• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የገዱ አንዳርጋቸው ፈተና

December 22, 2017 03:27 pm by Editor Leave a Comment

በህወሓት ተመልምለውና ለሥልጣን በቅተው ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ “የለውጥ ኃይል” እየተባሉ ከሚወደሱት መካከል አንዱ የሆነው ገዱ አንዳርጋቸው ለምስክርነት መጥሪያ ተቆርጦለታል። ገዱና ሌሎች ህወሓት እንደ ጭቃ ጠፍጥፎ የሠራው ብአዴን አባላት የተጠሩት በነ ንግሥት ይርጋ ክስ በመከላከያ ምስክርነት ነው።

ህዝባዊ ዓመጹ የተነሳው “በመልካም አስተዳደር ችግር” ምክንያት እንደነበር እነ ገዱ በተደጋጋሚ በየሚዲያው ሲናገሩ ቆይተዋል። ዓቃቤሕግ ደግሞ ክሱን የመሠረተው ሕዝባዊ ዓመጹን ከ“ሽብር” ጋር በማገናኘት ነው። በ“ለውጥ ኃይልነት” ሲወደስ የነበረው ገዱ አንዳርጋቸው ታማኝነቱ ለማን እንደሆነ በይፋ የሚያሳይበት ፈታኝ ወቅት ላይ የሚገኝ ሲሆን አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች “አንገቱ ላይ ያለውን ገመድ ለማጥበቅ በህወሓት የታቀደ ሤራ ነው” ብለውታል። በተለይ ሃይለማርያም ደሳለኝ እና ደመቀ መኮንን በመከላከያ ምስክርነት ተቶጥረው መጥሪያ ሳይቆረጥላቸው መቅረቱ ጉዳዩን ልዩ ትኩረት አሰጥቶታል።

ጌታቸው ሽፈራው በፌስቡክ ገጹ በዘገበው መሠረት፤ “ምስክሮቹ ለታህሳስ 12/2010 ዓም ቀርበው እንዲመሰክሩ ትዕዛዝ ተፅፎ የነበር ቢሆንም መጥሪያው ዘግይቶ በመውጣቱ አልደረሳቸውም። ታህሳስ 12/2010 ዓም ተከሳሾቹ ተነጣጥለን ወደ ችሎት አንገባም በማለታቸው ጉዳዩ ሳይታይ ቀርቷል።” ፈተናው ግን ሳይታይ የሚቀር አልሆነም።

የጌታቸው ሽፈራው በሙሉ ዘገባ እንዲህ ይነበባል፤

የአማራ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው፣ የሰሜን ጎንደር ዞን አስተዳደር አቶ ሙሉጌታ ወርቁ፣ የጎንደር ከንቲባ አቶ ተቀባ ተባባል እና ስለ ህዝባዊ አመፁ ማስረዳት ይችላሉ የተባሉ ባለስልጣናት እና የፖሊስ አዛዦች በእነ ንግስት ይርጋ ተፈራ ክስ መዝገብ ስር ለተከሰሱት 6 ግለሰቦች የመከላከያ ምስክር ሆነው (ታህሳስ 12፤ 2010) እንዲቀርቡ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት አዟል።

ባለስልጣናቱ ህዝባዊ አመፁ በመልካም አስተዳደር ችግር የተነሳ ግጭት እንደሆነ በተለያዩ ጊዜያት በሚዲያ ቀርበው ያስረዱ ሲሆን ዐቃቤ ሕግ ህዝባዊ አመፁን ከ”ሽብር” ወንጀል ጋር በማገናኘት ተከሳሾቹ ላይ የ”ሽብር” ክስ መስርቶባቸዋል።

በተጨማሪም ተከሳሾች ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንንም በመከላከያ ምስክርነት የቆጠሩ ሲሆን የሁለቱ ባለስልጣናት መጥሪያ አልወጣም ተብሏል።

በእነ ንግስት ይርጋ የክስ መዝገብ ስር የተከሰሱት ንግስት ይርጋ ተፈራ፣ አለምነህ ዋሴ ገ/ማርያም፣ ቴዎድሮስ ተላይ ቁሜ፣ አወቀ አባተ ገበየሁ፣ በላይነህ አለምነህ አበጀ እና ያሬድ ግርማ ኃይሌ ናቸው።

ተከሳሾቹ በምርመራ ወቅት በህዝባዊ አመፁ እጃቸው እንዳለበት እና የ”ሽብር ወንጀል” ፈፅመናል ብለው በሀሰት እንዲያምኑ ለማድረግ የሰብአዊ መብት ጥሰት እንደደረሰባቸው ሲገልፁ የቆዩ ሲሆን 1ኛ ተከሳሽ ንግስት ይርጋ ጥፍሮቿ እንደተነቀሉ በክስ መቃወሚያዋ ላይ ተገልፆአል። ሌሎች ተከሳሾችም ያልፈፀሙትን ፈፅማችሁታል ተብለው በደል እንደደረሰባቸው መግለፃቸው ይታወሳል።

ከባለስልጣናት ባሻገር የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች፣ ጋዜጠኞች፣ ፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም፣ ዶ/ር ያዕቆብ ኃይለማርያም እና ሌሎች ምሁራንም በተከሳሾቹ በመከላከያ ምስክርነት ተቆጥረዋል። ምስክሮቹ ለታህሳስ 12/2010 ዓም ቀርበው እንዲመሰክሩ ትዕዛዝ ተፅፎ የነበር ቢሆንም መጥሪያው ዘግይቶ በመውጣቱ አልደረሳቸውም። ታህሳስ 12/2010 ዓም ተከሳሾቹ ተነጣጥለን ወደ ችሎት አንገባም በማለታቸው ጉዳዩ ሳይታይ ቀርቷል።

ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Law, Politics Tagged With: andm, eprdf, Full Width Top, gedu, Middle Column, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule