በአንድ ጊዜ 8ሺ ሰው በአንድ ቀን ደግሞ እስከ 40ሺ ሰው የሚስተናገድበት ትልቅ የድግስ አዳራሽ በአዲስ አበባ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ከ120 አመት በፊት ሲሠራ የነበረው የምህንድስና፣ ቅርጽና ይዘት፣ የመንግሥታዊ ድግሡ ታዳሚዎች ማንነትና የግብሩ ሥርአት፣ “ቀድሞም ጠቢብ ነበር ሰለሞን አባቱምኒልክ ይበልጣል ሰው ይዞ መብላቱ” ዳግማዊ ምኒልክ ሰዉ ሁሉ አንድ ጊዜ ተሰብስቦ የሚበላበትን ትልቅ አዳራሽ ለመስራት በመወሰን፣ በ1889 ዓ.ም ክረምቱን መናገሻ ወርደው እንጨት ሲያስጠርቡ ከረሙ፡፡ ወታደሩም በድግስ ጊዜ ሜዳ ላይ ሆነን ጸሀይና ዝናብ እንዳይመታን ለኛ ብለው አይደለምን በማለት ደስ ተሰኘ፡፡ ላዳራሹ የሚያስፈልገውን 4 ማዕዘን፣ ሳንቃና እንጨትም ላሊ እየወጣና እየዘፈነ ማመላለስ ጀመረ፡፡ በ1890 ዓ.ም በዘመነ ማርቆስ ዳግማዊ ምኒልክ ከአውሮፓ መሀንዲሶችን … [Read more...] about የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ
Archives for October 2023
የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ
በ116ኛው የሠራዊት ቀን ሲከበር ንግግር ያደረጉት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ “ዐጼ ምኒልክ የጦር ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት ያቋቋሙበትን ቀን የሀገር መከላከያ ሠራዊት ቀን ኾኖ እንዲከበር ተደርጓል” በማለት ቀኑ ለምን እንደተመረጠ ይፋ አደረጉ። ከዚህ ሌላ ፊልድ ማርሻሉ በንግግራቸው፤ ሉዓላዊነቷ ተጠብቆ ከጀግኖች የተረከብናትን ኢትዮጵያ እንደተከበረች እና ማንነቷ እንደተጠበቀ ለማስቀጠል ወታደራዊ ዝግጁነታችንን አሳድገንና ቁመናችንን አዘምነን ማንኛውንም ተልዕኮ በላቀ ብቃት ለመፈጸም ሠራዊቱ ዝግጁ መሆኑን አሣውቀዋል። የሠራዊቱ አባላት የተሠጣቸውን ታላቅ አደራ በድል ለመወጣት የመፈጸም ብቃታቸውን በማሣደግ በዓላማ ጽናታቸው እንዲቀጥሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ አሳስበዋል፡፡ ሠራዊቱ ሀገሩን እና ህገ መንግስታዊ ሥርዓቱን … [Read more...] about የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ
ጥቅምት 15 ለምን?
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ቀን በአዲስ መልክ ጥቅምት 15 ቀን ላይ መከበሩ ለምን እንደሆነ ከዚህ በታች ለመረዳት እንዲቻል በቀላሉ የተሠራውን መግለጫ ይመልከቱ። ስለ ጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት የማዕረግ ምልክቶች ምን ያህል ያውቃሉ? ከ"ፊልድ ማርሻል ጄነራል" ጀምሮ እስከ "ምክትል አስር ዓለቃ" ድረስ በአጠቃላይ 18 ማዕረጎች ይገኛሉ። የማዕረጎቹን ዝርዝር ከነምልክቱ እነሆ፦ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about ጥቅምት 15 ለምን?
“በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት”
"በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት " በሚል መሪ ቃል ለሚከበረው ለዘንድሮ ለ116ኛው የሠራዊት ቀን እንኳን በሠላም አደረሳችሁ አደረሰን። እንደሚታወቀው ኢትዮጵያ የረዥም ዓመታት ሀገርን ከጠላት የመከላከል የተጋድሎ ታሪክ ካላቸው ሀገራት መካከል በጀግኖች ልጆቿ የአይበገሬነት ፊት የምትሠለፍ ታሪካዊት ሀገር ናት። ከቀደመው ዘመን ጀምረን አሁን ላይ ያለውን እውነታ እንኳ ብንቃኝ ኢትዮጵያ በርካታ የውጪ ወራሪ ሀገራት ያሠፈሠፉባት ጥቂት የማይባሉ የውስጥ እርስ በርስ ግጭቶች የተከሰቱባት በባንዳዎች የተፈተነችበትና በየትኛውም ዘመን ያልተንበረከከች የወራሪዎችን ፈተና አልፋ ዛሬ ላይ የደረሠች ሥለመሆኗ የታሪክ ድርሳናት መዝግቧል። በሀገራችን የጀግንነት የታሪክ መዝገብ ያልሠፈሩ ግን ደግሞ አለም ያወቃቸው ቱባ ባህሎችና ድንቅ ታሪኮች ያላት ኢትዮጵያ በታሪክ … [Read more...] about “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት”
“ውትድርና ሕይወቴ ነው”
ኢትዮጵያዊያን በሀገራችው ሰማይ ስር የመጣን ጠላት በማሽመድመድ ካስመዘገቡት ደማቅ ታሪክ ፊት ለፊት ትልቁን ድርሻ ከሚወስዱት አንዱ ናቸው። ለሀገራቸው በዋሉት ውለታ ከሚተረክላቸው ቀዳሚ ባለ ታሪኮች ቀድመው ይጠቀሳሉ። ሙሉ ህይወታቸውን ለሀገራቸው የሰጡ ናቸው። ጀግና ተዋጊ፣ የበቁ የጦር መሪ፣ የተሳካላቸው የጦር አዛዥ ሆነው አገልግለዋል። በበርካታ የጦር ሜዳ ውጊያዎች ተሳትፈው የሀገርን ሉዓላዊነት፣ የህዝብን ነፃነት ያስከበረ ደማቅ ድል አስመዝግበዋል። ብርጋዲየር ጄኔራል ተስፋዬ ሃብተማርያም። ጄኔራል መኮንኑ በ1934 ዓ.ም በጉራጌ ዞን ከቸሀ ወረዳ 20 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ሲሰ መንደር ተወለዱ። የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውንም እዚያው እምድብር ከተማ ተምረው በ1948 ዓመተ ምህረትም አጠናቀዋል። ከ1949-1952 ዓ.ም ድረስ አምቦ የእርሻ ልማት … [Read more...] about “ውትድርና ሕይወቴ ነው”
መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው
አየር ኃይል የኢትዮጵያ አየር ኃይልን በሁሉም መስክ የኢትዮጵያን ታላቅነት የሚመጥን አስተማማኝና ዘመናዊ አየር ኃይል የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል። በተለይም ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ አየር ኃይሉ በሁሉም ረገድ በመዘመንና ስኬታማ በመሆን ሀገር የምትኮራበት ታላቅ ተቋም መሆኑንም ገልፀዋል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል አሁን ላይ በውጊያ መሠረተ-ልማት፣ በሰው ኃይል ግንባታ፣ በቴክኖሎጂ ፈጠራና አጠቃቀም በአጭር ጊዜ ተጨባጭ ውጤቶችን ማስመዝገቡን በተቋሙ የተለያዩ ዲፓርትመንት ኃላፊዎች ተናግረዋል። የኢትዮጵያ አየር ኃይል አስተማማኝ የሀገር መከታ በመሆን ለየትኛውም ግዳጅ አፈጻጸም ብቁና ዝግጁ መሆኑንም አረጋግጠዋል። በመሆኑም የኢትዮጵያ አየር ኃይልን በሁሉም መስክ የኢትዮጵያን ታላቅነት የሚመጥን ዘመናዊ ተቋም የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል። በአየር ኃይል … [Read more...] about መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው
“ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ለፓርላማ በሰጡት ማብራሪያ፤ የተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምደባ በአግባቡ እንደሚሰራበት አመልክተዋል። "በምንም አይነትና መስፈርት አግባብ የሌለውና አድሎ ላይ የተመሰረተ ምደባ አይኖርም" ሲሉ ተናግረዋል። "እያንዳንዱ ተማሪ በጠየቀው በችሎታው፣ በሚገባው ቦታ እንዲመደብ እናደርጋል" ያሉት ሚኒስትሩ "አንድና ብቸኛው ከዛ የምንወጣበት አስቸኳይ የሆነና ቅርብ የሆነ ክትትል የሚያስፈልጋቸው የህክምና ጉዳይ ሲኖር ነው" ብለዋል። "የህክምና ኬዞችንም ስንመለከት ከዶክተር ወረቀት ማምጣት ብቻ ሳይሆን በቦርድ ደረጃ ተነጋግረውበት ያ የህክምና ጉዳይ ሌላ ቦታ ሄዶ ለመማር የማያስችል ነው፤ ለህይወቱ/ቷ አስቸጋሪ ነገር ያመጣል ከተባለ ብቻና ብቻ ነው" ሲሉ አስገንዝበዋል። የትምህርት ሚኒስትሩ ፤ "ለአንድ የመንግሥት ባለስልጣን ፣ አንድ የምክር … [Read more...] about “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ
42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ታሰሩ
የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ታምሩ ገምበታን ጨምሮ ቁጥራቸው ለጊዜው ያልታወቁ ሰዎች በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው መታሰራቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት ሰሞኑን መሆኑንና አቶ ታምሩ ገምበታ ግን ጥቅምት 5 ቀን 2016 ዓ.ም. መሆኑ ተገልጿል። የምክትል ዳይሬክተሩ ቤት በፍርድ ቤት የብርበራ ፈቃድ መበርበሩንና ዛሬ ጥቅምት 7 ቀን 2015 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ሊቀርቡ እንደሚችሉ ተጠቁሟል፡፡ የመንግሥት አስተዳደር ለውጥ ከተደረገ ጀምሮ የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ አገልግሎት ተቋም ውስጥ የተለያዩ ለውጦች (ሪፎርም) የተደረገ ቢሆንም፣ አንዳንድ የተቋሙ ሠራተኞች በድለላ ሥራ የተሰማሩ አካላት ጋር በመመሳጠር የሙስና ወንጀል ፈጽመዋል ተብለው በቁጥጥር ሥር ውለው በምርመራ ላይ እንዳሉም … [Read more...] about 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ታሰሩ
በተማሪዎች ፈተና ውጤት ለታየው ውድቀት ትምህርት ሚ/ር ኃላፊ መሆን አለበት ተባለ
የትምህርት ሚኒስቴር ለ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ዝቅተኛ ውጤት መመዝገብ ምክንያት የሆኑ ችግሮችን በጥናት ለይቶ እንዲያቀርብ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰዉ ኃብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጠየቀ። በይህ የተጠየቀው በምክር ቤቱ የሰዉ ኃብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የትምህርት ሚኒስቴርን የ2016 እቅድና የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የሥራ አፈፃፀም ዛሬ ሲገመግም ነው። በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ " ቀደም ሲል ሲሰጡ የነበሩ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤቶች የተማሪዎችን ትክክለኛ ችሎታ ያሳዩ አልነበሩም" ብለዋል። የፈተና አሰጣጡን በመቀየር የተመዘገበው የተማሪዎች ውጤት በዘርፉ ከዚህ ቀደም የነበሩ ችግሮች ማሳያ መሆናቸውን ጠቁመው ለዚህም ከወላጆች ጀምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተጠያቂ … [Read more...] about በተማሪዎች ፈተና ውጤት ለታየው ውድቀት ትምህርት ሚ/ር ኃላፊ መሆን አለበት ተባለ
ቀይ ባሕር እና ዓባይ “የኅልውና ጉዳይ ናቸው”፤ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል”
የዓባይ አጀንዳ ሲቋጭ የቀይ ባህር ጉዳይ መነሳቱ አጀንዳው እጅግ ተደርጎ የታሰበበት ለመሆኑ ማሳያ ተደርጓል። “የቀይባህር አጀንዳ ሃሳብ ማስቀየሪያ ነው” በማለት ለፕሮፓጋንዳ የሚነሱ የማይሳካላቸው በዚሁ መነሻ እንደሆነም ተመልክቷል። እጅግ ሰላማዊ በሆነና በሰጥቶ መቀበል መርህ አማራጮችን አቅርበው ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤት መሆን እንዳለባት ያመለክቱት ዐቢይ ቀይ ባሕር “ጉዳይ የኅልውና ነው” ብለውታል። የወንበዴው መሪ መለስ ዜናዊ “መንገዱን ጨርቅ ያድርግላችሁ” ሲል አሰብ ወደብና ቀይ ባህርን አስመልክቶ ለተከራከሩ የሰጠው መልስ ነበር። ኢትዮጵያን የሚያክል አገር የተቆለፈባት እንድትሆን የተስማማው ትህነግ፣ ላለፉት ሠላሳ ዓመታት ኢትዮጵያ አንጡራ ሃብቷን እንድትበትን ፈርዶባት ኖሯል። የድርጅቱ መሪ መለስ “አሰብን ከኢትዮጵያ ከመውሰድ ከኤርትራ መቀማት ይቀላል” በሚል ሥጋት … [Read more...] about ቀይ ባሕር እና ዓባይ “የኅልውና ጉዳይ ናቸው”፤ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል”