• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ

October 30, 2023 10:27 am by Editor Leave a Comment

በአንድ ጊዜ 8ሺ ሰው በአንድ ቀን ደግሞ እስከ 40ሺ ሰው የሚስተናገድበት ትልቅ የድግስ አዳራሽ በአዲስ አበባ በዳግማዊ አጼ ምኒልክ ከ120 አመት በፊት ሲሠራ የነበረው የምህንድስና፣ ቅርጽና ይዘት፣

የመንግሥታዊ ድግሡ ታዳሚዎች ማንነትና የግብሩ ሥርአት፣

“ቀድሞም ጠቢብ ነበር ሰለሞን አባቱ
ምኒልክ ይበልጣል ሰው ይዞ መብላቱ”

ዳግማዊ ምኒልክ ሰዉ ሁሉ አንድ ጊዜ ተሰብስቦ የሚበላበትን ትልቅ አዳራሽ ለመስራት በመወሰን፣ በ1889 ዓ.ም ክረምቱን መናገሻ ወርደው እንጨት ሲያስጠርቡ ከረሙ፡፡ ወታደሩም በድግስ ጊዜ ሜዳ ላይ ሆነን ጸሀይና ዝናብ እንዳይመታን ለኛ ብለው አይደለምን በማለት ደስ ተሰኘ፡፡ ላዳራሹ የሚያስፈልገውን 4 ማዕዘን፣ ሳንቃና እንጨትም ላሊ እየወጣና እየዘፈነ ማመላለስ ጀመረ፡፡

በ1890 ዓ.ም በዘመነ ማርቆስ ዳግማዊ ምኒልክ ከአውሮፓ መሀንዲሶችን በማስመጣት ውስጡ 1፣ ውቅሩ 3፣ ቁመቱ 120 ክንድ፣ ጎኑ ደግሞ 60 ክንድ የሆነ አዳራሽ አሰሩ፡፡ ይህም የሚበላበት ብቻ ነው፡፡ ለእንጀራ ለጠጅና ለስጋ ማቅረቢያ ደግሞ ለየብቻው ተሰራ፡፡ የእንጀራ ማቅረቢያው በስተደቡብ በኩል ቁመቱ 37 ክንድ ጎኑ 7 ክንድ፣ በሰሜን በኩል ያለውም እንደዚሁ ቁመቱ 37 ክንድ፣ ጎኑ ደግሞ 7 ክንድ ሆኖ ተሰራ፡፡

የሥጋውም ማቅረቢያ ቁመቱ 24 ክንድ ጎኑ 7 ክንድ ነው፡፡ የጠጁም ማቅረቢያ ጋንና ገንዳ ተተክሎበት አሳላፊዎች የሚቆሙበት በሰሜንና በደቡብ ቁመቱ እኩል 59፤59 ክንድ፣ ጎኑም እኩል 7፤7 ክንድ ሆኖ ተሰራ፡፡ ጠጅ የሚመላለስበት ገንዳም ቁመቱ እኩል በሰሜንና በደቡብ 7፤7 ክንድ ቁመቱም 2፤2 ክንድ ሆኖ ተሰራ፡፡ እያንዳንዱ የብረት ገንቦም 20፡20 ብርሌ የሚይዝ ሆኖ የብረቱ ገንቦ ባጠቃላይ በአንድ ጊዜ 700 ገንቦ/14000 ብርሌ ይይዛል፡፡

ግብር የሚበላበት አዳራሽ ጠጅ ቤትም ቁመቱ 92 ክንድ፣ ቁመቱ ደግሞ 20 ክንድ ነው፡፡ የማለፊያው ጠጅ ቤት ቁመት ደግሞ 50 ክንድ ሲሆን ጎኑም 14 ክንድ ነው፡፡ በገንዳው ግራና ቀኝ ባለመዘውር የብረት አሸንዳ የተተከለበት ሲሆን ግብር በሚበላበት ቀን ግራና ቀኝ ያለው አሸንዳ ካዳራሹ መካከል በትልቁ የብረት ድስት መዘውሩ እየተዘወረ ከድስቱ ላይ ሲፈስ፣ ከገደል የሚፈስ ትልቅ ውሃ ይመስላል፡፡

ባለ 3 ውቅር በሆነው አንድ ትልቅ አዳራሽ 3 ውቅር ቤቶች እያንዳንዱ ቤት ላይ 50፤50 ጉልላት አለበት፡፡ በእያንዳንዱ ውቅር ላይም የሰጎን እንቁላል ተደርጎበታል፡፡ በአዳራሹ ውስጥ የተሰቀለው ባለኤልክትሪክ ፋኖስ በበራ ጊዜ እንደ ጸሐይ ብርሀን አይን ይበዘብዛል፡፡ በምስራቅ በኩል በአረንጓዴ ብጫ ቀይ ሰማያዊና ብዙ ህብረ ቀለማት የተሸለመ ብርሀን የሚያስገባ ሶስት ባለመስታወት መስኮት ተሰርቶለታል፡፡

በምስራቅ፣ በምዕራብና በሰሜን ባሉት ታላቅ በሮች ላይም 2፡2 ባለመስታወት መስኮት አለው፡፡ በደቡብ በስጋ ማቅረቢያና ጠጅ ማሳለፊያ በኩልም 3 መስኮት አለው፡፡ በጓዳው በኩልም እጅግ ያማረ 5 ባለመስታወት መስኮት እንዲሁም ከማጠፊያና ማጠፊያው ላይ ደግሞ 4 ባለመስታወት መስኮት ተሰርቶለታል፡፡

መሃል ላይ 3ቱን ውቅሮች የሚደግፉ 34 አምዶች ቆመዋል፡፡ የአዳራሹ ግንብም ከውስጥና ከውጭ እንደ አምደ ወርቅ ሆኖ ተሰርቶ በብዙ ህብረ ቀለም በዕብነ በረድ እየተሸለመ ልዩ ልዩ በሆነ የወይን ሐረግ ተቀርጹዋል፡፡ ቅርጹም እጅግ ያማረ ነው፡፡

የአዳራሹ ስራ ሲጠናቀቅም ከባህር ማዶ የመጣ እንደወርቅ የሚያንጸባርቅ እጅግ ያማረ መንበረ ዳዊት ተተከለበት፣ በውስጡም ዘውድ ክዋክብትና ብዙ ያማሩ ነገሮች ተሰሩበት፡፡ ወርቅ በሚመስሉ አምዶች ላይም የእሳት ልሳን የመሰለ ባለወርቅ ዘርፍ ያለው መጋረጃ ተጋርዶበታል፡፡

ከጃንሆይ ምኒልክ ፊት ለፊት፣ ግራና ቀኝ፣ በአንዴ በግብር አዳራሹ በየማእረጉ የሚቀመጠውና በየጥጉ የሚቆመው ሰው 7987 ይሆናል፡፡ ይህም ሥጋ እንጀራና ጠጅ አሳላፊውን ሳይጨምር ነው፡፡ እነዚህ ደግሞ 380 ይሆናሉ፡፡ ፊት የገባው በልቶ ሲወጣ ቀጣዩ ደግሞ ምሽቱ እስኪያቋርጠው ድረስ ለ5 እና 6 ዙር እየገባ ይበላል፡፡

ጠጅ የሚመጣጠበት ኩባያ 3 ብርሌ ያክላል፡፡ ለግብር የሚመጣው ሰው ግብሩ እስኪዘጋጅ ድረስ ካዳራሹ በስተምዕራብ 200 ክንድ ርቆ ባለው ሜዳ ይሰበሰባል፡፡ ሰዉ ጨርሶ ከገባ በኋላ የገባው እንዳይወጣ፣ በልቶ የሚወጣውም ድጋሚ እንዳይደባለቅ አጋፋሪዎች ይቆልፉበታል፡፡ የገባው በልቶ ጠጥቶ ሲጨርስ በሰሜን በኩል ባለው ትልቅ በር ከሚገባው ጋር ሳይተያይ ይወጣል፡፡

ከአውሮፓ የመጣ 400 የሚሆን ታላላቅ የብረት መሶብ ከግብሩ አዳራሽ ከእንጀራ ማቅረቢያው ላይ ሳይነሳ ይቀመጣል፡፡ በግብር ቀን በአዳራሹ እየገባ የሚበላና የሚጠጣው ወታደር ብቻ አይደለም፡፡ ለጩኸት የመጣ ባላገር፣ እረኛ፣ የወታደር አሽከር፣ ባደባባይ የተገኘ ሁሉም ሰው እየገባ ያለከልካይ ይበላል ይጠጣል፡፡ አጋፋሪዎችም የማነህ አይሉትም፡፡

የምኒልክ ድግስ ሁል ጊዜ እንደጸና ተዘርግቶ የሚኖር በመሆኑ ለመግለጽ ያስቸግራል፡፡ አዛዦች በቀጭን ድርብ በአብደላከኒ ቀሚስ ባለወርቅ ጫማ ጎራዴ እየታጠቁ፣ አጋፋሪዎችና ዙፋን ቤቶችም እንደዚሁ እያጌጡ የእሳት ልሳን መስለው በአዳራሹ ይመላለሳሉ፡፡ የማር ጠጅ፣ የወይን ጠጅ፣ አረቄ፣ ሻምፓኝና ከውጭ አገር የመጡ ልዩ ልዩ መጠጦች ይቀርባሉ፡፡

በምኒልክ አዳራሻ ሁሉም ይጠግብበታል እንጂ ሰው አይመረጥበትም፡፡ ጠጅ፣ እንጀራና ሥጋ አሳላፊዎችም አፈጣጠናቸውና አካሄዳቸው አስገራሚ ነው፡፡ አንዱ ባንዱ ሲተላለፍ ሥጋ የያዘው ብርሌ የያዘውን፣ ዋንጫም የያዘው ሥጋ የያዘውን አይገፋውም፡፡ አስተናጋጆቹ ሳይገፋፉ እየተላለፉ ሲሾልኩ መላዕክት ይመስላሉ፡፡

በዚህ የተደነቀው አዝማሪም በአንዱ ቀን እንካ ተቀበል አለ፣

ቀድሞም ጠቢብ ነበር ሰለሞን አባቱ
ምኒልክ ይበልጣል ሰው ይዞ መብላቱ

ታሪክ ዘመን ዘ ዳግማዊ ምኒልክ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ፣ ከጸሓፌ ትዕዛዝ ገብረ ሥላሴ (ከ1837-1905 ዓ.ም ድረስ የኖሩ)፣ አርቲስቲክ  ማተሚያ ሊሚትድ 1959 ዓ.ም፣ ገጽ 278-284፣ 206-207

የፎቶ መግለጫ፣
– የተያያዘው ምስል የምኒልክ አዳራሽ አሁን ያለውን ይዘት የሚያሳይ ነው፡፡ ጠ/ሚኒስትሩም የ5ሚ ብር እራት እያበሉበት ነው፡፡

–  የምኒልክ የግብር አዳራሻ ከ110 አመት በፊት በ1900ዎቹ ዓ.ም መጀመሪያ የነበረውን ገጽታ የሚያሳይ ፎቶግራፍ፡፡ (@Sisay Tefera Mekonen)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Right Column, Social Tagged With: abiy ahmed, Meneliks Hall

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule