• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የከባድ ሙስና ተጠርጣሪዎች ክሱ ሳይሰጣቸው ተከሳችኋል መባላቸውን ተቃወሙ

September 1, 2013 03:12 am by Editor Leave a Comment

* አቶ በእግዚአብሔርና አቶ ምሕረተአብ ተጨማሪ ጊዜ ተጠየቀባቸው

* ሦስት የባለሥልጣኑ ሠራተኞች በነፃ ተሰናበቱ

* የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ስምንት የክስ መዝገቦች አቅርቧል

የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን በከባድ የሙስና ወንጀል ተሳትፎ በጠረጠራቸውና ከሦስት ወራት በላይ በእስር ላይ ባቆያቸው የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉሙሩክ ባለሥልጣን ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ ኃላፊዎች፣ ሠራተኞች፣ ነጋዴዎችና ሌሎች ተጠርጣሪዎች ላይ ነሐሴ 23 ቀን 2005 ዓ.ም ክስ መመሥረቱን፣ ለፍርድ ቤት ቢያሳውቅም፣ ተጠርጣሪዎቹ መከሰሳቸውን የሚያሳይ ክስ እንዳልደረሳቸውና የሕግ ሥርዓትን ያልተከተለ መሆኑን በመግለጽ ክሱን ተቃወሙ፡፡

የኮሚሽኑ መርማሪ ቡድን በተጠርጣሪዎቹ ላይ ምርመራውን አጠናቆ ለኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ማስረከቡን፣ ጊዜ ቀጠሮውን ሲከታተል ለነበረው  የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሁለተኛ ወንጀል ችሎት መግለጹ ተዘግቦ ነበር፡፡ በዕለቱ የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ መረከቡን ለችሎቱ በማረጋገጥ የክስ መመሥረቻ ጊዜ 15 ቀናት እንዲሰጠው ጠይቆ 13 ቀናት እንደተፈቀደለት ይታወሳል፡፡ የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ክስ መመሥረት የነበረበት ነሐሴ 13 ቀን 2005 ዓ.ም ቢሆንም፣ “ከመርማሪ ቡድኑ የደረሰኝ የምርመራ ግኝት ያልተሟላ በመሆኑ በወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ 38 ሐ መሠረት አሟልተህና የኦዲት ሪፖርቱንም አካተህ እንድታመጣ፤” ብሎኛል በማለት መርማሪ ቡድኑ፣ ነሐሴ 15 ቀን 2005 ዓ.ም ለተረኛ ችሎቱ ካሳወቀ በኋላ፣ በዓቃቤ ሕግ የታዘዘውን የምርመራ ሥራ ለማከናወን 14 ቀናት ጊዜ እንዲሰጠው መጠየቁ ይታወሳል፡፡ ተረኛ ችሎቱ “የጠየቀው ተጨማሪ ጊዜ ይፈቀድ ወይም አይፈቀድ የሚለውን አከራክሮ ለመወሰን መዝገቡን ወደ ኋላ ሄጄ መመርመር አለብኝ፡፡ ነገር ግን ባለኝ አጭር ጊዜ ውስጥ ልመረምር አልቻልኩም፡፡ በመሆኑም ጉዳዩን ሲከታተል የነበረው  ችሎት ነሐሴ 23 ቀን 2005 ዓ.ም ሥራ ስለሚጀምር አከራክሮ ብይን ይሰጥበታል፡፡ እስከዚያው ድረስ ያለው ጊዜ መርማሪ ቡድኑ ከጠየቀው 14 ቀናት ላይ ታሳቢ ይሆናል፤” በማለት ለነሐሴ 23 ቀን 2005 ዓ.ም ቀጥሮ ነበር፡፡

ከሰባት ቀናት በኋላ ነሐሴ 23 ቀን 2005 ዓ.ም መደበኛ ችሎቱ ተሰይሞ የኮሚሽኑ መርማሪ ቡድን ቀደም ብሎ በጠየቀው የ14 ቀናት ተጨማሪ ጊዜ ላይ ከተጠርጣሪዎቹ ጋር አወያይቶ ብይን እንደሚሰጥ ሲጠበቅ፣ የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ችሎት ቀርቦ ጉዳዩን ሲከታተለው ለነበረው ችሎት ክስ መመሥረቱንና በሌላ ችሎት እንደሚታዩ ገለጸ፡፡  የተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች ክስ ከተመሠረተባቸው በዕለቱ ማለትም ነሐሴ 23 ቀን 2005 ዓ.ም ክሱ እንዲነበብላቸውና የደንበኞቻቸው የመብት ጉዳይ እንዲታይላቸው፣  ወይም ያለውን ሁኔታ አውቀውት እንዲሄዱ ጉዳዩን ሲከታተል ለነበረው ችሎት አቤቱታ አቅርበውታል፡፡ ችሎቱ ክሱን አንብቦና ቀጠሮ ሰጥቶ የጊዜ ቀጠሮ ፋይሉን ለመዝጋት እንዲያመቸው  የክስ መዝገቡ እንዲቀርብ ጠይቋል፡፡

ክሱ ከሰዓት በኋላ እንደሚቀርብ ለችሎቱ የተነገረ ቢሆንም፣ ሳይቀርብ በመቅረቱ ችሎቱ ስለተጠርጣሪዎቹ ምንም ሳይል ተጠርጣሪዎቹ ባሉበት ቆይተው ለነሐሴ 24 ቀን 2005 ዓ.ም እንዲቀርቡ አዟል፡፡

የተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች፣ “ደንበኞቻችን መብታቸው ታልፎ ያለምንም ምክንያትና ከሕጉ ሥነ ሥርዓት ውጭ እንዴት ባሉበት ይቆዩ ይባላል፤” በማለት ጥያቄ ሲያነሱ፣ ለነሐሴ 24 ቀን 2005 ዓ.ም ቀርበው ክሱ እንደሚነበብላቸው በመግለጽ የዕለቱ ችሎት ሲጠናቀቅ  ሁሉም በሁኔታው ግራ በመጋባት  ተመልሰዋል፡፡

የጊዜ ቀጠሮ ሲሰጥ የከረመው ችሎት ክስ ተመሥርቶባቸዋል የተባሉትን ተጠርጣሪዎች ለነሐሴ 24 ቀን 2005 ዓ.ም ከመቅጠሩና መዝገቡን ከመዘጋቱ በፊት በእነጥጋቡ ግደይ  ምርመራ መዝገብ የነበሩት የባለሥልጣኑ ሠራተኞች አቶ ምሳሌ ወልደሥላሴ፣ ንጉሤ ክብረት እንዲሁም በእነ አምባው ሰገድ አብርሃ የምርመራ መዝገብ አቶ ጌታቸው አጐናፍር በነፃ መሰናበታቸውን የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ እንዳስታወቀው ገልጿል፡፡ በሌላ የምርመራ መዝገብ ደግሞ በአቶ ምሕረተአብ አብርሃ፣ በአቶ በእግዚአብሄር አለበልና በአቶ ፍፁም ገብረ መድኅን ላይ ምርመራ እንደሚቀረው የኮሚሽኑ መርማሪ ቡድን መግለጹንና የ14 ቀናት ተጨማሪ ጊዜ መጠየቁንም ችሎቱ አስታውቋል፡፡

አብረው ተጠርጥረው የታሰሩት ጥቂቶቹ በነፃና በዋስ ሲለቀቁ፣ በቀሪዎቹ 45 ተጠርጣሪዎች ላይ ደግሞ ክስ መመሥረቱ ሲነገር፣ በእሳቸው ላይ ቀሪ ምርመራ መኖሩ ተገልጾ 14 ቀናት የተጠየቀባቸው አርክቴክት በእግዚአብሔር ለችሎቱ ባቀረቡት አቤቱታ፣ “እኔ የዶክትሬት ተማሪ ነኝ፤  ደላላ አይደለሁም፡፡ 104 ቀናት ታስሪያለሁ፡፡ በከተማው ውስጥ የሚታዩትን አብዛኞቹን ሕንፃዎች የገነባሁት እኔ ነኝ፡፡ ብዙ ኩባንያዎችንም አቋቁሜያለሁ፡፡ ድርጅቶቼም ተመርምረዋል፡፡ ልማታዊ ነኝ እኔ ምን ልሁን? በዋስ ልውጣና ትምህርቴን ልከታተል፤” በማለት ችሎቱን ጠይቀዋል፡፡ ሌላው በኦሮሚያ ልዩ ዞን ሲሠሩ ምንጩ ያልታወቀ ሀብት በማከማቸትና በሌሎች  የወንጀል ድርጊቶች ተጠርጥረው ታስረው የነበሩ አቶ ሙሴ ጋሻው የተጠረጠሩበት የወንጀል ጉዳይ ወደ ኦሮሚያ የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ተዘዋውሮ እንዲታይ ትዕዛዝ ተሰጥቷል፡፡

ነሐሴ 24 ቀን 2005 ዓ.ም ክስ ተመሥርቶባቸዋል የተባሉት አቶ መላኩ ፈንታና አቶ ገብረዋህድ ወልደጊዎርጊስን ጨምሮ 45 ተጠርጣሪዎች ችሎት የቀረቡ ቢሆንም፣ ዳኞች ስላልተሟሉ ክሱ ሳይነበብላቸውና ሳይሰጣቸው ቀርቷል፡፡

በአጠቃላይ በ45 ተጠርጣሪዎች ላይ ክስ መመሥረቱን የኮሚሽኑ ተወካይ ጽሕፈት ቤት ቀርቦ አስረድቷል፡፡

በጽሕፈት ቤት ተጠርጣሪዎቹን በማስቀረብ ጊዜ ቀጠሮ ብቻ የሰጡት ዳኛ አቶ  አቦሃይ ጓዴ ሲሆኑ፣ አብዛኛዎቹን ተጠርጣሪዎች ለጥቅምት 11 ቀን 2006 ዓ.ም በመቅጠር እስከዚያው በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ አዘዋል፡፡ ሁለት መዝገቦችን ደግሞ ለጥቅምት 12 ቀን 2006 ዓ.ም ቀጥረዋል፡፡

በተሻሻለው የፀረ ሙስና ልዩ የሥነ ሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ቁጥር 434 መሠረት በተጠርጣሪዎቹ ላይ የሚካሄደው ምርመራ መጠናቀቅ ሲገባው፣ የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር 38ሐን በመጥቀስ ወደ መርማሪ ቡድኑ መመለሱ፣ ተገቢ አለመሆኑን የተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች ከመግለጻቸውም በተጨማሪ፣ ዓቃቤ ሕግ ክስ ማቅረቡን ከገለጸ ክሱ ተነቦላቸው በመብቶቻቸው ላይ ከተከራከሩ በኋላ ብይን መስጠት ተገቢና የሕጉ አሠራር ቢሆንም፣ በደንበኞቻቸው ላይ የተፈጸመው ግን ያላግባብና ከፕሮሲጀሩ ውጭ በመሆኑ አግባብ አለመሆኑን ጠበቆቹ ተናግረዋል፡፡ ጠበቆቹ ክሱ ለደንበኞቻቸው እንዲደርሳቸው ችሎቱን ሲጠይቁ፣ ፍርድ ቤቱ ከኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ጋር ተነጋግሮ በጽሕፈት ቤት በኩል እንዲደርሳቸው እንደሚያደርግ  በመግለጽ ችሎቱ አብቅቷል፡፡

የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ክስ ከመሠረተባቸው 45 ተጠርጣሪዎች መካከል አቶ መላኩ ፈንታ፣ አቶ ገብረዋህድ ወልደጊዮርጊስ፣ አቶ ነጋ ገብረ እግዚአብሔር፣ አቶ ከተማ ከበደ፣ አቶ ስማቸው ከበደ፣ ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ፣ ኮሎኔል ሃይማኖት ተስፋዬ፣  አቶ ያዴሳ ሚደቅሳ፣ አቶ እሸቱ ግረፍ፣ አቶ በላቸው በየነ፣ አቶ ጥሩነህ በርታ ይገኙበታል፡፡ የኦዲት ምርመራ ያላጠናቀቁ በፖሊስ ማረፊያ ቤት እንዲቆዩ ታዟል፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Law Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule