልሆነ ግብረ ሰዶማዊነትን የሚታገስ ባህልም ሕግም ኖሯት አያውቅም፡፡ ዜናው እጅጉን የሳበው ምዕራባውያንን ነው፡፡ ኡጋንዳ እንደ ሌሎቹ የአፍሪካ አገሮች በአንድ ወቅት ቅኝ ገዥ ስለነበራት የድሮው አስተሳሰብ የተፀናወታቸው ወገኖች ተቃውሞውን አድምቀውት ሰንብተዋል፡፡ አገራችን በማንም ቅኝ ተገዝታ ባለማወቋ፣ ባህሏ የራሷ በመሆኑ ተቃዋሚዎች የመተቸቱን ሞራል የኡጋንዳን ያህል አያገኙትም፡፡ ከዓለም ጋር አንድ በሚያደርገን በተባበሩት መንግሥታትም ቢሆን አንድ የሆነ አቋም ባለመኖሩ፤ ቢኖርም በተዓቅቦ … [Read more...] about የፀረ ግብረ ሰዶማዊነት ሕጋችን ቢከለስስ?

Filed Under: Law Tagged With: Left Column

ተከብሮ ያላስከበረ ሕገ-መንግስት …

December 9, 2013 09:37 am by Editor 2 Comments

ተከብሮ ያላስከበረ ሕገ-መንግስት …

ህዳር 29 ቀን 1987 ዓ.ም ሕገ-መንግስቱ የፀደቀበት ቀን ነው፡፡ ይህንንም ተከትሎ በመንግስት አሳሳቢነት እልፍ ሲልም አስገዳጅነት ህዳር 29 በየዓመቱ ከተለያዩ ጎሳ የተወጣጡ ሰዎች ተሰባስበው በመንግሰት ሹማምንቶች ፊት በአደባባይ ከበሮ የሚደለቅበት ቀን ነው፡፡ ይሁን እንጂ የአብዛኛው ኢትዮጵያዊያን መልካም ፍቃድና ተሳትፎ ባልታየበት የፀደቀው ህገ መንግስት በብዙሃን ዘንድ ተቀባይነቱ ጥያቄ ውስጥ የገባ ነው፡፡ በዚህም መሠረት ከቃሉ አጠቃቀም ጀምሮ እስከ አከባበሩ ክብረ በዓል አብዛኛዉ ሰው እኔንም ጨምሮ ግድ አይሰጠንም፡፡ ‹‹ይህ ህገ-መንግስቱን የመነዳ ተግባር ነው!!!›› ከገዢው መንግስት ተደጋግሞ የሚሰማ ለመፈረጅ ወይም ለመከሰስ የሚጠቀሙበት ቃል ነው፡፡ አንድ ወዳጄ እንዲህ አለኝ ‹‹ይህ ህገ መንግሰት ዝም ብሎ የተደረደረ ብሎኬት ነው እንዴ የሚናደው?›› በማለት ሲተች … [Read more...] about ተከብሮ ያላስከበረ ሕገ-መንግስት …

Filed Under: Law Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

በእነ መላኩ ፈንታ መዝገብ ሥር ያሉት 24 ተከሳሾች ክስ መሰማት ጀመረ

October 25, 2013 08:47 am by Editor Leave a Comment

በእነ መላኩ ፈንታ መዝገብ ሥር ያሉት 24 ተከሳሾች ክስ መሰማት ጀመረ

የፌዴራሉ የሥነ ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ዐቃቤ ህግ ከትናንት በስቲያ ጀምሮ በገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣናት እና ግብረ አበር ባለሀብቶች ላይ የመሰረተውን ክስ በፍርድ ቤት ማሰማት ጀምሯል። የኮሚሽኑ ዐቃቤ ህግ በተለይም በአንደኛው ተከሳሽ በአቶ መላኩ ፈንታ ላይ መዝገብ ቁጥር 14356 ስር ባለው 11ኛ ክስ ውስጥ ተከሳሹ በትዳር ያለችን ሴት አስኮብልለዋል የሚል ክስ መስርቶባቸዋል። ትናንት በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 15ኛ ወንጀል ችሎት ክሱ ሲነበብ፤ 1ኛው ተከሳሽ አቶ መላኩ ፈንታ የስራ ኃላፊነታቸውን በመጠቀም ለስራ ጉዳይ የመጣችን ሴት፤ ትዳሯን ፈታና በትዳር ውስጥ ያፈራቻቸውን ሦስት ልጆች በትና አብራቸው እንድትሆን አድርገዋል ሲል ስልጣንን ያለአግባብ የመጠቀም የሙስና ወንጀል ፈፅመዋል ሲል ከሷቸዋል። ወ/ሮ መቅደስ ለማ የተባሉት እኚሁ ሴት የቀድሞ ባለቤታቸውን ንብረት … [Read more...] about በእነ መላኩ ፈንታ መዝገብ ሥር ያሉት 24 ተከሳሾች ክስ መሰማት ጀመረ

Filed Under: Law Tagged With: Left Column

አደባበዬቻችን እና መንገዶቻችን መሉሱልን?!

October 8, 2013 08:16 am by Editor Leave a Comment

አደባበዬቻችን እና መንገዶቻችን መሉሱልን?!

‹‹ ዲሞክራሲ የሚመሠረተው መንግስት ሕዝቡን ሊያገለግል የቆመ ነው በሚል መሠረት ሃሳብ ላይ ነው፡፡ ይህም ማለት ሕዝብ መንግሥትን ለማገልገል የተፈጠረ አይደለም፡፡ በሌላ አነጋገር ህዝብ የአንድ ዲሞክራሳዊ አገር ዜጋ እንጂ ተገዥ አይደለም፡፡ መንግስት የህዝብን መብት በሚያስጠብቅበት ወቅት ህዝብ ደግሞ በልዋጩ ለመንግስት ታማኝነቱን ይገልፃል፤በጨቋኝ ሥርዓት ግን መንግስት ራሱን ከህዝብ በማግለል ታማኝነትን ከህዝብ ይሻል ፤መንግስት ውሳኔ የሚወስነው ተገቢውን የህዝብ ድጋፍና ተሳትፎ ሳያገኝ ከሆነ የህዝብ ታማኝነት መመኘት ከንቱ ቅዠት ይሆናል፡፡ ›› (what is democracy) ከሚለው መፃፍ የተወሰደ ነው፡፡ ጥላቻ ሁለተኛ ከባዱ የሰው ልጅ ስሜት ነው፤ፍቅር የመጀመሪያ ነው፡፡ ጥላቻ በፍራቻ በእውቀት ማነስና በተጠራጣሪነት የሚመጣ ነው፡፡ ጥላቻ ይቅር ባይነትና መግባባትን ያሣጣል፡፡ … [Read more...] about አደባበዬቻችን እና መንገዶቻችን መሉሱልን?!

Filed Under: Law Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

ጥያቄው ሃይማኖታዊ ነፃነት መብት ወይስ ፖለቲካዊ…

October 3, 2013 12:18 am by Editor Leave a Comment

ጥያቄው ሃይማኖታዊ ነፃነት መብት ወይስ ፖለቲካዊ…

‹‹መንግስት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም፤ ሃይማኖትም በመንግስት ጣልቃ አይገባም፡፡›› ሕገ መንግስት አንቀጽ 11 ንዕስ አንቀፅ 3፡፡ ‹‹ማንኛውም ሰው የማሰብ፤ የሕሊና እና የሃይማኖት ነጻነት አለው፡፡ ይህ መብት ማንኛውም ሰው የመረጠውን ሃይመኖት ወይም እምነት የመያዝ ወይም የመቀበል ሃይማኖቱንና እምነቱን ለብቻ ወይም ከሌሎች ጋር በመሆን በይፋ ወይም በግል የማምለክ፣ የመከተል፣የመተግበር፣ የማስተማር ወይም የመግለጽ መብትን ያካትታል፡፡›› ሕገ መንግስት አንቀጽ 27 ንዕሱ አንቀፅ 1፡፡ ‹‹ማንኛውም ሰው የሚፈልገውን እምነት ለመያዝ ያለውን ነጻነት በኃይል ወይም በሌላ ሁኔታ ማስገደድ ወይም መከልከል አይቻልም፡፡›› ሕገ መንግስት አንቀጽ 27 ንዕስ አንቀፅ 3 ፡፡ የሙስሊሞች ጥያቄ 1ኛ. በስልጣን ላይ የሚገኙት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አመራሮች … [Read more...] about ጥያቄው ሃይማኖታዊ ነፃነት መብት ወይስ ፖለቲካዊ…

Filed Under: Law Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

አጭር ማስታወሻ በሰማያዊ ፓርቲ የተቃውሞ ሠልፍ

September 5, 2013 08:57 am by Editor 2 Comments

አጭር ማስታወሻ በሰማያዊ ፓርቲ የተቃውሞ ሠልፍ

ነሀሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ሰማያዊ ፓርቲ ታላቅ የተቃውሞ ሠልፍ መጥራቱ የሚታወቅ ነው፤ ይሁን እንጂ በስልጣን ላይ ያለው መንግስት እንደሰፈር ጉልበታኛ ዱንኳን ሰባሪ ዘው ብሎ በሃይማኖት ስበብ ሰማያዊ ፓርቲ በጠራው ቀንና ሰዓት እንዲሁም ቦታ በህግ አግባብ ሣይሆን በጉልበት ሠልፍ መሰል ሠልፍ ማካሄዱ የሚታወቅ ነው፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም የተቃውሞ ሠልፍ በማድረግ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ የተቃውሞ ሠልፈኞች እንዲሁም የአገር ውስጥና የውጪ የመገናኛ ብዙሃን በተገኙበት መንግስት ሊመልሳቸው የሚገባ ጥያቄዎችን የጠየቀ ሲሆን ለጥያቄዎቹም ምላሽ የሰጠው የጊዜ ገደብ ሦስት ወር መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡ ይሁን እንጂ መንግስት በተሰጠው ጊዜ የተጠየቀውን ጥያቄ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ፓርቲውን በመወንጀል እና ስም የማጥፋት ዘመቻውን አጠናክሮ … [Read more...] about አጭር ማስታወሻ በሰማያዊ ፓርቲ የተቃውሞ ሠልፍ

Filed Under: Law Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

የከባድ ሙስና ተጠርጣሪዎች ክሱ ሳይሰጣቸው ተከሳችኋል መባላቸውን ተቃወሙ

September 1, 2013 03:12 am by Editor Leave a Comment

የከባድ ሙስና ተጠርጣሪዎች ክሱ ሳይሰጣቸው ተከሳችኋል መባላቸውን ተቃወሙ

* አቶ በእግዚአብሔርና አቶ ምሕረተአብ ተጨማሪ ጊዜ ተጠየቀባቸው * ሦስት የባለሥልጣኑ ሠራተኞች በነፃ ተሰናበቱ * የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ስምንት የክስ መዝገቦች አቅርቧል የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን በከባድ የሙስና ወንጀል ተሳትፎ በጠረጠራቸውና ከሦስት ወራት በላይ በእስር ላይ ባቆያቸው የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉሙሩክ ባለሥልጣን ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ ኃላፊዎች፣ ሠራተኞች፣ ነጋዴዎችና ሌሎች ተጠርጣሪዎች ላይ ነሐሴ 23 ቀን 2005 ዓ.ም ክስ መመሥረቱን፣ ለፍርድ ቤት ቢያሳውቅም፣ ተጠርጣሪዎቹ መከሰሳቸውን የሚያሳይ ክስ እንዳልደረሳቸውና የሕግ ሥርዓትን ያልተከተለ መሆኑን በመግለጽ ክሱን ተቃወሙ፡፡ የኮሚሽኑ መርማሪ ቡድን በተጠርጣሪዎቹ ላይ ምርመራውን አጠናቆ ለኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ማስረከቡን፣ ጊዜ ቀጠሮውን ሲከታተል ለነበረው  የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሁለተኛ … [Read more...] about የከባድ ሙስና ተጠርጣሪዎች ክሱ ሳይሰጣቸው ተከሳችኋል መባላቸውን ተቃወሙ

Filed Under: Law Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

  • « Previous Page
  • Page 1
  • …
  • Page 7
  • Page 8
  • Page 9
  • Page 10
  • Page 11
  • Next Page »

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule