ፈጽመዋል በተባሉት በዋና ወንጀል አድራጊነት፣ በአታላይነት፣ በከባድ እምነት ማጉደል፣ በሰነድ ማጥፋትና ሐሰተኛ ምስክርነት መስጠት ወንጀል የተጠረጠሩት ባልና ሚስት፣ አቶ ጌታቸው ጣሰውና ወይዘሮ ሸዋነሽ መንግሥቱ፣ እንዲሁም የቅርብ ዝምድና እንዳላቸው የሚገለጸው አቶ ዘውዱ ክንፈና አቶ ወንድአፍራሽ ፍቅሩ፣ ከፍተኛ ዋጋ ያለውን የሊዝ መብት፣ በተጭበረበረ መንገድ እንዲሸጥ አድርገዋል በሚል ታሠሩ፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ፈጽመዋል በተባሉባቸው ድርጊቶች ስድስት ክሶች የተመሠረቱባቸው በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ሲሆን፣ የፈጸሙት ወንጀል በዝምድና በተሳሰረ መንገድና ከፍተኛ መሆኑን በመግለጽ ፍርድ ቤቱ ዋስትና ከልክሏቸው፣ ጉዳያቸውን በማረሚያ ቤት ሆነው እንዲከታተሉ ብይን ተሰጥቶባቸዋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ፈጽመዋል የተባሉባቸው የወንጀል ድርጊቶችን በሚመለከት ክስ ያቀረበባቸው የፌዴራል … [Read more...] about ከፍተኛ ዋጋ ያለው የሊዝ መብት በተጭበረበረ መንገድ በማሸጥ የተጠረጠሩ ባልና ሚስት ታሰሩ
Law
የሕግ ያለህ
በግብረሰዶም ተጠርጣሪዎች ላይ የሳይኮሎጂና የሳይካትሪ ባለሙያ የምስክርነት ቃል ሰጡ
ሁለት የ10 እና የ11 ዓመት ዕድሜ ያላቸው የአራተኛና የአምስተኛ ክፍል ተማሪዎች ላይ የግብረሰዶም ጥቃት ፈጽመዋል በሚል ተጠርጥረው በእስር ላይ በሚገኙት የካራክተር ሆልማርክ አካዳሚ ስድስት መምህራን ክስ ላይ፣ ከዓቃቤ ሕግ ምስክሮች በተጨማሪ አንዲት የሳይኮሎጂና የሳይካትሪ ባለሙያ ሐምሌ 25 ቀን 2005 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ቀርበው የሙያ የምስክርነት ቃላቸውን ሰጡ፡፡ የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ በተጠርጣሪዎቹ ላይ የመሠረተውን የወንጀል ክስ በማየት ላይ ያለው የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ሰባተኛ የወንጀል ችሎት፣ ስማቸው በሚዲያ እንዳይገለጽ የከለከለላቸው የሳይኮሎጂስትና የሳይካትሪ ባለሙያዋ፣ በተጠርጣሪ መምህራን የግብረሰዶም ጥቃት ደርሶባቸዋል የተባሉትን ሁለት ወንድ ሕፃናት፣ ለሦስት ጊዜያት አግኝተው እንዳነጋገሯቸው ገልጸዋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹንም ሆኑ የጥቃቱ ሰለባ ናቸው የተባሉት … [Read more...] about በግብረሰዶም ተጠርጣሪዎች ላይ የሳይኮሎጂና የሳይካትሪ ባለሙያ የምስክርነት ቃል ሰጡ
ግብረሰዶም ፈጽመዋል በተባሉ ተጠርጣሪዎች ላይ ምስክሮች ተሰሙ
ከአዘጋጆቹ፤ ኢህአዴግ የፈጠራትና “በሕዝቦች መፈቃቀድ ላይ የተመሠረተችው” ኢትዮጵያ ይህንን ትመስላለች፡፡ ሰላማዊ ሰዎችን “አሸባሪ” እያሉ ለማሰር ሕግ ከማውጣትና ዜጎችን በፍርሃት ከመሸበብ ይልቅ እንዲህ ያለው አስጸያፊ ተግባር በህጻናት ላይ ከመፈጸሙ በፊት እጅግ ከረር ያሉና ቅጣታቸው የከበደ ሕጎችን ማውጣት፤ የማኅበረሰቡ ድርና ማግ የሆኑትን እና ኢትዮጵያዊ ጨዋነትን የሚያደፋሩ አማራጮችን መፍጠር፤ ወዘተ ጥቂቶቹ የመከላከያ አማራጮች ናቸው፡፡ ይህ በአንድ ት/ቤት የተፈጸመና ይፋ የሆነ ነው እንጂ በየጊዜው በተመሳሳይ ሁኔታ እየተደፈሩ ተበላሽተው የቀሩ ልጆች ስንት እንደሆኑ ለማወቅ አንዱ ህጻን እዚሁ ዜና ላይ እንደተናገረው ከሌሎች አራት ት/ቤቶች ተደፍሮ መጥቶ ወደዚህኛው (ካራክተር ሆልማርክ አካዳሚ) ከገባ በኋላም ተመሳሳይ ጥቃት እንደተሰነዘረበት ማንበቡ ከበቂ በላይ ማስረጃ … [Read more...] about ግብረሰዶም ፈጽመዋል በተባሉ ተጠርጣሪዎች ላይ ምስክሮች ተሰሙ
የአደባባይ የብልግና ቧልት በሕጉ እንዴት ይታያል?
የዛሬው ጽሑፍ የሚያጠነጥነው በወንጀል ሕግ ዙሪያ ነው፡፡ የወንጀል ሕግና የኅብረተሰቡ የሞራል አስተሳሰብ የጠበቀ ቁርኝት አላቸው፡፡ በአብዛኛው በኅብረተሰቡ እንደ ኃጢአት ወይም ነውር የሚቆጠሩ ድርጊቶች በወንጀል ሕግም የሚያስጠይቁ ናቸው፡፡ አመንዝራነት፣ ስርቆት፣ ስድብ፣ ግብረ ሰዶም ወዘተ. ኃጢአት ወይም ነውር ብቻ ሳይሆኑ ወንጀልም ተደርገው በወንጀል ሕጉ እንደሚያስቀጡ ተመልክቶ እናገኛለን፡፡ ይሁን እንጂ ኃጢአት ወይም ነውር የሆነ ድርጊት ሁሉ ግን ወንጀል ላይሆን ይችላል፡፡ ዝሙት አዳሪነትን ለዓብነት ብንመለከት ድርጊቱ ኃጢአት ወይም ነውር መሆኑ ባያጠያይቅም፣ በወንጀል ሕጋችን በመርህ ደረጃ የወንጀል ኃላፊነት የማያስከትል ድርጊት ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ የወንጀልና የኃጢአት ግንኙነት ስፋት እንደ ኅብረተሰቡ የሞራል አስተሳሰብ የሚለያይ ስለሚሆን በሁሉም ዘንድ ተመሳሳይ መግባባት ላይኖር … [Read more...] about የአደባባይ የብልግና ቧልት በሕጉ እንዴት ይታያል?
Harmony among Ethiopian various legislative frameworks
In this article I will attempt to examine whether or not Ethiopia as a federal state structure has put in place all necessary mechanisms so that it functions as it supposed to do so. Practical examples in other countries constituted as federal political state structure will be cited repeatedly to give our readers a full grasp of the complex legal issues at hand. This is in particular important for those who are not legal trained and find difficulty to understand the legal question at hand. In … [Read more...] about Harmony among Ethiopian various legislative frameworks
“ፍትሕ ሁሉን አቀፍ የሆነ መብት ነው”
ዶ/ር ያዕቆብ ኃይለ ማርያም 50ኛ ዓመቱን ለማክበር በዝግጅት ላይ የሚገኘው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ትምህርት ቤት የመጀመርያ ዙር ተመራቂ ናቸው፡፡ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን አሜሪካ ከሚገኘው የካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ በሕግ ያገኙ ሲሆን፣ የፒኤችዲ ዲግሪም ያገኙት እዚያው አሜሪካ ነው፡፡ ዶ/ር ያዕቆብ በቀይ ሽብር ምክንያት ከአገር ከመሰደዳቸው በፊት በሕግ አማካሪነትና በጠበቃነት ያገለገሉ ሲሆን፣ በአሜሪካ ከ20 ዓመታት በላይ በማስተማር ሥራ ላይ ተሰማርተው ቆይተዋል፡፡ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ፍርድ ቤት ሩዋንዳ ውስጥ በዓቃቤ ሕግነት ለሦስት ዓመታት አገልግለዋል፡፡ ወደ ማስተማር ሥራቸው ተመልሰው ለሁለት ዓመታት ከቆዩ በኋላ በተመድ ግብዣ በናይጄሪያና በካሜሩን መካከል የነበረውን የወሰን ክርክር ለማየት ተቀጥረው ለሁለት ዓመታት ያህል አገልግለዋል፡፡ በአብዛኛው በሰው … [Read more...] about “ፍትሕ ሁሉን አቀፍ የሆነ መብት ነው”
የኮሚሽኑ መርማሪ ቡድን በተጠርጣሪዎች 60 የክስ መዝገቦች መቋረጣቸውን አስታወቀ
- የ14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ተፈቀደለት - ሁለት ተጠርጣሪዎች በምርመራ ወቅት መደብደባቸውን ተናገሩ ‹‹ተያዘ የተባለው ሰነድ ሁሉ በሀብት ምዝገባ ያስመዘገብኩት ነው›› አቶ ገብረ ዋህድ ወልደ ጊዮርጊስ የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ምርመራ ቡድን፣ በተለያዩ የሙስና ወንጀሎች ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር በዋሉ ተጠርጣሪዎች እንዲቋረጡ ከተደረጉት 60 የክስ መዝገቦች ውስጥ 28 ያህሉን መሰብሰቡን ግንቦት 19 ቀን 2005 ዓ.ም. ለፍርድ ቤት አስታወቀ፡፡ መርማሪ ቡድኑ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሁለተኛ ወንጀል ችሎት ቀርቦ እንዳስረዳው፣ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ባለፉት 14 ተጨማሪ የምርመራ ቀናት ላይ የሠራውን የምርመራ ሥራ እንዳብራራው፣ ከገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ሥራዎች ጋር ግንኙነት ያላቸውን የኤሌክትሮኒክስ መሣሪያዎችን … [Read more...] about የኮሚሽኑ መርማሪ ቡድን በተጠርጣሪዎች 60 የክስ መዝገቦች መቋረጣቸውን አስታወቀ
በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩት ባለሥልጣናትና የታዋቂ ነጋዴዎች የፍርድ ቤት ውሎ
“ያለመከሰስ መብቴ አልተነሳም መንግሥት የሚያውቀው ሕመም አለብኝ” አቶ መላኩ ፈንታ፣ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር “እኔ በተጠረጠርኩበት ወንጀል ልጠየቅ ቤተሰቦቼን ግን ለምን? ምን ዓይነት አገር እየሆንን ነው?” አቶ ገብረዋህድ ወልደጊዮርጊስ፣ ምክትል ዋና ዳይሬክተር “ታዋቂ ግብር ከፋይና ታዋቂ ስለሆንኩ በዋስ ልለቀቅ” አቶ ከተማ ከበደ፣ የኬኬ ድርጅት ባለቤት “የዋስ መብቴ ተጠብቆ ሥራዬን ላስተካክል ለሠራተኞቼ ደመወዝ ልክፈል” አቶ ስማቸው ከበደ፣ የኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል ባለቤት ቀረጥና ታክስ በማጭበርበር፣ አራጣ በማበደርና በመመሳጠር ሕገወጥ ዕቃዎች እንዲያልፉ ያደረጉ ተጠርጣሪዎችን ክስ በማቋረጥ፣ የተከለከለ ሲሚንቶ ወደ አገር ውስጥ እንዲገባና ሕገወጥ ዕቃዎች ያለፍተሻ እንዲያልፉ አድርገዋል በሚል ተጠርጥረው በፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን … [Read more...] about በሙስና ወንጀል የተጠረጠሩት ባለሥልጣናትና የታዋቂ ነጋዴዎች የፍርድ ቤት ውሎ
The dilemma of adopting ethnic federal system in Africa: Ethiopian experience
This article aims to analyse the major challenges of adopting ethnic federal system in Africa with special focus on the context of Ethiopia’s ethnic federal system. It is argued that though the adoption of ethnic federal system in Ethiopia has created the opportunity for minority groups to exercise their cultural and linguistic rights, the ethnic federal experiment has faced enormous challenges. The challenges include problems of legitimacy, unprecedented emphasis on ethnicity and lack of … [Read more...] about The dilemma of adopting ethnic federal system in Africa: Ethiopian experience
አዲሱ የሃይማኖት ህግና የሃገሪቱ ህገመንግስት
አዲሱ የሃይማኖት ህግና የሃገሪቱ ህገመንግስት (በሰለሞን) መንግሥት ሕገ-መንግስቱን ሊያከበር ይገባል! (ከእምነት ቤቶች) በጉዳዩ ላይ እንድንወያይ ስንጠየቅ ይህ የሃገረቱን ህገመንግስት ይቃረናል እኛም እዚህ ተወክለን የመጣነው ለሌላ ጉዳይ እንጂ በህግ ላይ ህግ ለማውጣት አይደለም ብለን አጀንዳው እንዲመለስ አድርገናል ፡፡(ከተስብሳቢዎች አንዱ) በስራ ላይ የዋለውን እንደ አዲስ ለማጸደቅ በተዘጋጀው ረቂቅ ላይ ውይይት እንዲደረግ የእምነት ተቌማት የጋራ ጉባኤ ላይ ቀርቦ ነበር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ አይመለከተኝም ብላ ወጥታ ነበር ቀጥሎም የኢትዮጵያ እስልምና ጽህፈት ቤትም አይመለከተኝም ብሎ ነበር፡፡ በመጨረሻምወንጌላዊያን ይህ ህግ እነርሱ ላይ ተፈጻሚ ሆኖ የቆየ ቢሆንም በህግ መልክ እንደገና ሲቀርብ ግን ተገርመውበታል፡፡ “ኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች መርጠው በላኳቸው … [Read more...] about አዲሱ የሃይማኖት ህግና የሃገሪቱ ህገመንግስት