የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከኅብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማና ባደረገው ብርቱ ክትትል በህገ-ወጥ መንገድ ከ5.1 ቢሊዮን ብር (ከአምስት ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር) በላይ ሲያንቀሳቅስ የነበረ ግለሰብ ከ25 ግብረ-አበሮቹ ጋር በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራባቸው መሆኑን ገለፀ፡፡ ዜናውን የሰሙ “በነካ እጃችሁ ወኪሎቹ ጋር ጎራ በሉ” ሲሉ ተደምጠዋል። በወንጀሉ የተጠረጠረው ሳሙኤል እጓለ አለሙ በቅፅል ስሙ ሳሚ ዶላር የሚባል ሲሆን ነዋሪነቱን በአዲስ አበባ ከተማ በማድረግ ወደ አሜሪካን ሀገር በተደጋጋሚ የሚመላለስ የኤሌክትሪክ መሳሪያዎች፣ የቤት እና የቢሮ እቃዎችእንዲሁም ተዛማጅ መገልገያዎች የችርቻሮ ንግድ ፍቃድን ሽፋን በማድረግ ሕገ-ወጥ የውጭ ምንዛሬና በሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር ወንጀል ተጠርጥሮ በራሱና ዮዲት እጓለ አለሙ ከተባለች እህቱ ጋር በመሆን በስማቸው በተለያዩ ባንኮች … [Read more...] about ሳሚ ዶላር አንዱ ነው፤ ሌሎቹስ ዶላር አጣቢዎች? ምነው ዝም ተባሉ?
News
ዜና
አንድ ጣሳ ማሽላ በ250 ብር በሚሸጥበት አላማጣ ተከማችቶ የነበረ ከ3 ሺሕ ኩንታል በላይ የእርዳታ እህል ተገኘ
በአላማጣ ከተማ አሸባሪው ህወሓት ለታጣቂዎቹ አከማችቶት የነበረው ከ3 ሺሕ ኩንታል በላይ የእርዳታ እህል ተገኝቷል። አሸባሪውና ወራሪው የወያኔ ቡድን ለራያ አላማጣ ህዝብ የሚመጣውን የእርዳታ እህል ለህዝቡ ሳያደርስ ለታጣቂዎቹ ቀለብ እንዲውል በየ መጋዝኖቹ እና ወፍጮ ቤቶች አከማችቶት መገኘቱን ነው መረጃው ያመለከተው። ተከማችቶ የተገኘው የእርዳታ እህልም ከ2 ሺሕ 500 ኩንታል በላይ የዩ ኤስ አይዲ የተፈጨ የስንዴ ዱቄት፣ ከ400 ኩንታል በላይ ከረጢት የታሸገ ስንዴ፣ ከ100 ኩንታል በላይ ብስኩቶች እና ኃይል ሰጪ ምግቦች መሆኑም ተገልጿል። የሽብር ቡድኑ ካለፈው 1 ዓመት ከ4 ወር በላይ በሆነ ጊዜ ውስጥ ለሰብዓዊ እርዳታ እንዲውል የሚገባ የትኛውንም አይነት ድጋፍ ከህዝቡ እየነጠቀ ለታጣቂዎቹ ሲያከማችና ሲቀልብ እንደነበር የአላማጣ ከተማ ነዋሪዎች ምስክርነታቸውን … [Read more...] about አንድ ጣሳ ማሽላ በ250 ብር በሚሸጥበት አላማጣ ተከማችቶ የነበረ ከ3 ሺሕ ኩንታል በላይ የእርዳታ እህል ተገኘ
በአራዳ ክፍለ ከተማ ዜጎች የስፖርት ሜዳ አገኙ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ በአዲስ መልክ የተገነባውን የስፖርት ማዘውተሪያ ሥፍራ መርቀው ከፍተዋል። በተለምዶ "15 ሜዳ" ተብሎ የሚጠራው የስፖርት ማዘውተሪያ ሥፋራ ከዚህ ቀደም ለስፖርታዊ እንቅስቃሴ ምቹ እንዳልነበር ተጠቁሟል፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አነሳሽነት የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን በማሳተፍ በአዲስ መልኩ ተገንበቶ በመጠናቀቁ በዛሬው ዕለት ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት መሆኑን ኢዜአ ዘግቧል። የስፖርት ማዘውተሪያው ግንባታ ለስፖርታዊ እንቅስቃሴ በሚያመች መልኩ የተገነባ በመሆኑ የቀደመ አግልግሎቶቹን እንደሚሰጥ ተገልጿል፡፡ የስፖርት ማዘውተሪያ ሥፍራው ግንባታ የክረምት በጎ ፈቃድ ፕሮጀክት አካል መሆኑም ተገልጿል። (አዲስ ማለዳ) በዘመነ ት ህነግ አዲስ አበባ ውስጥ ወጣቶች ምንም ዓይነት … [Read more...] about በአራዳ ክፍለ ከተማ ዜጎች የስፖርት ሜዳ አገኙ
በሕገ ወጥ የውጭ ሀገራት ገንዘብ ምንዛሪ በተሰማሩ አካላት ላይ እርምጃ እየተወሰደ ነው
የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስና ከኦሮሚያ ፖሊስ ጋር በመቀናጀት በሕገ ወጥ የውጭ ሀገራት ገንዘብ ምንዛሪ በተሰማሩ ግለሰቦችና ድርጅቶቻቸው ላይ ጥናትን መሰረት ያደረገ እርምጃ መወሰዱን አስታውቋል፡፡ አገልግሎቱ ለሚዲያ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው ባለፉት ሁለት ወራት በሕገ ወጥ የውጭ ሀገራት ገንዘቦች ምንዛሪ ዙሪያ ሰፊና ጥልቀት ያለው ጥናት ሲካሄድ እንደነበር አመልክቷል፡፡ ችግሩ በጥናት ከተለየ በኋላም መረጃዎችንና ማስረጃዎችን መነሻ በማድረግ በተከናወነው ክትትል በሕገወጥ የውጭ ምንዛሪ ላይ ተሳታፊ የነበሩ 48 ግለሰቦችና ከፍተኛ መጠን ያላቸው የተለያዩ ሀገራት ገንዘቦች እንዲሁም ከድርጊቱ ጋር የተያያዙ የባንክ ደብተሮችና ልዩ ልዩ ሰነዶች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርጓል ነው የተባለው፡፡ በቁጥጥር ስር የዋሉት ግለሰቦች … [Read more...] about በሕገ ወጥ የውጭ ሀገራት ገንዘብ ምንዛሪ በተሰማሩ አካላት ላይ እርምጃ እየተወሰደ ነው
“ከሩቁ የሚፈራ የመከላከያ ሠራዊት ፈጥረናል”
ሳይዋጋ የሚያሸንፍ ጠንካራ የመከላከያ ሰራዊት እየገነባን ነው የመከላከያ ሠራዊት ቀንን ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀ "የጥንካሪያችን ምንጭ ሕዝባችን ነው" በሚል መልዕክት የፓናል ውይይት ተካሄደ። በመርሃ ግብሩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የመከላከያ ሚኒስቴር ሚኒስትር አብርሐም በላይ (ዶክተር)፣ አሁን በኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት ግንባታ ከፍተኛ አቅም ተፈጥሯል፤ ከሩቁ የሚፈራ መከላከያ ሠራዊት ፈጥረናል ብለዋል። የኢትዮጵያ ጠላቶች ሳንቆም ሊጥሉን ሞክረዋል፤ አሁን ቆመን ማንም ሊነቀንቀን የማይችልበት ደረጃ ደርሰናል ያሉት ሚኒስትሩ፣ በአሁኑ ጊዜ ሳይዋጋ የሚያሸንፍ ሠራዊት መገንባት መቻሉን አንስተዋል። ኢትዮጵያ የግዛት አንድነቷ በማንም እንደማይሸረፍ በመስዋዕትነት የሚያረጋግጥ ጀግና ወታደር ያላት ሀገር እንደሆነች የገለጹት ሚኒስትሩ፣ ይህን በተግባር እያረጋገጠ … [Read more...] about “ከሩቁ የሚፈራ የመከላከያ ሠራዊት ፈጥረናል”
“በመከላከያ ኃይላችን መሥዋዕትነት” የሰላም ንግግሩ ይቀጥላል – የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ቁልፍ የሚባሉ የትግራይ ከተሞችን መቆጣጠሩን ቀጥሏል ሲል የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ገለጸ። ይህንን ሲያደርግም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በከተሞች ውጊያ ሳይደረግ የህወሓትን ወታደራዊ ዐቅም ለማሽመድመድ የሚያስችል ስልት ተጠቅሟል። የኢትዮጵያ መንግሥት ከሰብአዊ የርዳታ ተቋማት ጋር በመቀናጀት በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች ሰብአዊ ርዳታ እንዲደርስ እየሠራ ይገኛል። የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት በእነዚህ አካባቢዎች አገልግሎት ለመጀመር የሚያስችል ዝግጅት እንዲያፋጥኑ እያደረገ ነው። ከየአካባቢው ማኅበረሰብ ጋር በመነጋገር ሕዝባዊ አስተዳደር የሚቋቋምበትንና ማኅበራዊ አገልግሎቶች የሚጀምሩበትን መንገድ እያመቻቸ ይገኛል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በአፍሪካ ኅብረት በኩል በደቡብ አፍሪካ በሚደረገው የሰላም ንግግር የሚሳተፍ ይሆናል። አጋጣሚውንም … [Read more...] about “በመከላከያ ኃይላችን መሥዋዕትነት” የሰላም ንግግሩ ይቀጥላል – የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ከመንግሥት ግዢ ጋር በተያያዘ የሚፈጸመው ሌብነት ሊታነቅ ነው
ሁሉም የፌዴራል ተቋማት የኤሌክትሮኒክስ የመንግሥት ግዥ ሥርዓትን ሊጠቀሙ ነው በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ሁሉም የፌዴራል ተቋማት የኤሌክትሮኒክስ የመንግሥት ግዥ ሥርዓትን ይጠቀማሉ ሲል የመንግሥት ግዥና ንብረት ባለሥልጣን አስታወቀ፡፡ የባለሥልጣኑ የኤሌክትሮኒክስ የመንግሥት ግዥ ሲስተም ፕሮጀክት ማናጀር አቶ ታደሰ ከበደ በተለይ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ እስካሁን ባለው ጊዜ ውስጥ በሲስተሙ ከ25 በላይ የሚሆኑ ጫረታዎች ወጥተዋል፡፡ በቀጣይ ሁለት ዓመታት የፌዴራል መስሪያ ቤቶች ላይ ትኩረት ተደርጎ ይሰራል፡፡ በቀጣይ ሥርዓቱን ወደ ክልሎች በማውረድ ይሰራል ያሉት አቶ ታደሰ፤ በ2015ና 2016 በጀት ዓመት መጨረሻ ድረስ ሁሉም የፌዴራል ተቋማት ጨረታዎችን የሚያወጡትና ግዥዎችን የሚያከናውኑት ሲስተሙን በመጠቀም ይሆናል ብለዋል፡፡ በዚህም እንደ አገር ያለውን … [Read more...] about ከመንግሥት ግዢ ጋር በተያያዘ የሚፈጸመው ሌብነት ሊታነቅ ነው
የወሲብ ምስሎች (ፖርኖግራፊ) ሥርጭት ከኢትዮጵያ እንዲታገድ ዘመቻ ተጀመረ
በኢትዮጵያ የወሲብ ቪዲዮዎችን የሚያሰራጩ ድህረገጾችን ለማሳገድ በአንድ የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት አባል ፊርማ ማሰባሰብ ተጀመረ። በኢትዮጵያ የወሲብ ቪዲዮዎችን የሚያሰራጩ ድህረገጾችን ለማሳገድ ፊርማ ማሰባሰብ መጀመሩን የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባል የሆኑት የተከበሩ ዶ/ር ፈትሂ ማህዲ ከብስራት ራዲዮ ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል።በአንድ ግለሰብ ተነሳሽነት የተጀመረዉ እንቅስቃሴዉ አሁን ላይ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባል በሆኑ 15 በሚደርሱ ሌሎች አባላትም ድጋፍ ማግኘቱን ጣቢያችን ሰምቷል። የማስታወቂያ ባለሙያ በሆነዉ አለማየሁ አጥናፍሰገድ በተባለ ግለሰብ በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ድህረገጾቹን ለማሳገድ እንዲሁም በህጻናት እና ወጣቶች አእምሮ ላይ የሚያደርሰዉን ጫና በማስተማር እና ማህበረሰብን የማንቃት እንቅስቃሴ አንድ ብሎ መጀምሩን ለብስራት ራዲዮ … [Read more...] about የወሲብ ምስሎች (ፖርኖግራፊ) ሥርጭት ከኢትዮጵያ እንዲታገድ ዘመቻ ተጀመረ
ትህነግና ኢትዮ 360 በአማራ ክልል ሰብል እንዲወድም በቅንጅት እየሠሩ ነው
ምዕራብ ጎንደርን ጨምሮ ሰፊ እርሻ መሬት ያላቸው አካባቢዎች ሰብል የሚሰበስብ ሰራተኛ ማስታወቂያ ሲያወጡ ይህ የመጀመርያቸው አይደለም። ማህበራዊ ሚዲያ በማይታወቅበት ጊዜ በኢቲቪና አማራ ቲቪ ጭምር በሚሊዮን የሚቆጠር ሰራተኛ እንፈልጋለን ብለው ማስታወቂያ ሲያስነግሩ ኖረዋል። ባለፈው አመት በዛ ቃውጢ ጦርነት ወቅት በማህበራዊ ሚዲያ በርካታ ሰብል የሚሰበስብ ሰራተኛ በማስታወቂያ ጠርተዋል። በሌላ አካባቢ ያለው አርሶ አደር የራሱ ሰብል እስኪደርስ ለአንድና ሁለት ወር ሰርቶ እንደሚመለስ ይታወቃል። በቋሚነት በርሃ ወርዶ የሚሰራ፣ ካምፕ ተሰርቶለት በአካባቢው የሚከርም ሞልቷል። የሰብል ስብሰባን ብቻ ስራቸው አድርገው በቆላማ አካባቢዎቹ የሚኖሩ በርካታ ወጣቶች አሉ። ለረዥም አመታት ዩኒቨርሲቲዎች ከሚቀበሉት ወጣት በላይ የቋራ፣ የመተማ፣ አርማጭሆ፣ ወልቃይት ጠገዴ አካባቢዎች ሰብል … [Read more...] about ትህነግና ኢትዮ 360 በአማራ ክልል ሰብል እንዲወድም በቅንጅት እየሠሩ ነው
የትህነግና የሸኔ ተላላኪዎች በናዝሬት እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል
በአዳማ ከተማ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን ጨምሮ 82 የሸኔና የህወሃት ተላላኪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገለጸ:: ሐሙስ መስከረም 19 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) በአዳማ ከተማ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን ጨምሮ 82 የሸኔና አሸባሪው ህወሃት ተላላኪዎች በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የከተማዋ ፀጥታና አስተዳደር ጽሕፈት ቤት ገልጿል። የአዳማ ከተማ ፀጥታና አስተዳደር ጽሕፈት ቤት ሀላፊ መኩሪያ ድንቁ ለኢዜአ እንደገለጹት አሸባሪው ሸኔና የህወሃት ተላላኪዎች በከተማዋ መስቀልና ኢሬቻን ጨምሮ ህዝባዊ በዓላትን ለማወክ እንቅስቃሴ ሲያደርጉ ነበር። በዚህም 33 የሸኔና አባ ቶርቤ አባላት እንዲሁም 49 የህወሃት ሴሎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ገልጸዋል። በመጪው ቅዳሜና እሁድ በሆራ ፊንፊኔና ቢሾፍቱ ሆራ አርሰዲ የሚከበረው የኢሬቻ በዓል ያለምንም የፀጥታ ችግር … [Read more...] about የትህነግና የሸኔ ተላላኪዎች በናዝሬት እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል










