• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው

October 20, 2023 05:07 pm by Editor 1 Comment

አየር ኃይል

የኢትዮጵያ አየር ኃይልን በሁሉም መስክ የኢትዮጵያን ታላቅነት የሚመጥን አስተማማኝና ዘመናዊ አየር ኃይል የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

በተለይም ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ አየር ኃይሉ በሁሉም ረገድ በመዘመንና ስኬታማ በመሆን ሀገር የምትኮራበት ታላቅ ተቋም መሆኑንም ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ አየር ኃይል አሁን ላይ በውጊያ መሠረተ-ልማት፣ በሰው ኃይል ግንባታ፣ በቴክኖሎጂ ፈጠራና አጠቃቀም በአጭር ጊዜ ተጨባጭ ውጤቶችን ማስመዝገቡን በተቋሙ የተለያዩ ዲፓርትመንት ኃላፊዎች ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ አየር ኃይል አስተማማኝ የሀገር መከታ በመሆን ለየትኛውም ግዳጅ አፈጻጸም ብቁና ዝግጁ መሆኑንም አረጋግጠዋል።

በመሆኑም የኢትዮጵያ አየር ኃይልን በሁሉም መስክ የኢትዮጵያን ታላቅነት የሚመጥን ዘመናዊ ተቋም የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል።

በአየር ኃይል አቪዬሽን ከባድ ጥገና ማዕከል የሮተሪ ዲፓርትመንት ዊንግ መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ኮሎኔል ኢንጂነር ሙሉቀን ደርሶ፤ አየር ኃይሉ የኢትዮጵያን ታላቅነት በሚመጥን መልኩ በሁሉም መስክ በዘመናዊ መልኩ እየተገነባ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በአየር ኃይሉ ለውጊያ፣ መለማመጃና ለትራንስፖርት አገልግሎት የሚውሉ አውሮፕላኖችን አስተማማኝ እድሳትና ጥገና በማድረግ ላይ ስለመሆኑም አንስተዋል።

በአየር ኃይሉ ቀደም ሲል የነበሩ አውሮፕላኖችን ከአናሎግ ወደ ዲጂታል የማሻሻያ ሥራ በማከናወን የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጡ እየተደረገ መሆኑንም አብራርተዋል።

የአየር ኃይል የከባድ ጥገና ማዕከል የምርምር እና ልማት ክፍል ኃላፊ ሌተናል ኮሎኔል ወንድማገኝ አርዓያ፤ በቴክኖሎጂ አጠቃቀምና በማሻሻያ ሥራዎች ስኬታማ መሆኑን ገልፀዋል።

በከባድ የጥገና ማዕከል አውሮፕላኖችን የማዘመን፣ የዕይታና ዒላማ አቅማቸውን የማጎልበት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በዚህም አየር ኃይሉ ያወጣ የነበረውን የውጭ ምንዛሬ ማስቀረት መቻሉን ገልጸው፤ በቀጣይም ተጨማሪ ገቢዎችን ለማስገኘት እንሰራለን ብለዋል፡፡

በአየር ኃይል የአቪዬሽን ጥገና ማዕከል መምሪያ ኃላፊ ኮሎኔል ደረጄ አስታጥቄ፤ አየር ኃይል የውጊያ መሠረተ-ልማቶችን በመገንባት ያከናወናቸው ተግባራት ግዳጆችን በአስተማማኝ ብቃት መወጣት የሚያስችሉ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡

በአየር ኃይሉ የትራንስፖርት ሄሊኮፕተር ጥገና ስኳድሮን ኃላፊ ሻለቃ አንድነት ብርሃኑ በበኩላቸው፤ አገራዊ ለውጡን ተከትሎ በአየር ኃይሉ በርካታ አመርቂ ሥራዎች ስለመከናወናቸው አብራርተዋል።

በአየር ኃይሉ የሄሊኮፕተር አብራሪዎቹ ሌተናል ኮሎኔል አየለ ዳዊት እና ሻለቃ ፀጋዬ አሰፋ ፤ አየር ኃይሉ አሁን ላይ በቴክኖሎጂ አጠቃቀምም ይሁን በግዳጅ አፈጻጸም አስተማማኝ ቁመና ላይ ይገኛል ብለዋል።

በአስቸኳይ ተልዕኮና ግዳጅ በቀንም ይሁን በሌሊት በመብረር ያሰብነውን ማሳካት የሚያስችል ቁመና ላይ እንገኛለንም ነው ያሉት።

እስከ 122 ሚ.ሜ ድረስ ያሉ የሮኬት ተተኳሾችን የሚያመርተው መከላከያ ኢንጂነሪንግ

የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ቢሾፍቱ በሚገኘው የሞተር ቬሂክልስ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ተገኝተው በመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን የተከናወኑ የፈጠራ፣ የምርምር ውጤቶችን እና ምርቶችን ተመልክተዋል።

የመከላከያ ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን እንደ አዲስ ከተደራጀ 2012 ዓ.ም ጀምሮ ነባር እና አዲስ ኢንዱስትሪዎችን በመያዝ የተለያዩ የአርማመንት ቴክኖሎጂ ውጤቶችን የማምረት እና የማዘመን፤ የቀላል እና የመካከለኛ መሣሪያ ተተኳሾችን እንዲሁም እስከ 122 ሚ.ሜ ድረስ ያሉ የሮኬት ተተኳሾችን ያመርታል።

ኮርፖሬሽኑ BRDM-2 ፣ PTR -60ብረት ለበስ ተሽከርካሪዎችን፣ T-55 እና T-72 ታንኮችን የመጠገን፣ የማደስ እና ኦቨር ሆል የማድረግ አቅም የገነባ ሲሆን በተጨማሪም የመከላከያ ሠራዊታችንን የማድረግ አቅም በከፍተኛ ደረጃ የሚያሳድጉ የምርምር እና የፈጠራ ስራዎችን ያከናውናል።

የትጥቅ ዝግጁነትና ሎጅስቲክስ

የመከላከያ ሰራዊት የሪፎርም ስራ በሁሉም መስክ የላቀ ውጤት እየተመዘገበበት መሆኑን የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገለጹ።

የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፤ የመከላከያ ሎጅስቲክስ ዋና መምሪያ የዝግጁነት አቅምና የሥራ እንቅስቃሴን ጎብኝተዋል።

በዚሁ ወቅት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፤ በኢትዮጵያ የትጥቅ ዝግጁነትና ዘመናዊ ጦር የማቋቋም ስራ በሂደት ቀጥሎ ዛሬ ላይ በእጅጉ መዘመኑን ገልጸዋል።

በመሆኑም ከዛሬ 116 ዓመት በፊት ዘመናዊ ሰራዊት ለማቋቋም የተደረገውን ጥረት መነሻ በማድረግ የሰራዊት ቀን መከበር መጀመሩን አንስተው ዘንድሮም በተለያዩ ዝግጅቶች ይከበራል ብለዋል።

የኢትዮጵያንና የሰራዊቱን ታሪክ በማጥናት የሰራዊቱ ቀን ታሪኩን በሚመጥን መልኩ በድምቀት የሚከበር መሆኑን ገልጸዋል።

በመከላከያ ሎጅስቲክስ መምሪያ የተሰሩ ፈጠራና የዝግጁነት ሥራዎችም የሰራዊቱን አቅም የሚያጎለብቱና ለሰራዊቱ ቀን ልዩ ድምቀት የሚሰጡ ናቸው ብለዋል።

ባለፉት አራት ዓመታት የአገር መከላከያ ሰራዊትን አቅም ማጎልበት ያስቻለ ተቋማዊ የለውጥ ስራ ተከናውኖ የላቀ ውጤት መመዝገቡንም አንስተዋል።

የአየር ኃይል፣ ሎጅስቲክስ መምሪያ፣ መከላከያ ኢንዱስትሪና መከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ ሪፎርሙን ተከትሎ እምርታዊ ለውጥ አምጥተዋል ብለዋል።

በመሆኑም አሁን ላይ በአስተማማኝ መልኩ ግዳጅ መፈፀም የሚችል ዘመናዊና የሀገር አለኝታ የሆነ ሰራዊት ተገንብቷል ብለዋል።

የመከላከያ ሎጅስቲክስ ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጄነራል አብዱራህማን እስማኤል፣ የሰራዊቱን የግዳጅ አፈፃጸም ውጤታማነት የማስቀጠል ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል። (ኢዜአ እና የመከላከያ ቴሌግራም ገጽ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: endf, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Comments

  1. Abebe says

    October 20, 2023 05:48 pm at 5:48 pm

    Ye Oromo Mekelakeya Bel Ethiopia Dersha Yelatem Ethiopuanema Eyewegwat New Afar Amara Gurage Eelayeta Ethiopiawiyan Nachew Eyetegodum New Yemiwegachewm Oromuma Yetebalew New .Mekelakeya Atibel

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule